en
Feedback
Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy

Athlete Tirunesh Dibaba Atheletics academy

Open in Telegram
414
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በማዕከሉ የ2016 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት (የገና በዓል) በድምቀት ተከበረ *****///***** ታህሳስ 27/2016 ዓ.ም በማዕከሉ በተከበረው በዓሉ ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መል
+9
በማዕከሉ የ2016 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት (የገና በዓል) በድምቀት ተከበረ *****///***** ታህሳስ 27/2016 ዓ.ም በማዕከሉ በተከበረው በዓሉ ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የማዕከሉ ዋና ዲን አቶ ጎሳ ሞላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ሰልጣኞቹ ከቤተሰብ ተለይተው እንደዚህ ዓይነት በዓላትን ሲያሳልፉ ብቸኝነት እንዳይሰማቸው ማዕከሉ ለበዓል የሚሆን አስፈላጊውን ዝግጅት እንዳደረገ ገልፀው በዓሉ የሰላምና የፍቅር የአንድነት እንዲሆን ተመኝተዋል። ማዕከሉ የገና በዓል አስመልክቶ ቀደም ብሎ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን በማድረግ በዓሉን ለማክበር በመመገቢያ አዳራሹ ውስጥ ልዩ ልዩ የበዓሉን ድባብ ለሰልጣኞቹ የሚያስተጋቡ መስተንግዶዎች ቀርበው በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። ሰልጣኞቹ በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት (የገና በዓል) በድምቀት ያከበሩ ሲሆን፤ በበዓሉ ላይ የማዕከሉ ዋና ዲን አቶ ጎሳ ሞላ፣ የት/ት ስልጠና ምርምር ም/ል ዲን ኢንስትራክተር መሀመድ ጃርሶ፣ የፋሲሊቲና መስተንግዶ መሪ ስራ አስፈፃሚ ኢንስትራክተር ገረመው ፈጠነ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በመጨረሻም የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ዋና ዲን አቶ ጎሳ ሞላ ለመላው ኢትዮጵያውያን በተለይም ለማዕከሉ ሰልጣኞች የገና በዓል የደስታ፣ የሠላምና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል

ማዕከሉ በወንዶች እግር ኳስ የአቋም መለኪያ ጫወታ የአሰላ ከተማ U20 እግር ኳስ ክለብን 3:0 #Goal አሸነፈ። ****////****** ቀን 19/2016 ዓ.ም ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም
+8
ማዕከሉ በወንዶች እግር ኳስ የአቋም መለኪያ ጫወታ የአሰላ ከተማ U20 እግር ኳስ ክለብን 3:0 #Goal አሸነፈ። ****////****** ቀን 19/2016 ዓ.ም ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም በአሰላ ከተማ አረንጓዴው ሰታዲየም ጠዋት 4:00 ሰዓት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ወንዶች እግር ኳስ ቡድን አቻውን በኦሮሚያ ሊግ የሚጫወተውን የአሰላ ከተማ እግር ኳስ ክለብን በተለየ የኳስ ቁጥጥር 3ለ0 በሆነ የጎል ልዩነት አሸነፈ። አሰላ ከተማ በሚገኘው አረንጓዴ ስታዲየም የተከናወነው ጫወታ በአማካኝ ተጫዋቹ በአኑዋር ሙካዲስ ጫወታው በተጀመረ በመጀመሪያው አጋማሽ የመጀመሪያውን ጎል ለማዕከሉ ከመረብ አሳርፏል። በመቀጠልም የማዕከሉ U18 ወንዶች እግር ኳስ ቡድን በሁለተኛ አጋማሽ ባደረገው ሰፊ የኳስ ቁጥጥር በአሸናፊ ኤርሚያስ ሁለተኛውን ጎል እና 3ኛውን ጎል በመሀል ተጫዋቹ አቤል ከመረብ በማሳረፍ ማዕከሉ 3ለ0 በሆነ ጎል አሸናፊ ሆኗል። ማዕከሉ በወንዶች እግር ኳስ ከዚህ ቀደም ባካሄደው የአቋም መለኪያ ጫወታው የዴራ ከተማ U18 እግር ኳስ ክለብን 9:1 በሆነ ሰፊ ጎል ማሸነፉ ይታወሳል።

