en
Feedback
Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy

Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy

Open in Telegram
414
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የማዕከሉ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን በ52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገባ። ****////**** ግንቦት 7/2015 ዓ.ም ከግንቦት 8/2015-13/2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ለሚካሄደው 52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ላይ ለመሳተፍ ማዕከሉ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ አዲስ አበባ ገብቷል። ማዕከሉ በሻምፒዮናው በ31 ሴት እና በ47 ወንድ በድምሩ በ78 አትሌቶች በአጭር፣ መካከለኛ፣ በረጅም ርቀት እና በሜዳ ተግባራት ስፖርት አይነቶች ይሳተፋል። #መልካም_የውድድር_ግዜ_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!!

ማዕከሉ በሴቶች እግር ኳስ በአቋም መለኪያ ጫወታ የድሬደዋውን መሲ ፓይሌት ፕሮጀክትን 1 ለ 0 አሸነፈ። **************///************ ሚያዚያ 22/2015 ዓ.ም ዛሬ በድሬደዋ አርቲ
+9
ማዕከሉ በሴቶች እግር ኳስ በአቋም መለኪያ ጫወታ የድሬደዋውን መሲ ፓይሌት ፕሮጀክትን 1 ለ 0 አሸነፈ። **************///************ ሚያዚያ 22/2015 ዓ.ም ዛሬ በድሬደዋ አርቲፊሻል ስቴዲየም ከሰዓት በኋላ ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የማዕከሉ ሴቶች U17 እግር ኳስ ቡድን አቻውን የድሬደዋውን መሲ ፓይሌት ፕሮጀክትን በተለየ የኳስ ቁጥጥር 1ለ0 በሆነ ጎል አሸነፈ። በድሬደዋ ከተማ በሚገኘው አርቲፊሻል ስቴዲየም የተከናወነው ጫወታ በ7 ቁጥሯ የአማካይ ተጫዋች ትሁን ገበየሁ ጫወታው በተጀመረ 6ተኛው ደቂቃ ላይ የማሸነፊያውን ጎል ለማዕከሉ ከመረብ አሳርፋለች። ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በሴቶች እግር ኳስ በአቋም መለኪያ ጫወታው ሃዋሳ ላይ የሲዳማውን ፕራይም ፕሮጀክትን ሲያሸንፍ ከከማል አካዳሚ ጋር ባካሄደው ጫወታ ደግሞ ኣቻ ተለያይቷል። በጫወታውም በአሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ እና በአሰልጣኝ ወርቅነሽ የሚሰለጥነው የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በነበራቸው ጫወታ ዛሬ በከተማው በነበረው የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ዝናባማና በስቴዲየሙ ውስጥ የነበረውን ውሃ በመቋቋም በኳስ ቁጥጥር የበላይነት በመውሰድ እና የጎል አጋጣሚዎችን በመፍጠር የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። #G_O_A_L ያስቆጠረች #ትሁን_ገበየሁ

ማዕከሉ በአፍሪካ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5000 ሜ. ሀገራችንን ወክሎ የሚወዳዳር 1 አትሌት አስመረጠ። ^^^^^^^^^///^^^^^^^^^ 💪💪💪 ሚያዚያ 1/2015 ዓ.ም በቀጣ
ማዕከሉ በአፍሪካ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5000 ሜ. ሀገራችንን ወክሎ የሚወዳዳር 1 አትሌት አስመረጠ። ^^^^^^^^^///^^^^^^^^^ 💪💪💪 ሚያዚያ 1/2015 ዓ.ም በቀጣይ በዛምቢያ እ.እ.አ ከሚያዝያ 19 ቀን እስከ ግንቦት 3 ቀን 2023 ዓ.ም በሉሳካ ብሔራዊ ሄሮድስ ስታዲየም ከ18/20 ዓመት በታች የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ ለመወዳደር በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል የ5000 ሜ ሰልጣኝ የሆነው አትሌት ንብረት ክንዴ ተመረጠ። #መልካም_ውጤት_ይሁንልህ!!

ማዕከሉ በ3ኛው የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን ተሸላሚ ሆነ። *****************///************** መጋቢት 22/2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ኮሚቴ አዘጋጅነት ከመጋቢት 20-24/2015 ዓ.ም እየተካሄደ ያለው 3ኛው የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ዛሬም ማዕከሉ በ3ኛው ቀን ተሳትፎው ሜዳሊያዎችንና ዲፕሎማውችን አግኝቷል። በሻምፒዮናው ማዕከሉ ዛሬ በ200ሜ. ወንድ የእጅ ጉዳት 4ኛ ዲፕሎማ እና 200 ሜ. ሴት 4ኛ ዲፕሎማ የተገኘ ሲሆን በአጠቃላይ በ3 ቀን የውድድር ግዜ ውስጥ 1 ወርቅ፣ 2 ብር፣ 2 ነሃስ እና 12 ዲፕሎማዎችን አግኝቷል። በመቀጠልም ሻምፒዮናው ነገም መጋቢት 23/2015 ዓ.ም ይቀጥላል #መልካም_ውጤት_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!!

