en
Feedback
Jimma Immigration and Citizenship Service

Jimma Immigration and Citizenship Service

Open in Telegram

Alku - bu la"Mother of mankind" "graden of Eden"

Show more
1 987
Subscribers
-324 hours
+257 days
+16930 days
Posts Archive
#CHINA #USA ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች። ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነ
#CHINA #USA ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች። ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነው። አሜሪካ ሰኞ ዕለት በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ላይ እጃቸው አለበት ባለቻቸው የቻይና ባለስልጣናት ላይ ነው የቪዛ እገዳ ጥላ ነበር። መረጃው የአል ዓይን ኒውስ ነው። @ethio_sun1 @ethio_san1

#AtoGelesaDilbo በኢህአዴግ የሽግግር ወቅት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀ መንበር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የፓርላማ አባሉ አቶ ገላሳ ዲልቦ በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለያ
#AtoGelesaDilbo በኢህአዴግ የሽግግር ወቅት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀ መንበር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የፓርላማ አባሉ አቶ ገላሳ ዲልቦ በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለያታቸውን ቤተሰቦቻቸው ገልፀዋል። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አንዱ መስራች የሆኑት አቶ ገላሳ ዲልቦ ባለፈው ዓመት በነበረው ምርጫ የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ጎላኦዳ ቁምቢ መልካ በሎ ወረዳዎችን በመወከል በግል ተወዳድረው በማሸነፍ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ። አቶ ገላሳ ዲልቦ ፤ ለረጅም ዓመታት በስደት ኑሯቸውን በለንደን አድርገው የነበሩ ሲሆን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በውጭ አገራት የነበሩ ተቃዋሚ ኃይሎች ጥሪ ማድረጋቸውን ተከትሎ ወደ አገር ቤት ከተመለሱ አንጋፋ ፖለቲከኞች መካከል አንዱ ነበሩ። @ethio_sun1 @ethio_san1

የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ተፅእኖ በስፔን ! በስፔን ሀገር በ37 ዓመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ የዋጋ ግሽበት ተመዘገበ። በሀገሪቱ በመጋቢት 9.8 % ግሽበት የተመዘገ ሲሆን ይህም በ37 ዓመት የ
የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ተፅእኖ በስፔን ! በስፔን ሀገር በ37 ዓመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ የዋጋ ግሽበት ተመዘገበ። በሀገሪቱ በመጋቢት 9.8 % ግሽበት የተመዘገ ሲሆን ይህም በ37 ዓመት የታየ ከፍተኛው የዋጋ ግሽበት ነው። የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ፤ ጦርነቱን ተከትሎ በሩስያ ላይ እየተጣሉ ያሉ ማዕቀቦች፣ ሩስያም ማዕቀብ በሚጥሉባት ላይ እየጣለች ያለው ማዕቀብ በበርካታ ሀገራት ላይ በግልፅ የሚታይ ተፅእኖ እሳደረ ይገኛል። በስፔን በ37 ዓመታት ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛው የዋጋ ግሽበት በሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት የኢነርጂ ዋጋ መጨመሩን ተከትሎ ሲሆን በሀገሪቱ መንግስት ላይ ጫና ፈጥሯል ተብሏል። @ethio_sun1 @ethio_san1

#ETHIOPIA ከነገ ጀምሮ ዜጎቻችንን የመመለስ ስራ ይጀመራል ተብሏል። ለረጅም ጊዜያት ሲጠበቅ የነበረው በሳዑዲ አረቢያ በከፋ ስቃይ ውስጥ ያሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ ነገ እንደሚጀመር ተገልጿል። የ
#ETHIOPIA ከነገ ጀምሮ ዜጎቻችንን የመመለስ ስራ ይጀመራል ተብሏል። ለረጅም ጊዜያት ሲጠበቅ የነበረው በሳዑዲ አረቢያ በከፋ ስቃይ ውስጥ ያሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ ነገ እንደሚጀመር ተገልጿል። የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሳዑዲ አረቢያ ሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከነገ ረቡዕ ጀምሮ ወደ አገራቸው የመመለስ ሥራ እንደሚጀመር አስታውቋል። ከ100 ሺህ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ከ7 እስከ 11 ባሉት ወራት ውስጥ ለመመለስ እንደታቀደ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። @ethio_sun1 @ethio_san1

