en
Feedback
ISLAMIC POST

ISLAMIC POST

Open in Telegram

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
203
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+530 days
Posts Archive
አራት ነገሮች ሴቶችን ያጠፋሉ።       የትዳር ህይወትን ያበላሻሉ ። በዱንያና በአኼራ ደስታን ያርቃሉ። 4──────⊱◈◈◈⊰────── 1#ምላስ #ማስረዘም.   የሴት ልጅ ውበት ዝምታው አደቧ ሀያእዋ ነው። በተለይ ባል ላይ ከፍ ከፍ ማለት እኔ አውቃለሁ ማለት የትዳርንም የዱንያንም የአኼራንም ህይወት ያበላሻል።እንዳውም ይሄ ከምእራባውያን የመጣ የፌሚኒስት ሴቶች ባህሪ ነው። ──────⊱◈◈◈⊰────── 2#ስሞታ #ማብዛት ለትዳር ከማይበጁ ሴቶች ባህሪ ውስጥ──────⊱◈◈◈⊰────── አንዱ ባህሪ ስሞታ ማብዛት ምስጋና ቢስ መሆን በትልቅ በትንሹ መጨቃጨቅ ነው። ስግብግብ ሁሉ አማረሽ ያየችው ሁሉ የሚያምራት የምትፈልገውን ካላገኘች ወቀሳዋ ለሽማግሌ የሚያስቸግር ሴት ናት። ──────⊱◈◈◈⊰────── 3#ውለታን #መካድ ስንት አመት የተንክባከባትን ባልዋን አንድ ቀን ጥፋት ስታይ ምን አደረክልኝ ? ከአንተ ኸይር አይቸ አላውቅም የምትል ሴት ቤቷን ማፍረስ የፈለገች ሴት ናት። አኼራም ላይ እሳት የመግቢያ ሰበብ እንደሆነም ተንግሯል። ──────⊱◈◈◈⊰────── 4  ከአጋሯ ውጭ ለሆኑ ወንዶች የምትገላለጥ እዩኝ እዩኝ የምትል  እና ወጣ ገባ የምታበዛ ያለባሏ ፍቃድ የምትጓዝ ውጭ ላይ ውበትን የምታሳይ እቤት ውስጥ ዝርክርክ የሆነች ሴት ነብዩ እንዳሉት አኺር ዘመን ላይ የሚመጡ መጥፎ ሴቶች እንደሆኑ ተናግረዋል፡        ──────⊱◈◈◈⊰────── ሴቶች ሆይ  ይሄን እና ሌሎች መጥፎ ባህሪያቶች ተጠንቀቁ?!

^ቲክቶክ^ كم رأينا من امرأة كانت تستحي، فلما جاء "تيك توك" نزع عنها حياءها، فبدأت تكثر الكلام مع الرجال، ويا له من ضرر عظيم! ➮ ስንትና ስንት ሴቶችን አየን ቀድሞ በእፍረት የታወቁ፣ ነገር ግን "ቲክቶክ" በመጣ ጊዜ እፍረታቸውን የገፈፋቸው፤ ከወንዶችም ጋር ማውራትና መቀለድ ያበዙ፤ ይህም እንዴት ያለ ትልቅ ጉዳት ነው! ◈እናማ እህቶቼ ይሄን 'ቲክቶክ' ተጠንቀቁ! አይ እኔ ጥሩ ነገር ነው ምሰራበት ልንል እንችላለን ግን ብዙዎቹ በዚህ ምክንያት ገብተው ነው ገደል የገቡት! ◉ ወሏህ ስንት ሰው አይየን በቲክቶክ ምክንያት ከሱና የወረደን ስንት እህቶችን አየን በዲን ስም ወተው ወንድ እራሱ ለመናገር የሚያፍረውን ቃል ስናገሩ ያውም ወንድና ሴቱ ቤተሰበሰበበት 'ሱብሀናሏህ' ስንቱን አውርተን እንችላለን! 🔖ቲክቶክ የማትጠቀሙ አሏህን አመስግኑ እና ፅናትም እንድሰጣችሁ ለምኑት፣የሚትጠቀሙ ደግሞ በቻላችሁት ያክል ለመውጣት ጥረት አድርጉ አሏህም ከዚህ ቆሻሻ እንድያወጣችሁ ለምኑት? ⚠️ የቲክቶክ አደጋዎች:- ⓵ከቁርአን ማራቅ ⓶ከዝክርና ከሶላት ማራቅ ⓷የልብ ጠንካራነትና እምነት መዳከም ⓸የጊዜ መባከን ⓹ሪያእ (ለሰዎች መታየት መውደድ) ⓺የሴቶችና የወንዶች አውራ ሰውነትን መመልከት ⓻ወንጀል ማስፋፋት ⓼ሐሜትና ሰዎችን ፣ሙዝቃና ዘፈን፣መንዙማና ነሽዳ የመሳሰሉት መላመድ የመሳሰሉ አደጋዎች አሉት ይሄን ለመጥቀስ ያክል ነው ተቆጥሮ አያልቅም። 🤲አሏህ ሁሏችንንም ከቲክቶክ ያርቀን مع السلامة ✍️ወንድማችሁ አቡ ሱፍያን (ኢብኑ አብደሏህ) 📲 ቻናል፦ t.me/nesiheti_linisa