ማዕከሉ በ2ኛው ቀን 3ኛው የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን ተሸላሚ ሆነ። *****************///************** መጋቢት 21/2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ኮሚቴ አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው 3ኛው የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ዛሬም ማዕከሉ በ2ኛው ቀን ተሳትፎው የተለያዩ ሜዳሊያዎችንና ዲፕሎማውችን አግኝቷል። በሻምፒዮናው ማዕከሉ በ400ሜ. ሴት የእጅ ጉዳት የብር ሜዳሊያ፣ በ400ሜ. ወንድ የእጅ ጉዳት የነሃስ ሜዳሊያ እና 2 ዲፕሎማዎች የተገኘ ሲሆን በ1500 ሜ ወንድ የእጅ ጉዳት 1 የነሃስ ሜዳሊያ እና 2 ዲፕሎማዎች በአጠቃላይ 1 ብር፣2ነሃስ እና 4 ዲፕሎማዎችን ሰብስቧል። በመቀጠልም ሻምፒዮናው ነገም መጋቢት 22/2015 ዓ.ም ይቀጥላል #መልካም_ውጤት_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!!

ማዕከሉ በ3ኛው የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ሻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ የ800 ሜ. በእጅ ጉዳት ወንድ አገኘ። ****************///********* መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ማዕከሉ ዛሬ በተጀመረው 3ኛው የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ሻምፒዮና ውድድር ላይ በ100 ሜ. የእጅ ጉዳት ሴት፣ በ800 ሜ. የእጅ ጉዳት ወንድ፣ እና በ800 ሜ. ጭላንጭል ወንድ ውድድር ሲያካሂድ ቆይቷል። በሻምፒዮናው ማዕከሉ በ800 ሜ. እጅ ጉዳት በአትሌት ዳንኤል ቢራቱ የወርቅ ሜዳሊያ ሲያገኝ በ800 ሜ. ጭላንጭል ወንድ 2 እና በእጅ ጉዳት ወንድ 2 ዲፕሎማዎችን አግኝቷል። ውድድሩ ነገም መጋቢት 21/2015 ዓ.ም የሚቀጥል ይሆናል #መልካም_ውጤት_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!!

የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጫወታ የሲዳማውን ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 አሸነፈ። **************///************ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም ዛሬ በማዕከ
+4
የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጫወታ የሲዳማውን ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 አሸነፈ። **************///************ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም ዛሬ በማዕከል ሜዳ ላይ ጥዋት 4:00 ሰዓት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የማዕከሉ የወንዶች U17 እግር ኳስ ቡድን አቻውን የሲዳማውን ፕሮጀክት ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያን በተለየ የኳስ ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ። በማዕከሉ ሜዳ ላይ የተከናወነው ጫወታ የአማካይ ተጫዋቹ አንዋር ሙስጂ በ25ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ግብ ለማዕከሉ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጫወታው በሃዋሳ ሎጊታ አርቲፊሻል ስታዲየም የሃዋሳ ከነማ U17 B ቡድንን 4ለ2 በሆነ ጎል ልዩነት አሸንፏል። በጫወታውም በአሰልጣኝ ደረጄ ታመነ የሚሰለጥነው የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በነበራቸው ጫወታ በኳስ ቁጥጥር የበላይነት በመውሰድ እና የጎል አጋጣሚዎችን በመፍጠር የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። በመጨረሻም ሰልጣኞቹ ከአቋም መለኪያ ጫወታው በአካል እና በስነልቦና ከፍተኛ መሻሻሎችን በማሳየት በማዕከሉ የወሰዱትን ስልጠና በውድድሩም በመድገም ከፍተኛ ለውጥ አሳይተዋል። #G_O_A_L ያስቆጠሩ #አንዋር_ሙስጂ #ሮቤል_ቢኒያም #አማኑኤል_ተላማጅ #ዳዊት_ፈተኔ

የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጫወታ የሲዳማውን ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 አሸነፈ። **************///************ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም ዛሬ በማዕከ
+4
የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጫወታ የሲዳማውን ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 አሸነፈ። **************///************ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም ዛሬ በማዕከል ሜዳ ላይ ጥዋት 4:00 ሰዓት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የማዕከሉ የወንዶች U17 እግር ኳስ ቡድን አቻውን የሲዳማውን ፕሮጀክት ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያን በተለየ የኳስ ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ። በማዕከሉ ሜዳ ላይ የተከናወነው ጫወታ የአማካይ ተጫዋቹ አንዋር ሙስጂ በ25ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ግብ ለማዕከሉ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጫወታው በሃዋሳ ሎጊታ አርቲፊሻል ስታዲየም የሃዋሳ ከነማ U17 B ቡድንን 4ለ2 በሆነ ጎል ልዩነት አሸንፏል። በጫወታውም በአሰልጣኝ ደረጄ ታመነ የሚሰለጥነው የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በነበራቸው ጫወታ በኳስ ቁጥጥር የበላይነት በመውሰድ እና የጎል አጋጣሚዎችን በመፍጠር የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። በመጨረሻም ሰልጣኞቹ ከአቋም መለኪያ ጫወታው በአካል እና በስነልቦና ከፍተኛ መሻሻሎችን በማሳየት በማዕከሉ የወሰዱትን ስልጠና በውድድሩም በመድገም ከፍተኛ ለውጥ አሳይተዋል። #G_O_A_L ያስቆጠሩ #አንዋር_ሙስጂ #ሮቤል_ቢኒያም #አማኑኤል_ተላማጅ #ዳዊት_ፈተኔ