#USA #ETHIOPIA የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ በኢትዮጵያ ካደረጉት የስራ ጉብኝት በኃላ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል ፤ በአሁኑ ወቅት በቀጠናው የጆ
#USA #ETHIOPIA የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ በኢትዮጵያ ካደረጉት የስራ ጉብኝት በኃላ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል ፤ በአሁኑ ወቅት በቀጠናው የጆ ባይደን አስተዳደር ዋነኛ ትኩረት በጦርነት ብዙ መስቅልቅል ላጋጠመው ትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ማቅረብ ነው ብለዋል። ልዩ መልዕክተኛው የአሜሪካ መንግሥት ትኩረቱን በትግራይ አድርጎ ለሌሎች አካባቢዎችም የሰብዓዊ እርዳታ ማድረስ ላይ ትኩረት አድርጓል ሲሉ አሳውቀዋል። " ... ከዚህ በላይ ትልቅ ትኩረት ሊያገኝ የሚችል ጉዳይ የለም " ያሉት አምባሳደር ሳተርፊልድ " የምናደርገውና እያልነው ያለው ይህን ዓላማ [የሰብዓዊ እርዳታ ማቅረብ] ማሳካት እና ማስቀጠል ማስቻል ነው " ብለዋል። አምባሳደር ሳተርፊልድ ከመጋቢት 12- መጋቢት 13 /2014 ዓ/ም በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከኢትዮጵያ መንግስት፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣናት እንዲሁም ከረድዔት ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተነጋግረዋል። ምንጭ፦ ሮይተርስ @ethio_sun1 @ethio_san1

