en
Feedback
ETHIO ≈ SCHOOL

ETHIO ≈ SCHOOL

Open in Telegram

ይህ ለተማሪዎች እና ለትምህርት ፈላጊዎች ተብሎ የተዘጋጀ ፈጣን የሆነ መረጃ የሚያገኙበት ቻናል ነው። እንዲሁም በተጨማሪ መረጃወችን በመሰብሰብ በሁሉም የ ት/ት ደረጃ ተማሪን የሚመለከት መረጃ በፍጥነት እናደርሳለን። ለCross ፦ 👇👇👇 👍 @Gashushu 👍 @Gashtiman25 ❤Join❤ 👇👇👇 @merejamnch

Show more
5 484
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
❤ማንበብ ሰው ያድርጋል. አንዳንድ ድንቃ ድንቅ አባባሎች እና የ ዓለም ክስተቶችን ወይም ተፈጥሮዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ??? እንግድያውስ... Join And Forward 👇👇👇 https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0 https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0

#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት
#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር ብሏል ሚኒስቴሩ። በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተገልጿል። " የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም በጉዳዩ ዙሪያ የመከሩ ሲሆን አሁን በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር እንደሚችሉ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። በዚህም መሰረት ከጥር 1/2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን ይጀምራሉ ተብሏል። በመሆኑም በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲዎቹ የሚያደርጉትን ጥሪ እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል። 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት
+2
#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር ብሏል ሚኒስቴሩ። በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተገልጿል። " የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም በጉዳዩ ዙሪያ የመከሩ ሲሆን አሁን በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር እንደሚችሉ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። በዚህም መሰረት ከጥር 1/2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን ይጀምራሉ ተብሏል። በመሆኑም በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲዎቹ የሚያደርጉትን ጥሪ እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል። 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

#ጥቆማ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሕክምና ኮሌጅ የጥርስ ሕክምና እና ማክሲሎፌሻል ቀዶ ሕክምና ትምህርት ክፍል ለ2016 ዓ.ም አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በመቀጠል የተገለፁት
#ጥቆማ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሕክምና ኮሌጅ የጥርስ ሕክምና እና ማክሲሎፌሻል ቀዶ ሕክምና ትምህርት ክፍል ለ2016 ዓ.ም አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በመቀጠል የተገለፁትን መስፈርቶች የምታሟሉ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑንን ኮሌጁ ገልጿል፡፡ ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦ - ከታወቀ የመንግሥት ተቋም በ Dental Medicine (DDS/DDM) የተመረቀ/ች - ሁለት ዓመት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ያላት - በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ የሚገኝ/የምትገኝ - እድሜ ከ40 ዓመት በታች - ስፖንሰርሺፕ ማምጣት የሚችል/የምትችል የማመልከቻ ቀን፡- ከጥር 01 እስከ የካቲት 13/2016 ዓ.ም የፈተና ቀን፡- የካቲት 18 እና 19/2016 ዓ.ም የምዝገባ ቀን፡- የካቲት 29/2016 ዓ.ም ትምህርት የሚጀምረው፡- መጋቢት 02/2016 ዓ.ም 📌Share&forward📌 📌Join📌 👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

# Maths MCQ on set theory 1. Which symbol is used to denote a universal set?    a) U    b) ∅    c) {}    d) ∈    2. Which operation gives the elements present in both sets A and B?    a) Union    b) Intersection    c) Difference    d) Complement    3. Which of the following is not a subset of set A?    a) A itself    b) ∅ (empty set)    c) Set containing all elements       except one element present in A    d) A set containing elements not        present in A 4. How many subsets can be formed from a set with n elements?    a) 2^n    b) 2n    c) n!    d) n^n 5. If A and B are two sets, and A is a proper subset of B, then which of the following statements is true?    a) A ∪ B = B    b) A ∩ B = B    c) A ∪ B = A    d) none 6. If A ⊆ B, it means that:    a) A is a proper subset of B    b) B is a proper subset of A    c) A is a subset of B, including the        possibility of being equal    d) B is a subset of A, excluding         the possibility of being equal    7. If A ∩ B = A, what is the relationship between sets A and B?    a) A is a proper subset of B    b) A is a superset of B    c) A and B are disjoint sets    d) none 8. The complement of the universal set is:    a) An empty set    b) The universal set itself    c) The set containing all          non-universal elements    d) None of the above    9. The set difference A - B is defined as:    a) The set of elements common         to both A and B    b) The set of elements in either A         or B (or both)    c) The set of elements in A that          are not in B    d) The set of elements in B that          are not in A    10. The power set of a set A is defined as:    a) The set of all subsets of A,          including the empty set    b) The set of all proper subsets of             A    c) The set of elements in A that          are also elements of another set    d) The set of elements in A that         are not in another set    #Answer 1. a) U 2. b) Intersection 3. d) A set containing elements not present in A 4. a) 2^n 5. a) A ∪ B = B 6. c) A is a subset of B, including the possibility of being equal 7. a) A is a proper subset of B 8. a) An empty set 9. c) The set of elements in A that are not in B 10. a) The set of all subsets of A, including the empty set https://t.me/qubeeacademy https://t.me/qubeeacademy If you're Highschool or Freshman or university student seeking video tutorials, check out our YouTube channel 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/channel/UCLPTQfMXS6we7aTT4g9MwCw

