en
Feedback
Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy

Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy

Open in Telegram
414
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ማዕከሉ በወንዶች እግር ኳስ የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ አቻውን 5ለ2 በሆነ ጎል ልዩነት አሸነፈ። *///** ሰኔ 3/2015 ዓ.ም ዛሬ በአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሜዳ ላይ ከሰዓት በኋላ 9:00 ሰዓት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የሁለቱ ቡድኖች የአቋም መለኪያ ጫወታ በማዕከሉ U17 የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በኳስ የበላይነት አካዳሚውን 5ለ2 በሆነ ውጤት አሸነፈ። በማዕከሉ ሜዳ ላይ የተከናወነው ጫወታ በአማካኝ ተጫዋቹ ግዛቱ ታረቀኝ አማካኝነት ጫዋታው በተጀመረ 12 ተኛው ደቂቃ ላይ የመጀመሪያውን ጎል ለማዕከሉ ከመረብ አገናኝቷል። በጫወታውም በአሰልጣኝ ደረጄ ታመነ የሚሰለጥነው የማዕከሉ የወንዶች U17 እግር ኳስ ቡድን ባሳዩት የኳስ ቁጥጥር እና የበላይነት በመጀመሪያው አጋማሽ የአማካኝ ተጫዋቹን ግዛቱን ተከትለው ሮቤል ቢኒያም እና ናንግ ዱዋር ባስቆጠሩት ጎል ማዕከሉን 3ለ1 በሆነ ውጤት የመጀመሪያውን አጋማሽ በመሪነት አጠናቀዋል። በመቀጠልም የማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአመቱ ውስጥ ባካሄዳቸው በሜዳውና ከሜዳ ወጪ ጫወታዎች አስራ ሁለት የአቋም መለኪያ ጫዎታዎችን አካሂዶ 8 ጫዎታዎችን ሲያሸንፍ 3 ጫዎታዎችን አቻ ሲለያይ አንድ ጫዎታ ተሸንፎ የአመቱን ግብ ማሳካት ችሏል። በመጨረሻም በአሰልጣኝ ደረጄ የሚሰለጥነው ቡድኑ እስካሁን ባካሄዱት የአቋም መለኪያ ጫዎታዎች ሰልጣኞቹ ያገኙት ጥቅም በአካል ብቃት፣ክህሎት፣ ታክቲክና ስነልቦና ዝግጁነት በቀጣይ ለሚኖሩ ስልጠናዎችና ጫዎታዎች ጠንክረው እንዲሰሩና ክፍተቶች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ያግዛቸዋል ብለዋል አሰልጣኙ። #🅖︎🅞︎🅞︎🅛︎ 1. G‌i‌z‌a‌t‌u‌ T‌a‌t‌e‌k‌e‌g‌n‌ 2. R‌o‌b‌e‌l‌ B‌i‌n‌i‌y‌a‌m‌ 3. N‌a‌n‌g‌ D‌u‌w‌a‌r‌ 4. T‌e‌s‌f‌a‌l‌e‌m‌ T‌a‌r‌e‌k‌e‌g‌n‌ 5. N‌a‌t‌h‌r‌e‌t‌ S‌o‌l‌o‌m‌o‌n‌

ማዕከሉ በ52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ6ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ። ****///*** ግንቦት 13/2015 ዓም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየውና የተለያዩ ክለቦች፣ ክልሎች፣ከተማ መስተዳድሮች እና የስፖርት ተቋማቶች የተሳተፉበት 52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ፍፃሜውን አገኘ። በሻምፒዮናው ማዕከሉ ዛሬ ከተሳተፈባቸው የፍፃሜ ውድድሮች በከፍታ ዝላይ ሴት ኛጆክ ፖል 3ኛ ደረጃን በመያዝ የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ስትሆን በ5000 ሜ ወንድ፣ በ4x100 ሪሌ እና 4x400 ሜ ሪሌ ወንድ/ሴት የዲፕሎማ ተሸላሚ ሆነዋል። በ52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በመዝጊያ ውድድሮች በሴቶችና በወንዶች አሸናፊ ቡድኖች የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት ከአምባሳደር መስፍን ቸርነት ተቀብለዋል። ማዕከሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን፣ መቻል ክለብን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን፣ኦሮሚያ ክልልንና ሲዳማ ክለብን ተከትሎ በሴት 55 ነጥብ በመያዝ 3ኛ ደረጃ ሲይዝ በወንዶች 68 ነጥብ በመያዝ 6ኛደረጃ በድምሩ 123 ነጥብ በአጠቃላይ በሻምፒዮናው የ6ኛ ደረጃ በመያዝ 52ኛውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮናን በድል አጠናቀዋል። በመጨረሻም የማዕከሉ ሁሉም አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የማዕከሉ ሰራተኞች በተመዘገበው ውጤት #እንኳን_ደስ_አላችሁ!! መልዕክት ማዕከሉ አስተላልፏል።

በምርኩዝ ዝለይ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ #አበራ_አለሙ 4:10 ሜትር ከፍታ በመዝለል ለማዕከሉ በ52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ወርቅ አስመዝግቧል።
በምርኩዝ ዝለይ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ #አበራ_አለሙ 4:10 ሜትር ከፍታ በመዝለል ለማዕከሉ በ52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ወርቅ አስመዝግቧል።