ማዕከሉ በኢትዮጵያ አጭር፣መካከለኛ የ3000 ሜ መሠናክል የርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ7ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ። *****///******* ታህሳስ 7/2016 ዓ.ም ለአምስት ተከታታይ ቀናት ከታህሳስ 3-7/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ስታዲየም ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ አጭር፣መካከለኛ የ3000 ሜ መሠናክል የርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ማዕከሉ በወንዶች 6ኛ እና በሴቶች 8ኛን ደረጃ በያዝ በድምሩ የ7ኛን ደረጃ ይዞ አጠናቀቀ። በሻምፒዮናው ዛሬ በተካሄደው ውድድር በወንዶች ምርኩዝ ዝላይ አበራ አለሙ 3.75 ሜትር በመዝለል የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሲሆን፣ ሙሉቀንና ነስረዲን 3.45 ሜትር በመዝለል 4ኛ እና 6ኛ ደረጃ በመውጣት የዲፕሎማ ተሸላሚ ሆነዋል።በመቀጠልም የማዕከሉ ሰልጣኞች በሴቶች 4X100 7ኛ፣ በወንዶች 4X100 ሜ. 8ኛ እና 4X800 ድብልቅ ሪሌ 8ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። በውድድሩ ላይ ማዕከሉ በወንዶች 42 ሰልጣኞችን እና በሴቶች 38 ሰልጣኞችን በድምሩ 80 ሰልጣኞችን በአጭር፣ መካከለኛ፣ 3000 ሜትር መሠናክል እና በሜዳ ተግባራት ከፍታ ዝላይ፣ ርዝመት ዝላይና በምርኩዝ ዝላይ በሁለቱም ፆታ የተሳተፉ መሆኑን ከስልጠና ክፍል ያገኘነው መረጃ ጠቁሟል። በመጨረሻም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በተካሄደው የኢትዮጵያ አጭር፣መካከለኛ የ3000 ሜ መሠናክል የርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል #2_ወርቅ፣ #2_ብር፣ #1_ነሃስ እና 8 ዲፕሎማዎችንና በርካታ ነጥቦችን በመሰብሰብ በሴቶች በ29 ነጥብ 8ኛ፣ በወንዶች 49 ነጥብ 6ኛ ደረጃን በመያዝ በአጠቃላይ ድምር ማዕከሉ 78 ነጥብ በመሰብሰብ 7ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ። ማዕከሉ ለሁሉም አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች፣ ሰራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል!

ማዕከሉ የመጀመሪያውን #የብር_ሜዳሊያ በዲስከስ ውርወራ ተሸላሚ ሆነ። ****///***** ታህሳስ 4/2016 ዓ.ም ከታህሳስ 3-7/206 ዓ.ም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ
+9
ማዕከሉ የመጀመሪያውን #የብር_ሜዳሊያ በዲስከስ ውርወራ ተሸላሚ ሆነ። ****///***** ታህሳስ 4/2016 ዓ.ም ከታህሳስ 3-7/206 ዓ.ም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ አጭር መካከለኛ፣ 3000 ሜ. መሠ.፣ የርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ላይ ማዕከሉ በተለያዩ የውድድር ተግባራት ላይ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ይገኛል። በሻምፒዮናው ዛሬ ታህሳስ 4/2016 ዓ.ም ማዕከሉ በተሳተፈባቸው ውድድሮች ዲስከስ ውርወራ በሰልጣኝ ቴዎድሮስ ቦጋለ 42:00 ሜትር ርቀት በመወርወር ለማዕከሉ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ ሲያመጣ በአሎሎ ውርወራ 12:86 በመወርወር 6ኛ ዲፕሎማ ፣ በ3000 ሜ.መሠ አትሌት ወሰኔ አሰፋ 6ኛ ዲፕሎማ፣ ሼል ኡማን ርዝመት ዝላይ 6.86 ሜ. 6ኛ ዲፕሎማ፣ ደራርቱ አኖታ 100 ሜ. መሠ. 15'63 ሰዓት 6ኛ ዲፕሎማ፣ ብርቱካን ገዳሙ 8ኛ ነጥብ እና 4x1500ሜ. ድብልቅ ሪሌ 8ኛ ነጥብ አግኝቷል። በመጨረሻም ማዕከሉ በቀጣይ በሚካሄዱ ውድድሮች በተለያዩ የውድድር ተግባራት ለፍፃሜ ውድድር ማለፋቸውን ለማወቅ ችለናል። #መልካም_ውጤቴ_ለተወዳዳሪ_አትሌቶቻችን!