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ምንድነው ያሉት ? #ብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት አንድ ተቀማጭነቱን ውጭ ሀገር ላደረገ የቴሌቪዥን ጣቢያ ከሰሞኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈፀመውን የሰው ልጆችን በእሳት የማቃጠል ድርጊት " አረመኔያዊ " ሲሉ በማውገዝ የተሰማቸውን ከባድ ሀዘን ገልፀዋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዚህ ንግግራቸው ድርጊቱ " አለምን ያሳዘነ ፤ የአረመኔነት ድርጊት ነው " ሲሉ ገልፀዋል። ብፁዕነታቸው " ባለፈው 2013 ዓ/ም ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ያላየነው ያልሰማነው " የለም ያሉ ሲሆን " በትግራይ ህዝብ ላይ የደረሰው መከራ እጅግ የሚያሳዝን እጅግ የሚያስለቅስ ነው፤ መፈጠረን ሁሉ የሚያስጠላ ድርጊት ተፈፅሟል " ብለዋል። ነገር ግን የአሁኑ ድርጊት ከሁሉ የባሰ ነው ብለውታል። ከሰሞኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተፈፀመው ድርጊት በተጨማሪ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ተፈፅሟል ያሏቸውን የጭካኔ ተግባራት ዘርዝረዋል። " በትግራይ ክሊኒኮች፣ ሆስፒታሎች ፣ ት/ቤቶች ፣ መድሃኒት ቤቶች ፋብሪካዎች በጠቅላላ ወድመዋል፣ የቀረ ነገር የለም አሁን ደግሞ እንደገና ህፃናት በእናቶች እቅፍ ሆነው፣ ምግብ አጥተው እያለቀሱ እንደቅጠል ደርቀው በምግብ እጦት በእናቶቻቸው እቅፍ ሲሞቱ ፤ እናቶቻቸው እያለቀሱ ጡት እንዳያጠቧቸው እነሱም እራሳቸው በረሃብ ስለደረቁ ወተት የለም እንደዚህ ያለውን ሁኔታ እያየን ነው " ብለዋል። ብፁዕነታቸው እከዛሬ የሆነው ሆኗል ፣ የጠፋው ጠፍቷል፣ የሞተው ሞቷል፣ ያለቀው አልቋል፤ አሁን ግን ቢበቃ ሲሉ ተደምጠዋል። " ሀዘናቸው እጅግ ከባድ " መሆኑን የገለፁት ብፁዕነታቸው " ይሄ የሁሉም የኢትዮጵያዊያን በተለይም የትግራይ ህዝብ ሀዘን ነው እና መከራው ግን በሁሉም ደርሷል ቀስ እያለ እየተስፋፋ በመላ ኢትዮጵያ ደርሷልና በቃው ከእንግዲህ ወዲህ ምናለ ለተረፈው ህዝብ ይቅርታ ቢደረግለት ወይም ደግሞ ቢያሳዝነን ለምን እንዲህ አይነት ችግር ይፈጠራል ፤ ይብቃ " ሲሉ ተናግረዋል። ብፁዕነታቸው ፤ በትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ ለመናገር እስካሁን እድል እንዳላገኙ በመግለፅ ፤ ከዚህ በፊት ሾልኮ የወጣውን ቪድዮ ላይ ሁኔታውን ለመግለፅ ከሞከሩበት ውጭ ሌላ እድል አግኝተው እንደማያውቁ አስረድተዋል። ከዚህ በፊት ሾልኮ በወጣ ቪድዮ ላይ ብፁዕ አቡነ ማትያስ በትግራይ ያለውን ሁኔታ ከተናገሩ በኃላ በወቅቱ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም። ቅዱስ ፓትርያርኩ መነጋገሪያ ሆኖ በነበረው ቪድዮ ትግራይ ክልል ውስጥ ይሰራል ያሉት አረመኒያዊ ስራ እንዲቆም ያቀረቡት ጥይቄ አለመሳካቱን ፤ ፍቃድም እንዳልተሰጠ ገልፀው ሚናገሩት ሁሉ በተደጋጋሚ እንደሚመለስና ፍቃድ እንዳላገኙ ተናግረው ነበር። ከዚህ በኃላም የቤክርስትያኒቱ ሲኖዶስ ዋና ፀሀፊው ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ ሰጥተው በነበረው መግለጫ ፤ የትኛውም መልዕክት ከመተላለፉ በፊት በሲኖዶስ በሚደረግ ስብሰባ ውሳኔ ሊሰጠው እንደሚገባና አቡነ ማትያስ ያስተላለፉት የግል አቋም እንጂ የሲኖዶሱ ውሳኔ እንዳልሆነ አሳውቀው ነበር። የቅዱስ ፓትርያርኩ ፤ የሰሞኑ ንግግር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚወክል ስለመሆን ፤ አለመሆኑ ቅዱስ ፓትርያርኩ በግልፅ አልተናገሩም ፤ አልያም ከዚህ ቀደም እንደነበረው በሲኖዶስ በኩል የተገለፀ ነገር እስካሁን የለም። ቅዱስ ፓትርያርኩ የተናገሩትን ሙሉውን ያንብቡ 👇 https://telegra.ph/Holiness-Abune-Mathias-03-20

#PMOEthiopia የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 5ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ (ዝርዝሩን ከላይ ያንብቡ) @ethio_sun1
+1
#PMOEthiopia የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 5ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ (ዝርዝሩን ከላይ ያንብቡ) @ethio_sun1

የሚፈልጉትን ለማግኝት #የደውሉ ☎️ 0912294529 ☎️ 0919271519 በ ቴሌግራም ወስጥ መስመር ያግኙን @ethio_m12 ✍ @ethio_g19 ✍
የሚፈልጉትን ለማግኝት #የደውሉ ☎️ 0912294529 ☎️ 0919271519 በ ቴሌግራም ወስጥ መስመር ያግኙን @ethio_m12@ethio_g19

በሶማሌ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጣውን ነዳጅ ለመቆጣጠር በቅንጅት ይሰራል-አቶ ሙስጠፌ መሃመድ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በክልሉ የ
በሶማሌ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጣውን ነዳጅ ለመቆጣጠር በቅንጅት ይሰራል-አቶ ሙስጠፌ መሃመድ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በክልሉ የሚስተዋለውን የነዳጅ ዘይት ስርጭት ችግር መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡   በውይይት መድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡   በውይይታቸውም በክልሉ የሚስተዋለውን የነዳጅ እጥረት እና ስርጭት ችግር ዘላቂ እልባት መስጠት በሚቻልባቸው መገዶች እና መወሰድ እንደሚገባቸው ተገልጿል @ethio_sun1 @ethio_san1