ማዕከሉ 5ኛውን የብር ሜዳሊያ በ200 ሜ. ሩጫ ወንድ ተሸላሚ ሆነ። **************//////**************** ግንቦት 12/2015 ዓ.ም 5ኛ ቀኑን ያስቆጠረውና በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ እየተካሄደ የሚገኘው 52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቶክስ ማሰልጠኛ ማዕከል የተለያዩ የውድድር ድሎችን እያስመዘገብ ይገኛል። ዛሬ በተካሄዱት ውድድርም በ200 ሜ መሰናክል ወንድ ንያል ያንግ 21:16 2ኛ ደረጃ፣ በ400 ሜ. መሰ ሴት ባንቺ ተሰማ 59:20 3ኛ ደረጃ፣ በጦር ውርወራ ወንድ ኦኮት ጀምስ 3ኛ ደረጃ፣ በ400 ሜ መሰ ሴት ደራርቱ አኖታ 6ኛ ዲፕሎማ፣ጦር ውርወራ አብዱል ከሪም ኑሪ 7ኛ ደረጃ ዲፕሎማ፣ እና አበበ ለሜቻ 8ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በመቀጠልም ዛሬ በሻምፒዮናው የተለያዩ ግ/ፍጻሜ ውድድር የተካሄዱ ሲሆን የማዕከሉ አትሌቶች በ4X100 ሜ. ሴት/ወንድ ለፍጻሜ አልፈዋል።

የማዕከሉ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች የመቻል ስፖርት ክለብን ጎበኙ። ^^^^^^^^^^^///^^^^^^^^^^ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች ዛሬ 8:00 ሰዓት ጀምሮ አዲስ አበባ የሚገኘውን የመቻል ስፖርት ክለብን ጎበኙ። በጉብኝቱ በስፖርት ክለቡ የሚገኘውን ጅምናዝየም፣ የፎቶ ጋለሪ/Gallery/፣ እና የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን ጎብኝተዋል።

ማዕከሉ 3ኛውን የብር ሜዳሊያ በ110 ሜ. እና በ3000 ሜ. መሰ ተሸላሚ ሆነ። ****************////*************** ግንቦት 11/2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው 52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ዛሬ በነበረው የ3ኛ ቀን በተካሄደው ውድድር ማዕከሉ በወንዶች በ110 ሜ. መሰናክል እና በ3000 ሜ. መሰናክል ወንድ የብር ሜዳሊያ አግኝቷል። በሻምፒዮናውም በማዕከሉ የ110 ሜ. መሰናክል ሯጭ በአትሌት ስንታየሁ የምሻው የብር ሜዳሊያ እና በ3000 ሜ. መሰናክል ሯጭ በአትሌት ሚልኬሳ የብር ሜዳሊያ ተገኝቷል። በመቀጠልም ዛሬ በተካሄደው በሶስተኛው ቀን መርሃ ግብር ማዕከሉን የወከሉት አትሌቶች የተለያየ የማጣሪያ ውድድር በማካሄድ ወደ ሚቀጥለው የግማሽ ፍጻሜ ውድድር ማለፍ ችለዋል። በመጨረሻም ሻምፒዮና ነገም ግንቦት 12/2015 ዓ.ም የሚቀጥል ይሆናል #መልካም_ውጤት_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!!

ግንቦት 9/2015 ዓ.ም ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው 52ኛው የኢትዮዽያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ማዕከሉ በ400ሜ. ሩጫ ወንዶች በዮሀንስ ተፈራ አማካኝነት የብር ሜዳሊያ ሲያገኝ፣ በሻቱ ቶሊና 4ኛ
+6
ግንቦት 9/2015 ዓ.ም ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው 52ኛው የኢትዮዽያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ማዕከሉ በ400ሜ. ሩጫ ወንዶች በዮሀንስ ተፈራ አማካኝነት የብር ሜዳሊያ ሲያገኝ፣ በሻቱ ቶሊና 4ኛ በመውጣት ዲፕሎማ አስገኝታለች። እንዲሁም በ100 ሜ. መሰናክል ሴቶች ሩጫ ደራርቱ አኖታ እና በ110ሜ. መሰናክል ወንዶች ስንታየሁ የሚሻ፣ ጌታሁን ታደሰና አማኑኤል በሀይሉ ፣ በ3000ሜ መሰናክል ሴት ብርቱካን ጋዳሙ፣ በወንዶች ሚልኬሳ ፍቃዱ እና ጀማል ጀዋር ለፍፃሜ አልፈዋል። በነገውም ዕለት የፍፃሜና ሌሎች ውድድሮች የሚካሄዱ ሲሆን ሻምፒዮናው እስከ ግንቦት 13/2015 ዓ.ም የሚቀጥል ይሆናል።

52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኢትዮጵያ ስፖርት እካዳሚ ዛሬ ተጀመረ። ****///*** መጋቢት 8/2015 ዓ.ም ዛሬ ከማለዳው 2፡00 ሰዓት ጀመሮ ሲካሄድ የቆየው 52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የተለያዩ ውድድሮች ሲካሄዱ ቆይተዋል። በሻምፒዮናው የማዕከሉ ሰልጣኞች በተለያዩ ውድድሮች በርዝመት ዝላይ ሴትና፣ በከፍታ ዝላይ ወንድ ውድድር ፍጻሜ ሲያገኙ በ800 ሜ. ወ/ሴ፣ በ100 ሜ. ወንድ/ሴት፣ እና በ400 ሜ. ወ/ሴ የማጣሪያ ውድድር በማካሄድ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ውድድር አልፈዋል። በመቀጠልም ሻምፒዮናው ነገ መጋቢት 9/2015 ዓ.ም የሚቀጥል ይሆናል #መልካም_ውጤት_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!!