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በባንክ እና ፋይናንስ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመጀመር ዝግጅት ላይ ነው። የዩኒቨርሲቲው የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በባንክ እና ፋይናንስ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም (MS in
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በባንክ እና ፋይናንስ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመጀመር ዝግጅት ላይ ነው። የዩኒቨርሲቲው የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በባንክ እና ፋይናንስ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም (MS in Banking and Finance) ለመጀመር የስርዓተ ትምህርት ረቂቅ ግምገማ አካሒዷል። ረቂቁ ተጨማሪ ግብዓቶች ተጨምረውበት ከዳበረ በኋላ ወደ ሥራ እንደሚገባ ተገልጿል። https://t.me/joinchat/Jj9zCCe-pnoyYmY0

በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ “Winter In-service” ፕሮግራም የምትማሩ ነባር እና አዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥር 01 እና 02/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ትምህርት ጥር 0
በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ “Winter In-service” ፕሮግራም የምትማሩ ነባር እና አዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥር 01 እና 02/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ትምህርት ጥር 03/2016 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል። ለበለጠ መረጃ፦ www.mwu.edu.et 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

#ጥቆማ የአዲስ ቻምበር ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የተለያዩ አጫጭር የቢዝነስ ስልጠናዎችን ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ ይሰጣል፡፡ ከታህሳስ 22 እስከ ጥር 25/2016 ዓ.ም የሚሰጡት ስልጠናዎች፤ ፋይናንሺያል
#ጥቆማ የአዲስ ቻምበር ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የተለያዩ አጫጭር የቢዝነስ ስልጠናዎችን ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ ይሰጣል፡፡ ከታህሳስ 22 እስከ ጥር 25/2016 ዓ.ም የሚሰጡት ስልጠናዎች፤ ፋይናንሺያል ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ኮሚዩኒኬሽን፣ ሴክሬተሪያል ሳይንስና ኦፊስ ማኔጅመንትን ጨምሮ በ12 የሙያ መስኮች ላይ ትኩረት ያደረጉ ናቸው፡፡ ለበለጠ መረጃ፦ ☎️ 011-551-3882 / 0911194965 / 0913249766 / 0911343078 የኢ-ሜይል አድራሻዎች፦ dejedesalegn@gmail.com assefakasa2@gmail.com hiwottlhn9@gmail.com (የስልጠናዎቹን አይነት፣ የጊዜ ርዝመት እና ክፍያ መጠን የሚያሳይ ከኢንስቲትዩቱ የተገኘ መልዕክት ከላይ ተያይዟል፡፡) 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

#Amhara በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢ
#Amhara በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን በክልሉ ያለው የጸጥታ ችግር በተማሪዎች ምዝገባ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል ብለዋል። ክልሉ 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር ሲገባው ያን ማድረግ አለመቻሉን ኃላፊው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ከሁለት ሚሊዮን በላይ ያልተመዘገቡ ተማሪዎች መኖራቸውን የገለፁት ኃላፊው ፤ መማር የሚገባቸው ተማሪዎች የትምህርት ዕድል እንዳያገኙ መደረጉን አመልክተዋል። በጸጥታው ችግር ምክንያት ሁለት ሺህ በሚጠጉ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን ከመማር ማስተማር ሥራ ውጪ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይሁን እንጂ መምህራኑ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ የማድረግ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ባለው ግጭት "ወደ 42 ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ጉዳት ማስተናገዳቸውንም" ጠቁመዋል። 📌Share&forward📌 📌Join📌 👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