ማዕከሉ የአቋም መለኪያ ጫወታውን ከኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ጋር አካሄደ። ****///** መጋቢት 15/2015 ዓ.ም በአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሜዳ ላይ ዛሬ 4:00 ሰዓት
+9
ማዕከሉ የአቋም መለኪያ ጫወታውን ከኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ጋር አካሄደ። ****///** መጋቢት 15/2015 ዓ.ም በአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሜዳ ላይ ዛሬ 4:00 ሰዓት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የማዕከሉ የ1ኛ ዓመት ከ17 ዓመት በታች የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ከአቻው ኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከ2ኛ ዓመት ጋር የአቋም መለኪያ ጫወታውን አካሄደ። በጫወታው በማዕከሉ በአሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ የሚሰለጥነው ሴት እግር ኳስ ቡድን በኳስ ቁጥጥር የበላይነት ተወስዶበት እና የጎል አጋጣሚዎችን በለመፍጠሩ የተሻለ እንቅስቃሴ አላደረገም። በመቀጠልም ሰልጣኞቹ በአቋም መለኪያ ጫወታው በታክቲክና፣ በስነልቦና ክፍተቶች በማሳየት በማዕከሉ የተሰጣቸውን ስልጠና በሜዳ ላይ ያልተተገበረበት ጫወታ መሆኑን በሜዳ ላይ በነበረው እንቅስቃሴ ለማየት ችለናል፣ ሰልጣኞቹ በቀጣይ ከላይ የታዩትን ክፍተቶች በማሻሻል እንዲሁም ስልጠናው በነዚህ ነገሮች ላይ አትኩሮ መሰራት እንዳለበት አመላክቶናል ብለዋል አሰልጣኙ። በመጨረሻም ጫወታው የማዕከሉ የ1ኛ ዓመት ሴት እግር ኳስ ቡድን ከአቻው ከኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ 2ኛ ዓመትጋር ባካሄደው ጨዋታ 4:2 በሆነ የጎል ልዩነት ተሸንፏል። #G_O_A_L ያስቆጠሩ #ሊዲያ #ዲቦራ

ማዕከሉ ለ100/200 ሜ.፣ ለ800 ሜ እና ለ1500 ሜ. ሰልጣኞች የውስጥ ምዘና ውድድር አካሄደ። **************//******* መጋቢት 1/2015 ዓ.ም በማዕከሉ የካቲት 30/2015 ዓ.ም በ100/200 ሜ.፣በ800 ሜ. እና ለ1500 ሜ. ለሚሰለጥኑ ሰልጣኞች የውስጥ ምዘና ውድድር ሲሰጥ ቆይቷል። በምዘናው አትሌቶች ያላቸውን ወቅታዊ አቋማቸውን የሚያዩበትና በቀጣይ ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የአጭር፣መከክለኛ፣3000 ሜ. መሰ.፣ የሜዳ ተግባር እና የርምጃ ውድድር ላይ የሚሳተፉ አትሌቶችን የሚለዩበት ምዝና መሆኑን ከአሰልጣኞች ለማወቅ ችለናል። በመቀጠልም በምዘናው ሰልጣኞች የግል ሰዓታቸውን ያሻሻሉበት ውድድር ነበር።

የማዕከሉ U17 ወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከአዳማ ከተማ U20 እግር ኳስ ቡድን ጋር ጫወታ አካሄደ። *************//********** የካቲት 27/2015 ዓ.ም የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ
የማዕከሉ U17 ወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከአዳማ ከተማ U20 እግር ኳስ ቡድን ጋር ጫወታ አካሄደ። *************//********** የካቲት 27/2015 ዓ.ም የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ትላንት እሁድ የካቲት 26/2015 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ስታዲየም ከአቻው ከአዳማ ከተማ U20 ቡድን ጋር የወዳጅነት ጫወታውን አደረገ። ማዕከሉ በወንዶች U17 እግር ኳስ እስከ አሁን ባካሄዳቸው የወዳጅነት ጫወታዎች ሀዋሳ ከተማ U17 ቡድንንና የአሰላውን ፕሮጀክት በአሸናፊነት ሲያጠናቅቅ ከአዳማው U17 ቡድን ጋር በወንጂ ሜዳ ላይ አቻ ተለያይቷ። በመቀጠልም ማዕከሉ ትላንት እሁድ በአዳማ ሜዳ ላይ ከአዳማ ከነማ U20 ቡድን ጋር ባደረገው ጨዋታ ከፍተኛ ፉክክር የታየበት መሆኑ እና የአዳማ ከተማው ቡድን ከ20 ዓመት በታች የሚጫወቱ ተጨዋቾች መሆናቸው የማዕከሉ የ1ኛ ዓመት ሰልጣኞች ልምድ እንደሚያገኙ ለማየት ችለናል።