ብዙ ጊዜ በጉጉት ከምንጠብቃቸው ነገሮች ይልቅ በድንገት የምናገኛቸው ነገሮች ውብ ናቸው🌸 አላህዬ በድንገት ያስደስተን🤲🤲🌺የተገኘ

በማንኛውም ነገር አስመሳይ ብትሆን እንኳ በዲንህ ግን አስመሳይ አትሁን አታስመስል። እውነተኛ ሁን/ኚ!

👉 ጓደኝነትህን ከፍ ያለ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ጋር አድርግ፡፡ ካንተ የተሻሉ ሰዎችጋ የምትውል ከሆነ እንደ እነሱ መሆን ትጀምራለህ፡፡ ተራ የሆነ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ጋር ስትሆን ተቃራኒውን ትሆናለህ፡፡ 👉 እድገትህ ያለው ከፊትህ እንጂ ከኋላህ (ካለፈው) አይደለም፣ የፊትህ ላይ አተኩር፡፡ 👉 ከምንም በላይ ራስህን አሳድግ፡፡ በፅሁፍም ሆነ በንግግር ሃሳብህን በሚገባ ለመግለፅ ተማር፣ ስልጠና ውሰድ፡፡ ይሄ ብቻ ተፈላጊነትህን በ50% ይጨምራል፡፡ 👉 በተቻለ መጠን ውስጥህ መሆን የሚፈልገውን ሁን፤ የሚያስደስትህን ስራ፡፡  👉 ትሁት ሁን፡፡ ትሁት ሰው እኔ ብቻ ነኝ አዋቂ አይልም፡፡ ከሌሎች ይማራል፤ ያለማቀረጥ ያነባል፣ ሎሎችን ይሰማል፣ ይማራል፡፡ 👉አካልህን እና አእምሮህን በሚገባ ተንከባከብ፡፡ በምድር ላይ ስትኖር የሚኖርህ አንድ አካል እና አንድ አእምሮ ስለሆነ በትጋት ጠብቀው ተንከባከበው፡፡

ምንም ያህል ያለንበት ሁኔታ ከባድ ቢሆንም አሁንም አልሀምዱሊለላህ❤️‍🩹 ♻️

ትልቁ ኪሳራ ማለት...ጀናዛው ላይ ሊሰገድበት ብቻ ተብሎ መስጊድ የገባ ሰው ነው። ♻️ልትቀበር ተብላ በከፈን ጊዜ ብቻ ሒጃቧን ፀጉሯን የሸፈነ ሴት ናት። ☝️ጌታዬ ሆይ በዲንህ ላይ አጽናን፣መልካም መመለስን ወዳንተ መልሰን

«أَلَمْ يَعْلَم بِأَنَّ اللَّهَ يَرَىٰ «አላህ የሚያየው መሆኑን አያውቅምን?!» (ሱረቱ አል-ዐለቅ፡ 14)

ወንጀል በውስጥህ ተደብቆ አይቀርም፤ የሰራኸው ወንጀል ፊትህ ላይ ይመሰክርብሃል! ♻️የአላህን ትዕዛዝ መጣስና በፈጸምከው ወንጀል መዘፈቅ ገና በወጣትነትህ የፊትን ኑር ይገፍፈዋል። 🫧ውበትህን አጥፍቶ፣ ፊትህን አጨልሞ፣ በቁምህ እንደበሰበሰና እንደጠወለገ አስፈሪ ሬሳ ያደርገዋል። 💦ከአላህ ቅጣትና ቁጣ በፊት፣ ፊትህ ላይ የሚታየው የወንጀልህ ክፋትና ውርደት ለሰው ሁሉ ማሳፈሪያ ይሆንብሃል!»