#Update በሚሰጠው የአቅም መለኪያ ፈተና ከደረጃው ዝቅ የሚል እንጂ የሚባረር ሰራተኛ እንደማይኖር የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ ከ16 ሺህ በላይ የከተማ አስተደደሩ ሠራተኞች ሊፈተኑ መሆኑ ከተገለፀ ጊዜ ጀምሮ የከተማ አስተዳደሩ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆይተዋል፡፡ መናኸሪያ ሬዲዮም የፈተናውን አስፈላጊነትና የሰራተኞቹን ቀጣይ እጣፈንታ አስመልክቶ የከተማ አስተዳደሩን ጠይቋል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ስር ካሉ በተደጋጋሚ የህዝብ ቅሬታ የሚነሳባቸው፤ለሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጡ እንዲሁም የአገልግሎት ጥራታቸው የተጓደሉ 16 ተቋማትን መለየታቸውን የሚናገሩት በከተማ አስተዳደሩ የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ የሰው ሃብት አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ መላኩ ታምሩ አሰራራቸውን ለማሻሻል የተቋማቱን አሰራር ፈርሶ በድጋሚ እንዲደራጅ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ ከተቋም ማደራጀት በኋላ ለቦታው የሚመጥን የሰው ሃይል ማዘጋጀት በማስፈለጉ ሰራተኞችን ወደ መፈተን እንደተገባም ያስረዳሉ፡፡ ፈተናው ከስራው ጋር ይገናኛል ወይ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ፈተናው በቀጥታ ስራውን የተመለከተ መሆኑን ጠቅሰው ሶስት አይነት ባህሪ እንዳለው አቶ መላኩ አስረድተዋል፡፡ በዚህ መንገድ ተፈትነው ለማለፊያ የተቀመጠውን እንደ ደረጃቸው 50 እና60 በመቶ ካመጡ በመቀጠል ወደ ድልድል እንደሚገቡ እንዲሁም በድልድሉም 3 ዘርፎች ለውድድር እንደሚቀርብና ከዚያም ከሶስቱ መካከል ያሸነፉበት ላይ እንደሚመደቡም ሃላፊው ገልፀዋል፡፡ ሌላው መመዘኛውን ያላለፉ ሰራተኞች ቀጣይ እጣፈንታ ምን ይሆናል የሚለው ጉዳይ በተለይ ሰራተኞቹን አብዝቶ ያስጨነቀና ብዙ ጥያቄዎችን ያስነሳ እንደመሆኑ ይህንንም በተመለከተ ሃላፊውን ጠይቀናል፡፡ ማንኛውም ለፈተና የቀረበ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛ መመዘኛውን ቢወድቅ እንደማይባረር የገለጹ ሲሆን ከነበረዉ ደረጃ ዝቅ ብሎ በነበረው የደሞዝ መጠን ስራዉን እእዲቀጥል ይደረጋል ብለዋል፡፡ እንደ ሃላፊው ገለፃ ሰራተኛው አሁን ፈተናውን ቢወድቅም የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቶት በድጋሚ ተፈትኖ ማለፍ ካልቻለ ግን ጥቅሙ ተከብሮለት ይሰናበታል ነዉ ያሉት፡፡ ለፈተናው በተለያየ ምክንያት መገኘት ያልቻለ ተፈታኝ ምክንያቱ ታይቶ እንደ አስፈላጊነቱ ለፈተና የሚቀርብበት መንገድ እንደሚመቻችም ጭምር ተጠቁሟል። ፈተናውም በሶስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ማለትም በአማርኛ፣በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ እንደተዘጋጀም ተመላክቷል። በቴክኒክ ችግር ምክንያት ሳይሰጥ የቀረው የመንግሥት ሰራተኞች የመመዘኛ ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20 እንደሚሰጥ ከተማ አስተዳደሩ የሳወቀ ሲሆን ለደረሰው መጉላላትም መላው ሰራተኞቹን ይቅርታ ጠይቋል። 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

❤ማንበብ ሰው ያድርጋል. አንዳንድ ድንቃ ድንቅ አባባሎች እና የ ዓለም ክስተቶችን ወይም ተፈጥሮዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ??? እንግድያውስ... Join And Forward 👇👇👇 https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0 https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0

