Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy
Open in Telegram
414
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Good morning , how could this happen? look https://cutt.ly/ewU7dTdi
ማዕከሉ የ1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ግምገማዊ ውይይት አካሄደ።
***********************///***************
ቀን 23/2015 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል የ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት ዝርዝር ዕቅድ አዘጋጅቶ በየደረጃው ካሉ አመራሮችና ሰራተኞች ጋር ምክክር በማድረግና መግባባት ላይ በመድረስ ወደ ተግባር መግባቱ ይታወሳል። በመሆኑም ከሀምሌ 1/2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2015 ዓ.ም በተደረገው የ1ኛ ሩብ አመት አፈጻጸም በርካታ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል። በነበረው የ1ኛ ሩብ ዓመት ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የ2016 ዓ.ም የአዳዲስ እጩ ሰልጣኞች ምልመላን በተመለከተ የጸጥታ ችግር በሌለባቸው በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ምልመላው መካሄዱና በስኬት መጠናቀቁ እንዲሁም የአዲስና ነባር ሰልጣኞች ቅበላ መካሄዱን በሪፖርቱ ተካቷል።
ትላንት ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም በማዕከሉ እቅድ፣ ክትትል፣ እና ግምገማ ቡድን መሪ በአቶ ሙሳ አብደላ የ2016 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት የክፍሎችን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የአካዳሚው ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ አቶ አንበሳው እንየውን ጨምሮ ሁሉም አመራሮችና የማዕከሉ ሰራተኞች በተገኙበት ሪፖርቱ ቀርቧል።
በዚሁም መድረክ የማዕከሉ ዲን አቶ ጎሳ ሞላ እንደገለጹት የሰልጣኞች የመኝታ፣ የምግብ ፣ የህክምና ፣የመጸዳጃ ቤቶችን ንጽህና ለመጠበቅ የሚያስችል ስራ መሰራቱን እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎችን ዝግጁ የማድረግ ስራ፣የቤተ መጽሃፍትና የሰልጣኞች የኢንተርኔት መጠቀሚያ ቦታ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በመቀጠልም የማዕከሉ ዲን እንደገለጹት የ2016 ዓ.ም የሰልጣኞችን ቅበላ በሚመለከት ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ እንደተገባ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ አንበሳው እንየው የመድረክ ንግግር በማድረግ ተጠናቀቀ።
በማዕከሉ የ2016 በጀት ዓመት እቅድ ተገመገመ።
==========///==========
ጷግሜ 1/2015 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል አመራሮችና ሁሉም ሰራተኞች በተገኙበት የ2015 በጀት አመት አፈጻጸም እና የ2016 በጀት አመት እቅድ ዛሬ ጷግሜ 1/2015 ዓ.ም በማዕከሉ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተገመገመ።
በመድረኩ የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2016 በጀት ዓመት እቅድ በማዕከሉ የእቅድ በጀት ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ ቡድን መሪ በአቶ ሙሳ አብደላ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በመቀጠልም የማዕከሉ ዋና ዲን ኢንስትራክተር ጎሳ ሞላ በንግግራቸው እንደገለጹት በ2015 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባዘጋጃቸው ውድድሮች ላይ ተቋማችን የተሳተፈና እንዲሁም ተሳትፎ ባደረግንባቸው ውድድሮችም ላይ በርካታ ሜዳሊያዎችና ዋንጫም ጭምር የተገኘበትና ውጤታማ የሆንበት ዓመት መሆኑንም ገልጸዋል። በመጨረሻም የማዕከሉ ዲን ኢንስትራክተር ጎሳ ቀጣይ የ2016 በጀት ዓመት መልካም የስኬት ዓመት እንዲሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።
በማዕከሉ ነገን ዛሬ እንትከል በሚል መሪ ቃል የማዕከሉ አመራሮች፣ሰራተኞች እና አሰልጣኞች የችግኝ ተከላ አሻራቸውን አሳረፉ።
*********🌿🌱🌱🌿☘️🍀🌲**********
ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሀገራችን ኢትዮጵያ ነገን ዛሬ እንትከል በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተነሳችበት መርሃ ግብር ላይ የማዕከሉ አመራሮች፣ ሰራተኞች እና አሰልጣኞች አሻራቸውን አሳርፈዋል።