መሀርታን የሚያስጠይቅ ወንጀል የለብኝም ብለህ ካሰብክ...ለዚህ ሀሳብህ መሀርታን ጠይቅ!

ፕሮፋይላችንና ስቶሪያችን ስታይ በጣም ደስ የሚሉ አላህን ይፈራል አላህን ትፈራለች የሚያስብሉ ናቸው። ነገር ግን በውስጥ የምንሰራው ስራ እኛ ይቅርና ሸይጣን እንኳን የሚያፍርብን የሆነ ብዙ አይነት ወንጀሎችን ስንዳፈር እንታያለን። ፕሮፋይላችን ሌላ እኛ ሌላ አላህን እንፍራ። በፕሮፋይላችን እንደ አማርነው ሁላ በውስጥ ብቻችንንም ስንሆን አላህን እንፍራ። ደግሞ ሰውን በፕሮፋይሉና በኢስቶሪ አንመዝን👌

የጁመዓ ቀን ሱናወች 🧼 ገላን መታጠብ : ንጹህ ልብስ መልበስ እና ሽቶ መጠቀም። ​📖 ሱረቱል ካህፍን መቅራት: በዕለቱ ወይም በሌሊቱ አጠናቆ መቅራት። ​✨ ሶለዋት ማብዛት: በነቢዩ (ﷺ) ላይ ሶለ
የጁመዓ ቀን ሱናወች
🧼 ገላን መታጠብ : ንጹህ ልብስ መልበስ እና ሽቶ መጠቀም። ​📖 ሱረቱል ካህፍን መቅራት: በዕለቱ ወይም በሌሊቱ አጠናቆ መቅራት። ​✨ ሶለዋት ማብዛት: በነቢዩ (ﷺ) ላይ ሶለዋት ማውረድ። ​🕌 ወደ መስጊድ በማለዳ መሄድ: ኹጥባ ሳይጀመር በጊዜ መገኘት። ​👂 ኹጥባን በፅጥታ ማዳመጥ: ኢማሙ ሲናገር ጭጭ ብሎ ማዳመጥ። ​🤲 ዱዓ ማብዛት: በተለይ ከዐስር በኋላ እስከ መግሪብ ባለው ጊዜ። #አፍሪካ_አካዳሚ #አራተኛ_ዙር

🔸قال العلّامة ابن عثيمين - رحمه الله:- "وكلما قويت الأذية قرب النصر ، وليس النصر مختصاً بأن يُنْصَرَ الإنسان في حياته ، ويرى أثر دعوته قد تحقق ، بل النصر يكون ولو بعد موته بأن يجعل الله في قلوب الخلق قبولاً لما دعا إليه ، وأخذاً به وتمسكاً به ، فإن هذا يعتبر نصراً لهذا الداعية وإن كان ميتاً " . ​🔸 ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ይላሉ፦ ​«መከራና እንግልት በበረታ ቁጥር ነስር (የአላህ እርዳታ) ይበልጥ ይጠጋል። ነስር ማለት አንድ ሰው በህይወት እያለ ብቻ የሚረዳበትና የዳዕዋውን ውጤት በዓይኑ አይቶ የሚያረጋግጥበት ብቻ አይደለም። ይልቁንም ነስር ማለት እርሱ ከሞተ በኋላ እንኳ ሊሆን ይችላል። ይኸውም አላህ በሰዎች ልብ ውስጥ እርሱ ጥሪ ላደረገበት እውነት ተቀባይነትን በመስጠት ሰዎችም ያንን ይዘውና አጥብቀው እንዲከተሉት በማድረግ ነው። በዚህም ያ ዳዒ ሞቶ እንኳ ቢሆን እርሱ ታላቅ ድል እንደተቀዳጀ ይቆጠራል።» ​

