EECMY - School (online class)
Open in Telegram
This channel is created with the thought of teaching students by supplying important files. Please pay attention.
Show more487
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+230 days
Posts Archive
በተደረገው ውይይት ላይ
1. ተማሪዎች በአቅማቸው ውጤታቸውን ለማሻሻል ግብ አሥቀምጠው መማር እንዳለባቸው
2, ትምሕርት ቤቱ ባሥቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በግልና በቡድን፡በቤትና በትምህርት ቤት ጥናታቸውን እንዲያጠናክሩ
3. በስነምግባራቸውም ምሥጉን እንዲሆኑና በተለይም ተዘጋጅቶላቸው የቀረበውን የሥነምግባር መመሪያ እንዲያከብሩ፡ ማንኛውም የስነሥርአት ጥሠት ከክፍል ሐላፊ መምሕር ጀምሮ እስከዲሥፕሊን ኮሚቴ ጉዳያቸው እየታየ የእርምት እርምጃ እንደሚወሠድ ፡የተማሪዎች ተወካዮችም ተግተው ሐላፊነታቸውን በፓርላማቸው በኩል እንዲወጡ ፡
4 የ6ኛም ሆነ የ8ኛ ክፍል ሑሉም ተማሪዎች ከሠኞ እስከ ሐሙሥ ከመደበኛ ት/ት ሠአት ውጪ ትምሕርት ቤቱ በመጠነኛ ክፍያ እየሠጠ ባለው ማጠናከሪያ ትምሕርት ላይ በንቃት እንዲሣተፉ ሥምምነት ላይ ከተደረሠና ተማሪዎችም በነፃነት ሐሣባቸውን ከገለፁ በሇላ ሥብሰባው ከቀኑ10:45 ተጠናቋል፡፡
ት/ቤቱ
በእንጦጦ ወንጌላዊት አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በውጤትና በሥነ-ምግባር መሻሻል ዙሪያ በ6/3/2017 ዓ.ም.ውይይት መካሄዱን የሚየሳይ ፎቶግራፍ መግለጫ
የተከበራችሑ የ6ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ወላጆች/አሣዳጊዎች በሙሉ
ነገ አርብ ሕዳር6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:45 እሥከ 10:30 ሠአት ከ6ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር በፈተና ዝግጅት፡ በውጤትና ሥነምግባር ማሻሻል፡ በአጠናን ዘዴ ላይ ውይይት የምናደርግ መሆኑን ከወዲሑ በአክብሮት እናሣውቃለን፡፡
ት/ቤቱ
እንኳን ደሥአለን እንኳን ደሥአላችሑ
የ19ኛውን ብሔር ብሔረሠቦች አከባበር ምክንያት በማድረግ በወረዳ ደረጃ በተደረገው የጥያቄና መልሥ ውድድር ላይ ተማሪያችን ተማሪ ሢፈን ጥላሑን ትምሕርት ቤታችንን ወክላ በመወዳደር አንደኛ ደረጃ በመውጣት የምሥክር ወረቀት ተበርክቶላታል፡፡
ት/ቤቱ
በእንጦጦ ወንጌላዊት ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረው የብሔር ብሔረሰበች ሕዝቦች ምክንያት በማድረግ በተማሪዎች መካከል የጥያቄና መልስ ተካሄደ።
የተከበራችሑ ወላጆች /አሣዳጊዎች
የጥቅምት ወር ክፍያ ያልከፈላችሑ ወላጆች /አሣዳጊዎች በዚሕ ሣምንት ከፍላችሑ እንድታጠናቅቁ እያሣሠብን ክፍያ ያልከፈሉ ተማሪዎችን ለማሥተናገድ መቸገራችንን እንገልፃለን፡፡ በተጨማሪ የተማሪ ውጤት የሚመጣው ተማሪዎች ጠንክረው ሢያጠኑና በተለያየ መንገድ ሢደገፉ ሥለሆነ በስብሠባ ላይ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የ6ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በማጠናከሪያ ጥናት ፕሮግራም ከሰኞ እስከ ሐሙሥ ድረስ መሣተፋቸውን እንድትከታተሉልን እናሣሥባለን፡፡
ት/ቤት
