2 324
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 324
ለ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ተማሪዎች
ማክሰኞ መስከረም 24/2015 ዓ.ም ኦረንቴሽን ስለሚሰጣችሁ ጠዋት 3፡00 ሰዓት ላይ በት/ቤት ቤተ-መጻህፍ እንድትገኙ አሳስባለሁ፡፡
2 324
ማስታወሻ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች
የሚከተሉትን ነጥቦች በአግባቡ አንብባችሁ እንድትዘጋጁ
ሀ. ለፈተና ወደ ዩንቨርሲቲ መግቢያ ጊዜ ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከመስከረም 26
እስከ 28 ነው፡፡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ጥቅምት 5 ተብሏል ቢሆንም ምንአልባት
አንድላይ ግቡ የሚባል ከሆነ ድንገት እንዳይሆንባችሁ ከወዲሁ እናንተም እንድትዘጋጁ፡፡
ለ. ለፈተና ወደ ዩንቨርሲቲ ስትገቡ የት/ቤት መታወቂያ፣ የፈተና መታወቂያ ፣ ሙሉ
የተስተካከለ የደንብ ልብስ፣ አንሶላና ትራስ፣ ቅያሪ ልብስ፣ ደረቅ ምግቦች መያዛችሁን
አረጋግጡ፡፡
ሐ. የሚከለከሉ ነገሮች፡
ማንኛውም ዓይነት ኤሌክትሮኒክስ ሰዓትን ጨምሮ
የተንጨበረረ ጸጉር ለወንዶችና ባዕድ ጸጉር(ዊግ) ለሴቶች
ያልተሟላ የደንብ ልብስ
መ. የፈተናችሁ ቦታ እዚሁ ሀዋሳ ሲሆን የትኛው ካምፓስ የሚለው ወደፊት የሚገለጽ
ይሆናል፡፡
የምትፈልጉትን ለመሆን የማትፈልጉትንም ጭምር እያደረጋችሁ ሁለት ነገሮች ላይ ትጉ በስራና በጸሎት፡ ስራችሁ ለፈተና ብቁ ያደርጋችኋል ጸሎታችሁ በጥበቃ ሙሉ ያደርጋችኋል፡፡
2 324
ማስታወቂያ
ለ2014 የት/ት ዘመን 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
- ከዚህ በፊት በተገለጸላችሁ መሰረት ከመስከረም 9-11 ወጥ ሞዴል ፈተና በከተማ አስተዳደሩ ይሰጣል
- ይህንን ሞዴል ፈተና ያዘጋጁት ልምድ ያላቸው ለረጅም ጊዜ ጥያቄ በማዘጋጀት የሚታወቁ ባለሙያዎች ስለሆኑ ለናንተ ዝግጅት በጣም ጠቃሚ ነው
- የፈተናው ፕሮግራም ሰኞ፡ ጠዋት እንግሊዘኛ ከሰዓት ሂሳብ ማክሰኞ፡ ጠዋት ፊዚክስ ወይም ጂኦግራፊ ከሰዓት ኬሚስትሪ ወይም ታሪከ ረቡዕ ፡ ጠዋት ቺቪክ ከሰዓት ባዮሎጂ
- መግቢያ ሰዓት ጠዋት፡ 2፡00 ከሰዓት 7፡30
- ስትመጡ የተስተካከለ ጸጉር፣ ንጹህ የሆነ የደንብ ልብስና ሌሎች ለፈተና አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን መያዛችሁን አረጋግጡ
- የማጠናከሪያ ክፍያ መክፈላችሁን አረጋግጡ
2 324
ማስታወቂያ
የ2015 የት/ት ዘመን ት/ት የሚጀምረው ለሁሉም የክፍል ደረጃዎች ከ9ኛ ክፍል በስተቀር መስከረም 09/2015 መሆኑን አውቃችሁ ሁላችሁም የደንብ ልብሳችሁን በስርዓት ለብሳችሁ፣ ጸጉራችሁን በአግባቡ ተሰርታችሁ በተጠቀሰው ቀን እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
9ኛ ክፍል ት/ት የሚጀመረው መስከረም 12/2015 ይሆናል፡፡
መልካም በዓል ይሁንላችሁ!!
2 324
ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የክረምት ትምህርት በመልካም ሁኔታ መጀመሩ የሚታወቅ ነው፡፡ሆኖም አንድ አንድ ተማሪዎች በየክፍሉ ሳምንቱን ሙሉና ሁለት ቀናት የቀሩ ተማሪዎችን ማየት ችለናል፡፡ ስለዚህ ያልመጣችሁ ተማሪዎች ሰኞ እንደማናስገባችሁ አውቃችሁ ከወላጅ ጋር በመምጣት ማስረጃችሁን እንድታቀርቡ እያሳሰብን የቀራችሁም ሆነ ወደፊት የምትቀሩ ተማሪዎች ለሚወሰንባችሁ ውሳኔ እናንተ እና ወላጆቻችሁ ሀላፊነቱን የምትወስዱ መሆኑን እንድታውቁ በድጋሚ እናስጠነቅቃለን፡፡
2 324
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
አሻራ የሚወሰድበት “online registration” አርብ ሀምሌ 01/2014 ስለሚካሄድ ሁላችሁም የደንብ ልብሳችሁን እና ጸጉራችሁን በስነ-ስርዓት አስተካክላችሁ 2፡00 ሰዓት ላይ እንድትገኙ አሳስባለሁ፡፡ ይህ መረጃ የደረሳችሁ ተማሪዎች ሁሉመ መገኘቱ ግድ ስለሆነ ለሌሎች ጓደኞቻችሁ አስተላልፉ ፡፡