#RUSSIA #USA ሩስያ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደንን ጨምሮ ሌሎች የአሁን እና የቀድሞ ባለስልጣናት ወደ ሀገሬ ድርሽ እንዳትሉ ስትል ማዕቀብ ጣለች። መረጃው የአርቲ ኒውስ እና የአልዓይን ኒ
#RUSSIA #USA ሩስያ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደንን ጨምሮ ሌሎች የአሁን እና የቀድሞ ባለስልጣናት ወደ ሀገሬ ድርሽ እንዳትሉ ስትል ማዕቀብ ጣለች። መረጃው የአርቲ ኒውስ እና የአልዓይን ኒውስ ነው። #Joinus 👇👇👇 @ethio_sun1 @ethio_san1

ቤተሰቡን ያስታረቀው ልጅ.... ስሙ የአብስራ ደጉ ይባላል። እሁድ የካቲት27 ጠዋት ወለቴ ከሚገኘው እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፀበል ተጠምቆ ከተመለሰ በኋላ ቤቱን ጠርጎና አስተካክሎ እቃም አጥቦ 4ሰዓ
ቤተሰቡን ያስታረቀው ልጅ.... ስሙ የአብስራ ደጉ ይባላል። እሁድ የካቲት27 ጠዋት ወለቴ ከሚገኘው እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፀበል ተጠምቆ ከተመለሰ በኋላ ቤቱን ጠርጎና አስተካክሎ እቃም አጥቦ 4ሰዓት አካባቢ ይወጣል። የአብስራ እናትና አባቱ ስለተኮራረፉ ከአንድ ወር በላይ አብረው አይደሉም። ይህ ሳይረብሸው አልቀረም ከቤት እንደወጣ ሳይመለስ ይቀራል። በዚህ ወቅት እናትና አባት ተጨንቀው መፈለግ ይጀምራሉ። ህጻን የአብስራ ግን ሊገኝ አልቻለም፤ ወላጆቹ እንደተጨነቁ አምስት ቀናት አለፉ። በዚህ ጊዜ እናት ለባይሽ ኮልፌ በጎ አድራጎት ማኅበር ደውላ ልጄን አፋልጉኝ ስትል አልቅሳ ትማጸናለች። ባለቅን ልቦቹ የእናትን ጭንቀት ተረድተው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አፋልጉኝ ያወጣሉ። በዚህ ጊዜ የማኅበሩ ተከታታይ ሳጅን ገነት ስልክ ደውላ ህጻኑ የት እንደሚገኝ ታሳውቃለች። እናትና አባቱ ስለተኮራረፉ ከቤት ጠፍቶ ለቀናት ቤተክርስቲያን በር ላይና ጎዳና እያደረ የሰነበተው ህጻን የአብስራ የተገኘው ትላንት ለሊት በአዲስ አበባ ጎዳና ላይ ብቻውን ሲጓዝ ፖሊሶች አግኝተውት መሆኑን ነው የተገለጸላቸው። የተጨነቁት እናትና አባት የምስራቹ ሲነገራቸው በደስታ እያለቀሱ ለየብቻ ሮጠው ፖሊስ ጣቢያ ቶሎ ቢደርሱም ልጅ የአብስራ "የጠፋሁት አውቄ ነው፥ እናንተ ካልታረቃችሁ ወደ ቤት ተመልሼ አልገባም፥ ወይም ማሳደጊያ ላኩኝ"ብሎ ወላጆቹን ከሰሳቸው። ይሄንን ከአብራካቸው ክፋይ የሰሙት እናትና አባት ከወር በላይ የተኮራረፉበትንና የተራራቁበትን ችግር ተነጋግረው ፈተው፥ እሺ ብለው ታርቀው እየሳቁ ወደ ቤታቸው ከልጃቸው ጋር ገብተዋል። መረጃውን ያገኘነው ለባይሽ ኮልፌ በጎ አድራጎት ማህበር ነው። @ethio_sun1 @ethio_san1