#ጥቆማ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ Oral and Mailloficial Surgery የድህረ-ምረቃ ሬዚደንሲ 4ኛ ዙር ሠልጣኞችን ተቀብሎ ለማስተማር ይፈልጋል። ተከታዮቹን ቅድመ ሁኔታዎች የ
+1
#ጥቆማ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ Oral and Mailloficial Surgery የድህረ-ምረቃ ሬዚደንሲ 4ኛ ዙር ሠልጣኞችን ተቀብሎ ለማስተማር ይፈልጋል። ተከታዮቹን ቅድመ ሁኔታዎች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች በሆስፒታሉ ሜዲካል ኮሌጅ ሬጅስትራር መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። - በትምህርት ሚኒስቴር ከታወቀ የመንግሥት ትምህርት ተቋም በ DMD/DDS የተመረቁ - ሁለት ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው - የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ - የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) ወስደው ማለፋቸውን የሚያሳይ ውጤት ማቅረብ የሚችሉ ምዝገባ የሚካሄደው፦ ከታህሳስ 15 እስከ ጥር 05/2016 ዓ.ም ተከታዩን ሊንክ በመጠቀም ይመዝገቡ፦ sis.y12hmc.edu.et (የኮሌጁ መልዕክት ከላይ ተያይዟል።) 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

መቐለ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ጆርናል ይፋ አድርጓል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ "የቢዝነስ እና ልማት ጆርናል" /MUJBD/ ዛሬ ይፋ አድርጓል:: መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀደም በተለያዩ
መቐለ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ጆርናል ይፋ አድርጓል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ "የቢዝነስ እና ልማት ጆርናል" /MUJBD/ ዛሬ ይፋ አድርጓል:: መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የትምህርት እና የምርምር መስኮች የሚታተሙ 12 ጆርናሎች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

#Tigray በትግራይ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በዚህ ሳምንት ይሰጣል፡፡ ፈተናው ለሦስት ቀናት ከታህሳስ 18 አስከ 20/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ ፈተናውን ለመውሰድ 60 ሺህ ተማሪዎች
#Tigray በትግራይ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በዚህ ሳምንት ይሰጣል፡፡ ፈተናው ለሦስት ቀናት ከታህሳስ 18 አስከ 20/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ ፈተናውን ለመውሰድ 60 ሺህ ተማሪዎች መመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ መግለጹ ይታወሳል፡፡ 📌Share&forward📌 📌Join📌 👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የሩሲያ የትምህርት ማዕከል በይፋ አስመርቋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሩሲያው Ulianovsk የፔዳጎጂ ዩኒቨርሲቲ መካከል የተደረገን የአጋርነት ትብብር ተከትሎ ማዕከሉ መከፈቱ ተገ
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የሩሲያ የትምህርት ማዕከል በይፋ አስመርቋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሩሲያው Ulianovsk የፔዳጎጂ ዩኒቨርሲቲ መካከል የተደረገን የአጋርነት ትብብር ተከትሎ ማዕከሉ መከፈቱ ተገልጿል። ማዕከሉ የሩሲያ ቋንቋ ትምህርት እንደሚሰጥ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም በሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የባህልና የትምህርት ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ታምኖበታል፡፡ ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች በምርምር እንዲሁም በትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በጋራ ለመስራት እንደሚያስችላቸውም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ 📌Share&forward📌 📌Join📌 👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

photo content
+1

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ2016 አዲስ ለተመደቡ እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትለው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተው ወደ ተቋሙ ለተመደቡ ተማሪዎች አቀባበል ማድረግ ጀምሯል።
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ2016 አዲስ ለተመደቡ እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትለው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተው ወደ ተቋሙ ለተመደቡ ተማሪዎች አቀባበል ማድረግ ጀምሯል። ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ምዝገባ ታህሳስ 15 እና 16/2016 ዓ.ም እንደሚከናወን መግለፁ ይታወቃል። 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

በአማራ ክልል በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቷል። በክልሉ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 8
+1
በአማራ ክልል በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቷል። በክልሉ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 8,434 ተማሪዎች ብቻ የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ገልፀዋል። በተፈጥሮ ሳይንስ 54 ተማሪዎች 600 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡ ሲሆን፤ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ደግሞ ስድስት ተማሪዎች 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን ጠቁመዋል። ከደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት 646 በማምጣት በክልሉ ቀዳሚ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ኤልያስ ደሳለኝ እንዲሁም ከባህር ዳር ኤስ.ኦ.ኤስ ትምህርት ቤት 632 በማስመዝገብ ከሴቶች ቀዳሚ ውጤት ያመጣችው ተማሪ ሶስና ደሳለኝ ከተሸላሚዎቹ መካከል ይገኙበታል። ተማሪዎቹ ከገንዘብ በተጨማሪ የሞባይል ስልክ እና የመጽሐፍት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