ዛሬ ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ጀምሮ በማዕከሉ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩን የማዕከሉ ዲን አቶ ጎሳ ሞላ ያስጀመሩ ሲሆን በእለቱ ለችግኝ ተከላ በተዘጋጀበት ቦታ ላይ የተለያየ ዝርያ ያላቸው በርከት ያሉ ችግኞችን ሁሉም የማዕከሉ ሰራተኞች ችግኝ ተከላውን አከናውነውል።
በማዕከሉ ከሰኔ 8-10/2015 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው የአመቱ የመዝጊያ ምዘና ውድድር ተጠናቀቀ።
****///******
ሰኔ 10/2015 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሲካሄድ የቆየው ከሰኔ 8-10/2015 ዓ.ም ድረስ የተካሄደው የ2015 ዓ.ም የመዝጊያ ምዘና ውድድር ክለቦች፣ አሰልጣኞችና የተለያዩ የስፖርት ባለሙያዎች በተገኙበት ምዘናው ፍፃሜውን አግኝቷል።
በአመቱ የመዝጊያ ምዘና ውድድር ላይ የተለያዩ ክለቦች መቻል ስፖርት ክለብ፣ ኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አትሌቲክስ ክለብ፣ ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ፣ ፌዴራል ማረሚያ ስፖርት ክለብ፣ አዳማ ከነማ አትሌቲክስ ክለብ ተወካዮችና አሰልጣኞች የተገኙበት የአመቱ መዝጊያ ምዘና ውድድር ዛሬ በድምቀት ፍፃሜውን አገኘ።
በመጨረሻው ቀን የተካሄደው ውድድሮች በ100 ሜ.መሠ ሴት፣ 110 ሜ. ወንድ፣ 200 ሜ. ወ/ሴ፣ 800 ሜ. ወ/ሴ፣ ከፍታ ዝላይ ወ/ሴ እና በምርኩዝ ዝላይ ወ/ሴ የተካሄዱ ሲሆን በአጠቃላይ በ3 ቀን በመዝጊያ ምዘና ውድድሮች ላይ ብዛት ያላቸው አትሌቶች የግል ሰዓታቸውን ያሻሻሉበት ውድድር መሆኑን ከአሰልጣኞች ለማወቅ ችለናል።
በመጨረሻም በማዕከሉ ስቴዲየም ሲካሄድ የቆየው የማዕከሉ የወንዶች U17 እግር ኳስ ቡድን ከአቻው የአዳማው ተስፋ ቡድን ጋር ባካሄዱት የወዳጅነት ጫወታ ማዕከሉ 4ለ1 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ።
በማዕከሉ የተላያዩ የክለብ አሰልጣኞች የተገኙበት የ2015 ዓ.ም የመዝጊያ ምዘና ውድድር ዛሬ ተጀመረ።
****///******
ሰኔ 8/2015 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ዛሬ የተጀመረው ከሰኔ 8-10/2015 ዓ.ም ድረስ የሚካሄደው የ2015 ዓ.ም የመዝጊያ ምዘና ውድድር ክለቦችና የተለያዩ የስፖርት ባለሙያዎች በተገኙበት ዛሬ ተጀምሯል።
ዛሬ በተጀመረው የ2015 ዓ.ም የመዝጊያ ምዘና ውድድር ላይ ክለቦች፣አሰልጣኞች እና የተለያዩ የስፖርት ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በመጀመሪያው ቀን የመዝጊያ ምዘና ውድድር በ400ሜ. መሠ ወ/ሴ፣ በ5000ሜ. ወ/ሴ፣በ1500 ሜ. ወ/ሴ፣ ርዝመት ዝላይ ወ/ሴ፣ እና በዲስከስ ወርወራ ወ/ሴ ውድድሮች ተካሂደዋል።
በመጨረሻም የ2015 ዓ.ም የመዝጊያ ውድድር ነገም ሰኔ 9/2015 ዓ.ም ጠዋት 2:30 ጀምሮ ይቀጥላል።
ማዕከሉ የቢሾፍቱውን የሴቶች እግር ኳስ ቡድን 2ለ1 በሆነ ጎል አሸነፈ።
********************//*****************
ሰኔ 4/2015 ዓ.ም
በቢሾፍቱ ስታዲየም ዛሬ ሰኔ 4/2015 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው ጫወታ የማዕከሉ ሴት እግር ኳስ ቡድን አቻውን የቢሾፍቱ ከተማ ሴቶች እግር ኳስ ቡድንን 2ለ1 በሆነ የጎል ብልጫ አሸነፈ።
በቢሾፍቱ ከተማ ስታዲየም የተካሄደው ጫወታ የመጀመሪያውን ጎል ተቃራኒው ቡድን 1 ጎል በማስቆጠር እየመራ ቢቆይም በ35ተኛው ደቂቃ ላይ ለማዕከሉ የአማካኝ ተጫዋቿ በኮኮቤ ደጀኔ የአቻውን ጎል ከመረብ አሳርፋለች።
በመቀጠልም በአሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ እና በአሰልጣኝ ወርቅነሽ የሚሰለጥነው የማዕከሉ የ1ኛ ዓመት የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ባሳዩት የሁለተኛውን አጋማሽ የኳስ የበላይነት ጫወታ በ72ተኛው ደቂቃ ላይ እየሩስ ገመቹ ባስቆጠረችው የማሸነፊያ ጎል ማዕከሉ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸናፊ ሆኗል።
በመጨረሻም የማዕከሉ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በ2015 ዓ.ም ባካሄዳቸው በሜዳውና ከሜዳ ወጪ ጫወታዎች 9(ዘጠኝ) የአቋም መለኪያ ጫዎታዎችን አካሂዶ አምስት ጫዎታዎችን አሸንፎ 1(አንድ) ጫዎታ አቻ ሲለያይ 3(ሶስት) ጫዎታዎችን ተሸንፎ የአመቱን የ2015 ዓ.ም የአቋም መለኪያ ጫወታዎችን አጠናቋል።
#🅖︎🅞︎🅞︎🅛︎
1. ኮኮቤ ደጀኔ
2. እየሩስ ገመቹ
