en
Feedback
SWA Lafto KG to Grade 4 division

SWA Lafto KG to Grade 4 division

Open in Telegram

Educational channel

Show more
951
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አዲሱን channel ይቀላቀላሉ

የተከበራችሁ የሳዌአ ቤተሰቦች:-በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን የሚሆን ደረቅ ምግቦችን ሩዝ፣ፓስታ፣ማካሮኒ፣ፓስቲኒ ፍርኖ ዱቄት፣ስኳር.....ዘይት፣ የንፅህና መጠበቂያ ዳይፐር፣ሞዴስ፣ላርጎ፣ሳሙና (ደረቅ ወይም ፈሳሽ)፣ሶፍት....በመላክ የተለመደ ትብብራችሁን እንድታደርጉ በታላቅ አክብሮት እየጠየቅን የመጨረሻ የማስረከቢያ ቀን እስከ ረቡዕ፣ህዳር 8፣2014 ብቻ የተራዘመ መሆኑን እንገልፃለን።ከዚህ ቀን በሗላ የሚመጡትን ግን መልሰን ወደቤት የምንልክ ይሆናል። የመዋዕለ ሕፃናት አስተዳደር

የተከበራችሁ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች:-ከሰኞ ጀምሮ የፈረቃ ለውጥ ስለተደረገ ልጆቻችሁን በተቀየረው ፈረቃ ብቻ እንድትልኩ በድጋሚ እናስ ታውሳለን። የመዋዕለ ሕጻናት አስተዳደር።

Amen !RIP kin ena melkam nebersh tewdajwa ehitachen amlak nefsishin begenet yanurlin!

Nebes yemar ehetachen

school rules for kindergarten students

ታህሳስ 8.docx0.95 KB

ቀን 8 / 4 / 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ4ኛ ዙር ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎችን የአዲስ
ቀን 8 / 4 / 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ4ኛ ዙር ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ይፋ አደረገ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ደሙ በዛሬዉ እለት በሰጡት መግለጫ እንዳሳወቁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን እየተከላከሉ የገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራዉን በከተማዉ ለማስጀመር በተቀመጠዉ ውሳኔ መሰረት ቀደም ሲል ህዳር 16 የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቸ በክለሳ ትምህርት ውስጥ እንዳልፉ ፣ ህዳር 28 በግል ትምህርት ቤቶች ከ1 ክፍል ጀምሮ እና በመንግሰት ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በሶስት ዙሮች መጀመሩን ገልጸዉ ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ በ4ኛ ዙር ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎች በግል ትምህርት ቤቶች የቅድመ መጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች እና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች መሆናቸዉን ሀላፊዉ አሳውቀዋል፡፡ ሀላፊዉ በመግለጫቸዉ አክለዉም ህጻናት ተማሪዎችን ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማሩ ስራ እያመጣን በመሆኑ የተዘጋጀዉን የኮቪድ ፕሮቶኮልን በአግባቡ መተግበር እንዲቻል የትምህርት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን ሚና እንዲወጡ ጥራቸዉን አቅርበዋል፡፡ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና የትዊተር ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

የመዋእለ ሕጻናት አስተዳደር

የተማሪዎች ደንብ ደብዳቤ.docx0.51 KB

የተከበራችሁ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች :- 1) የመጨረሻውን የተማሪዎች የክፍል ድልድልና ፈረቃ አውጥተናል።ስለዚህ በሚገባ በማየት ትምህርት ሲጀመር በፈረቃችሁ ብቻ ልጆቻችሁን እንድትልኩ እናሳስባለን ። ከዚህ በሗላ ምንም የፈረቃ ማሻሻያ ጥያቄዎችን የማናስተናግድ መሆኑንም እናሳውቃለን። 2) የሚከተለውን መመሪያ በሚገባ አንብባችሁ እንድትተገብሯቸውም በትህትና እንጠይቃለን። 3)መጽሐፍ ያልወሰዳችሁ ወላጆች እንድትወስዱ። 4) የህዳር ወር ክፍያ ያልከፈላችሁ ወላጆች እንድትከፍሉ እንጠይቃለን ።

ውድ ተማሪዎች ከሰኞ ታህሳስ 5/2013 ጀምሮ ከትምህርት ቤት መውጫ ስዓት ከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት(9:00) መሆኑን እናሳውቃለን ።

ህዳር 19 ቀን 2013 ዓ.ም ለተከበራችሁ የሳዌአ የተማሪዎቻችን ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች ከሰኞ ህዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት እንደሚጀመር ከት\ት ጽ\ቤት መልዕክት ደርሶናል። በዚሁ መሰረት እናንተም ተገቢውን የኮቪድ-19 ጥንቃቄን በማድረግና ልጆቻችሁ በተመደቡበት የት\ት ቀናት መላክ እንዲያስችላችሁ ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ በማክበር እናሳስባለን፡፡