የተከበራችሑ ወላጆች/አሣዳጊዎች
በየሣምንቱ ሠኞ ሠኞ ከቅድመ አንደኛ እስከ 8ኛ ክፍል የተማሪዎች የግል ንፅሕና አጠባበቅ ቁጥጥር ይደረጋል፡፡ ሥለሆነም በእለቱ
- የወንድ ተማሪዎቻችን ፀጉር በአግባቡ ተቆርጦ፡ የሤትተማሪዎች ፀጉርም በአግባቡ ተሠርቶ
- ሑሉም ተማሪዎች ንፁሕ የትምሕርት ቤት የደንብ ልብስ/uniform / ለብሰው
- የሐሉም ተማሪዎች ጥፍር በአግባቡ ተቆርጦ ወደ ትምሕርት ቤት እንዲመጡ ያድርጉልን፡፡
በተጨማሪ ሠኞ ሠኞ በትምህርት ቤታችን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ንግግር መለማመጃ ቀን ሥለሆነ ተማሪዎቻችን እቤትም እንዲለማመዱ ቢያበረታቷቸው፡፡
ት/ቤቱ
የጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ወርሐዊ የትምህርት ክፍያ ያላጠናቀቃችሑ ወላጆች እንድታጠናቅቁ እየጠየቅና በወቅቱ ክፍያ ያልተፈፀመላቸውን ተማሪዎች የማናሥተናግድ መሆኑን ከወዲሑ በአክብሮት እንገልፃለን፡፡
ት/ቤቱ
የጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ወርሐዊ የትምህርት ክፍያ ያላጠናቀቃችሑ ወላጆች እንድታጠናቅቁ እየጠየቅና በወቅቱ ክፍያ ያልተፈፀመላቸውን ተማሪዎች የማናሥተናግድ መሆኑን ከወዲሑ በአክብሮት እንገልፃለን፡፡
ት/ቤቱ
ቅዳሜ ጥቅምት 16/2017ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሠአት ጀምሮ ከቅድመ አንደኛ፡አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ተማሪዎች ወላጆች/አሣዳጊዎች ጋር ሠፋ ያለ ውይይት ተደርጓል በስብሰባው ላይም
1. የ6ኛ ና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ዉጤት ሥለማሻሻልና ተማሪዎች በማጠናከሪያ ትምሕርት ላይ እንዲሣተፉና እንዲደገፉ
2.የእንግሊዝኛ እና ሒሳብ ት/ት ውጤት ማሻሻል ላይ
3. የ ተማሪዎች ስነ ምግባር
4.በ2017 ዓ.ም የት/ቤት ራዕይና መሪ እቅድ የጋራ ማድረግ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገ ፡ ውሳኔዎች ከተላለፉና የቅድመ አንደኛ ደረጃ የወተመ ኮሚቴ ከተመረጠ በሇላ ሥብሰባው ከቀኑ 5:00 ሠአት ተጠናቋል፡፡በስብሰባው ላይ ጊዜያችሑን መሥዋዕት አድርጋችሑየተገኛችሑ ወላጆችን በሙሉ በትምህርት ቤቱ ማሕበረሰብ ሥም እናመሠግናለን፡፡
ት/ቤቱ
ቅዳሜ ጥቅምት 16/2017ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሠአት ጀምሮ ከቅድመ አንደኛ፡አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ተማሪዎች ወላጆች/አሣዳጊዎች ጋር ሠፋ ያለ ውይይት ተደርጓል በስብሰባው ላይም
1. የ6ኛ ና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ዉጤት ሥለማሻሻልና ተማሪዎች በማጠናከሪያ ትምሕርት ላይ እንዲሣተፉና እንዲደገፉ
2.የእንግሊዝኛ እና ሒሳብ ት/ት ውጤት ማሻሻል ላይ
3. የ ተማሪዎች ስነ ምግባር
4.በ2017 ዓ.ም የት/ቤት ራዕይና መሪ እቅድ የጋራ ማድረግ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገ ፡ ውሳኔዎች ከተላለፉና የቅድመ አንደኛ ደረጃ የወተመ ኮሚቴ ከተመረጠ በሇላ ሥብሰባው ከቀኑ 5:00 ሠአት ተጠናቋል፡፡በስብሰባው ላይ ጊዜያችሑን መሥዋዕት አድርጋችሑየተገኛችሑ ወላጆችን በሙሉ በትምህርት ቤቱ ማሕበረሰብ ሥም እናመሠግናለን፡፡
ት/ቤቱ