ታች ከተጠቀሱት ውስጥ መውሊድን ያከበረው ማን ነው
Anonymous voting

ታች ከተጠቀሱት ውስጥ መውሊድን ያከበረው ማን ነው
Anonymous voting

🔷ከስሜቱ ጋር ሲገጥም ሐቅን ከሚከተል ፣ ከስሜቱ ጋር ሲጋጭ ሐቅን ከሚቃረን ሰው  አትሁን ኡመር ኢብን ዓብዱልዓዚ እንዲህ ብሏል :- "ከስሜቱ ጋር ሲገጥም ሐቅን ከሚከተል ፣ ስሜቱ ሐቅን ሲጋጭ ከሚቃረን ሰው  አትሁን። ያን ጊዜ አንተ በተከተልከው ሐቅ አትመነዳም ፤ ሐቅን በመቃረንህ ደግሞ ትቀጣለህ። ኢብን ተይሚያ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናገረ :- "ነገሩ እርሱ እንደተናገረው ነው። ምክንያቱም በሁለቱም ቦታዎች አላማው ስሜቱን መከተል እንጅ ለአሏህ ብሎ አይደለምና። - ባሰራጨሃቸው ፋይዳዎች አላህ ይጠይቅሃል። ዝንባሌህን ለመርዳት ወይም ነፍስህን ለመበቀል ነው ያሰራጨኸው (ወይስ ለሌላ አላማ)? ብሎ ይጠይቅሃል። ሁሉም ሰው ራሱን የመመርመር ግዴታ አለበት።  "እገሌ ኢላማ ያደርገኛል" ወይም "እርሱ ይፈልገኛል" አትበል። አዎ ኢላማ ያደርግሃል ፣ ሙስሊም አይደለህም እንዴ? ይህ እኮ አንተ በቁርአንና በሐዲስ የተነገረህ ነው። ድርጊቱ በአንተ ላይ ካለ ወደ አሏህ ተጸጽተህ ተመለስ። ካልሆነ ደግሞ  አላህን አመስግን - ምክንያቱም ዲን ምክክር ነውና። ቀደምት ሙስሊሞች "እኔን ፈልጎበት ነበር ፤ እኔን ማለቱ አልነበረም" የሚለውን ፍልስፍና አያውቁትም ነበር - ምክንያቱም ሐቅ ከሆነ ከህጻናትም ይሁን ከሽማግሌ ይቀበሉ ነበርና። የአሏህ ቁርአን ስለጣኦት አምላኪዎች ፣ ስለከሐዲዎች እና ስለወንጀለኞች የሚገልጹ ታሪኮችን ይዟል። እነርሱ በወደቁበት እንዳንወድቅ ፣ መጽሐፉን  እንድናሰላስል አሏህ አዞናል። - ከሰለፎች የቁርአን አንቀጽ ወይም ሐዲስ ወይም የሰለፎች ንግግር ሲነገረው "እኔን አላማ አድርጎ ነው" ፤ "እኔን ፈልጎበት ነው" የሚል አንድም  አላገኘንም። አዎ አንተን ይመለከትሃል። ደካማና ስሜትህን ለመከተል የተጋለጥህ አይደለህምን? -በሰለፎችና በእኛ መካከል ያሉ ልዩነቶች፣ ሰለፎች  ወደነፍሳቸው ይመለሳሉ ፣ ራሳቸውን ይገመግማሉ  ፣ ይወቅሳሉ።   እርሷንም  ይንቃሉ። እኛ ግን ወደሌላ አካል እንቀስራለን። ይህንን በሽታ ራቁና ከማንም በፊት እነዚህን ፋይዳዎች ተጠቀሙ። ነፍሳችሁን ፈትሹ ፣ ሂሳብ አድርጉ። እርሷንም  ገስጿት። አፊያን ከአሏህ እንለምናለን። من شرح صحيح البخاري

📌يقول سرير الجنازة لبني آدم: "انظر إلي بعقلك *** أنا المهيأ لنقلك أنا سرير المنايا *** كم سار مثلي بمثلك" የጀናዛ አልጋ ለሰው ልጆች እንዲህ ይላል انظر إلي بعقلك — በአእምሮህ አስተውለኝ፣ በጥልቀት አስብብኝ። أنا المهيأ لنقلك — እኔ ከዚህ ዓለም ወደ መቃብር ለመውሰድህ የተዘጋጀሁ ነኝ። أنا سرير المنايا — እኔ የሙታን መሸከሚያ ነኝ። كم سار مثلي بمثلك — እንደ አንተ ያሉ ብዙ ሰዎች በእኔ ተሸክመው ወደ መቃብር ሄደዋል ሰው በዱንያ ምንም ያህል ቢኖር መጨረሻው ሞት ነው ስለዚህ ለአኺራ መዘጋጀት ይገባል።

ሁጥባ_መርካቶ_ባዩሽ_መስጂድ_በሸይህ_አቡድ_ሰላም.m4a25.20 MB

صلوا على النبي؟ اللهم صل وسلم وبارك على نبينا محمد