በሔሊኮፕተር ፈጠራው 100 ሺህ ብር የተሸለመው ወጣት የግሉን አውሮፕላን ሠርቶ በሰማይ ላይ መንሳፈፍ የልጅነት ምኞቱ ነበር ፣ በሽረ እንደሥላሴ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ዕበ ለገሠ። ሐሳቡን ወደ ተ
+1
በሔሊኮፕተር ፈጠራው 100 ሺህ ብር የተሸለመው ወጣት የግሉን አውሮፕላን ሠርቶ በሰማይ ላይ መንሳፈፍ የልጅነት ምኞቱ ነበር ፣ በሽረ እንደሥላሴ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ዕበ ለገሠ። ሐሳቡን ወደ ተግባር ለመለወጥ እልህ አስጨራሽ ጉዞ ማድረጉን ይናገራል። ከበርካታ ጥረቶች በኋላ ለሦስት ደቂቃ ያህል መብረር የምትችል ሔሊኮፕተር መስራቱን ይናገራል። በስምንት ወራት ውስጥ ተሠርታ የተጠናቀቀችው ሔሊኮፕተሯ፣ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባት ዕበ ገልጿል፡፡ ለአብራሪው ብቻ የሚሆን ቦታ ቢኖራትም፣ እስከ አራት ሰው ወይም አራት ኩንታል ጭነትን ተሸክማ መብረር እንደምትችል ተናግሯል፡፡ ሔሊኮፕተሯ ተጠናቃ ወደ ሥራ ስትገባ ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎዎችን ለማጥፋት፣ የአንበጣ መንጋን ለመከላከልና ቅኝት ለማድረግ ታገለግላለች፡፡ ሰዎች ለትራንስፖርት ሊጠቀሙበትም ይችላሉ ብሏል። ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ በተካሔደው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ውድድር፣ ሔሊኮፕተር ሠርቶ በማቅረብ አንደኛ በመውጣት 100 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል። የሽልማቱን ገንዘብ በትግራይ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንደሰጠ ወጣቱ ጠቁሟል፡፡ ሔሊኮፕተሯ ተሻሽላ ገበያ ላይ መዋል የምትችልና የተሠራችበት ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ በአካባቢ የሚገኙ መሆናቸውም ወጣቱን ለአሸናፊነት አብቅቶታል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ፈጠራውን ለማገዝ ቃል እንደገባለት የገለጸው ዕበ፣ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ ነገር ይዞ ለመቅረብ እንደሚሠራ ተናግሯል፡፡ #ሪፖርተር 📌Share&forward📌          📌Join📌           👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጊብሰን ትምህርት ቤቶችን የዕውቅና ፍቃድ አግዷል። ባለስልጣኑ ለጊብሰን አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም
+3
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጊብሰን ትምህርት ቤቶችን የዕውቅና ፍቃድ አግዷል። ባለስልጣኑ ለጊብሰን አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ለጊብሰን ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ታህሳስ 12/2016 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ የዕውቅና ፍቃዳቸው መታገዱን ገልጿል። የጊብሰን ትምህርት ቤቶች የዕውቅና ፍቃድ የታገደባቸው ምከንያቶች፦ - የስርዓተ ትምህርት ጥሰት መፈፀም፣ - የትምህርት ቢሮ ካላንደርን አለመጠቀም፣ - ከመንግሥት ፖሊሲ መመሪያና ደንቦች ጋር የሚጣረሱ መመሪያዎች መከተል፣ -ከስርዓተ ትምህርቱ ውጪ የሆኑና ያለፀደቁ የማስተማሪያ መጽሐፍት ለማስተማሪያነት መጠቀም። ትምህርት ቤቱ የማስጠንቀቂ ደብዳቤ ተልኮለት በ15 ቀናት ውስጥ ማስተካከያ በማድረግ አፈፃፀሙን በሪፖርት እንዲያሳውቅ በባለስልጣኑ የተጠየቀ ቢሆንም በተጠየቀው ጊዜ ውስጥ ትምህርት ቤቱ ምላሽ እንዳልሰጠ ባለስልጣኑ ገልጿል። በዚህም ከታህሳስ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለትምህርት ቤቶቹ የተሰጠው የዕውቅና ፍቃድ የታገደ መሆኑን ባለስልጣኑ አሳውቋል። 📌Share&forward📌 📌Join📌 👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