#Update የአራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሽኝት በመስቀል አደባባይ ተካሂዳል። በአሁን ሰዓት ላይ የቅዱስነታቸው የክብር አስከሬን
+2
#Update የአራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሽኝት በመስቀል አደባባይ ተካሂዳል። በአሁን ሰዓት ላይ የቅዱስነታቸው የክብር አስከሬን ከመስቀል አደባባይ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት ያደረገውን ጉዞ አጠናቆ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ደርሷል። በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ልዩ ለዩ መንፈሳዊ ሥርዓቶች ከተከናወኑ በኋላም ጉዞ ወደ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሚደረግ ሲሆን በካቴድራሉ ሥርዓተ ጸሎት እና ፍትሀት ሲደረግ አድሮ እሁድ መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ ሥርዓተ ቀብሩ የሚፈጸም ይሆናል። ምንጭ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት @ethio_sun1

የፌድራል መንግስት አጣርቼ እርምጃ እወስዳለው አለ ድርጊቱም ከኢትዮጵያን ባህል እና እሴት የወጣ አሰቃቂ ነው አለ ።
+1
የፌድራል መንግስት አጣርቼ እርምጃ እወስዳለው አለ ድርጊቱም ከኢትዮጵያን ባህል እና እሴት የወጣ አሰቃቂ ነው አለ ።

ህንድ ዛሬ ባጋጥማት የቴክኒክ ችግር ወደ ፓኪስታን ሚሳኤል ማሶንጨፎን አስታወቀች።
ህንድ ዛሬ ባጋጥማት የቴክኒክ ችግር ወደ ፓኪስታን ሚሳኤል ማሶንጨፎን አስታወቀች።

ሀዝነሽ ቅጥ አጣ ሀገሬ ያውም በገዛ ልጆቻሽ 😭😭😭😭
+1
ሀዝነሽ ቅጥ አጣ ሀገሬ ያውም በገዛ ልጆቻሽ 😭😭😭😭

#Ethiopia ዛሬ በተለያይ ማሃበራዊ ድህር ገጾች የተለቀቀው ቪዲዮ አረመኒያዊ ተግባር አሁነም በሀገራችን እንድቀጠል ነው !! በዚህ ትውልድ ያለነው ወጣቶች ፣ ጎልማሶች ፣ በእድሜም የገፋን ሰዎች
+4
#Ethiopia ዛሬ በተለያይ ማሃበራዊ ድህር ገጾች የተለቀቀው ቪዲዮ አረመኒያዊ ተግባር አሁነም በሀገራችን እንድቀጠል ነው !! በዚህ ትውልድ ያለነው ወጣቶች ፣ ጎልማሶች ፣ በእድሜም የገፋን ሰዎች ጭምር በሰው ልጆች ሊደረጉ ይችላሉ ተብለው የማይገመቱ እጅግ በርካታ አስደንጋጭ አሰቃቂ ግፎችን በቪድዮ፣ በፎቶ ተመልክተናል። በየጊዜው የነበሩ እጅግ ዘግናኝ ከህግ ሆነ ከሞራልም ውጭ የሆኑ ድርጊቶችን ወደ ኃላ ተመልሰን ለመዘርዘር ጊዜውም አይበቃን ፤ በተለይም 3 እና4 ዓመታትን ያሳለፋችሁ የምታውቁት ነው። 😢😢😢😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😱😱😱😱☝️☝️☝️☝️☝️

👉 ለውጡን ለማሳካት የምንችለው እኛ ብልጽግናዎች የላቀ ሃሳብ ስላለን ብቻ ሳይሆን ከህዝባችንም ጋር ተቀራርበን የምንሰራ ስለሆንም ነው ።
👉 ለውጡን ለማሳካት የምንችለው እኛ ብልጽግናዎች የላቀ ሃሳብ ስላለን ብቻ ሳይሆን ከህዝባችንም ጋር ተቀራርበን የምንሰራ ስለሆንም ነው ።

ኢትዮጵያ ሀገራችን ውስጥ ስድት ከሞቖሌ ወደ አማራ ክልል በዚህ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን የአማራ ህዝብም በስረዓት ተቀብሎችዋል። #ሰላም #ለኢትዮጵያ!
ኢትዮጵያ ሀገራችን ውስጥ ስድት ከሞቖሌ ወደ አማራ ክልል በዚህ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን የአማራ ህዝብም በስረዓት ተቀብሎችዋል። #ሰላም #ለኢትዮጵያ!