ማዕከሉ በ2016 ዓ.ም ስልጠና ዘመን ሁለተኛውን የሰልጣኞች የውስጥ ምዘና አካሄደ። ****///**** ህዳር 24/2016 ዓ.ም የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ላለፉት 3 ቀናት
+7
ማዕከሉ በ2016 ዓ.ም ስልጠና ዘመን ሁለተኛውን የሰልጣኞች የውስጥ ምዘና አካሄደ። ****///**** ህዳር 24/2016 ዓ.ም የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ላለፉት 3 ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የ2016 ዓ.ም ስልጠና ዘመን ሁለተኛውን የአትሌቶች ውስጥ ምዘና ውድድር ዛሬ ህዳር 24/2016 ዓ.ም አጠናቀቀ። በውስጥ ምዘና ውድድሩም በአትሌቲክስ ስፖርት ዘርፍ የአጭር፣ መካከለኛ እና 3000 ሜ. መሠናክልን ጨምሮ በሜዳ ተግባራት ከፍታ ዝላይ፣ ምርኩዝ ዝላይ ርዝመት ዝላይ እንዲሁም በአሎሎ ውርወራ፣ ዲስከስ ውርወራ እና በጦር ውርወራ ስፖርቶች ለሚሰለጥኑ ሰልጣኞች የውስጥ ምዘናው ተሰቷል። ምዘናውን በተመለከተ የአትሌቶች ት/ት ስልጠና መሪ ስራ አስፈፃሚ ኢንስትራክተር ገስጥ ከበደ እንደገለፁት የምዘናው አስፈላጊነት አትሌቶች ያሉበትን ብቃት ለማወቅና በቀጣይ በኢትዮጵያ የአጭር፣ መካከለኛና 3000 ሜ. መሠናክል፣ የሜዳ ተግባር፣ የርምጃ ውድድር ላይ የሚሳተፉ አትሌቶችን ለመለየት የታሰበ ውድድር ነው ብለዋል። ቀጥለውም አሰልጣኙ ይህ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ሰልጣኞች የብቃት ደረጃቸውን ከመለየቱም ባሻገር 3ኛ እና 4ኛ ዓመት የሆኑ ሰልጣኞች እራሳቸውን ለክለቦች የሚያስተዋውቁበት መድረክም ነው ብለዋል። በመጨረሻም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከታህሳስ 3/2016-7/4/2016 ዓ.ም በሚካሄደው በኢትዮጵያ የአጭር፣ መካከለኛና 3000 ሜ. መሠናክል፣ የሜዳ ተግባር፣ የርምጃ ውድድር ላይ ለሚሳተፈው የማዕከሉ አትሌቶች መልካም ውጤት እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

ማዕከሉ በወንዶች እግር ኳስ የአዳማውን U18 እግር ኳስ ክለብን 2ለ1 በሆነ #Goal አሸነፈ። *****////****** ህዳር 23/2016 ዓ.ም የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል
+9
ማዕከሉ በወንዶች እግር ኳስ የአዳማውን U18 እግር ኳስ ክለብን 2ለ1 በሆነ #Goal አሸነፈ። *****////****** ህዳር 23/2016 ዓ.ም የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ወንዶች U18 እግር ኳስ ቡድን ከአዳማ ከተማ U18 እግር ኳስ ቡድን ጋር ትላንት ህዳር 22/2016 ዓ.ም በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ሲያካሂድ የቆየውን ጫወታ 2ለ1 በሆነ ጎል ልዩነት አሸነፈ። ትላንት በአበበ በቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጫወታ ለማዕከሉ በመጀመሪያው አጋማሽ የመጀመሪያውን ጎል ለማዕከሉ የአማካኝ ተጫዋቹ አኑዋር ሙካዲስ ባስቆጠራት ጎል ማዕከሉን ቀዳሚ አድርጎታል። በማዕከሉ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን አሰልጣኝ, ኢንስትራክተር ደረጄ ታመነ እንደገለፁት ትላንት በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም የተደረገው ጫወታ ጠንካራ ፉክክር የታየበትና ሰልጣኞቹ እየወሰዱ ያለውን ስልጠና በውድድሩ የተገመገሙበትና የሰልጣኞቹን ብቃት ያየንበት ሁኔታ መሆኑን ለቀጣይ ስራዎች ከፍተኛ መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን አሰልጣኙ ገልፀዋል። #Goal ያስቆጠሩ #አኑዋር_ሙካዲስ #ዘላለም_ተመስገን

20ኛው አለም ዓቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በማዕከሉ በደማቅ ስነ-ስርዓት ተከበረ። ***********************////****************** ህዳር 18/2016 ዓ.ም የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል 20ኛውን አለም ዓቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በማዕከሉ መሰብሰቢያ አዳራሽ “ ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፣ በህብረት እንታገለው!” በሚል መሪ ቃል የማዕከሉ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ተከበረ። በዓሉን በንግግር የከፈቱት የማዕከሉ ዋና ዲን አቶ ጎሳ ሞላ እንደገለጹት ሙስና የአንድ ሀገርን ልማት በማደናቀፍና ኢኮኖሚ እንዲወድቅ በማድረግ ዜጎችን ለከፍተኛ ድህነት መራቆት፣ መንገላታት ይዳርጋል እንዲሁም አደገኛ ወንጀልም ነው ብለዋል፣ ሙስና በሁሉም ቦታ የሚከሰትና የተለያየ ባህሪና መገለጫ ያለው በሽታ ነው ብለዋል። ይህንን ብልሹ አሰራር ማስቆም ባንችል ለመቀነስ መታገል የሁሉም ዜጋ ሀላፊነት ነው ብለዋል የማዕከሉ ዋና ዲን። በመቀጠልም የዓለም የፀረ ሙስና ቀንን ለማክበር በተዘጋጀው የውይይት ሰነድ በማዕከሉ የስነምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አረፋይኔ ደረሰ ለታዳሚው በማቅረብ በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት በማድረግ ዝግጅቱ ተጠናቀቀ።