Al-inaya Ye Hadra Jemea (Butajira) አል-ዒናያ የሀድራ ጀመዓ ቡታጂራ
Open in Telegram
እንኳን ደህና መጡ አል-ዒናያ የሀድራ ጀመዓ ቡታጂራ ለእናንተ ያዘጋጀናቸው ነገሮች -አስተማሪ የሆኑ ታሪኮች -ቂሷዎች እና ሀዲሶች -የሀድራ ቅጂዎች አስተያየት ካለቹ @Katbaren https://t.me/joinchat/U4q9OHoSPqgy3teR
Show more567
Subscribers
+224 hours
+117 days
+1230 days
Posts Archive
Repost from Katbare pro ቃጥባሬ ፕሮ
✨🦋የዐሹራ ፆም🦋✨
ከረመዷን ቀጥሎ ከሁሉም በላጩ ፆም🩵
የሙሀረም ወር ❮አስረኛው❯ ቀን ነው።
❝🦋ሠይደልዉጁድ ﷺአስለ አሹራ ተጠይቀው..“ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል ያስምራል”❞
📃አቢ ቀታደህ አል-አንሷሪይ🩵
🦋የዐሹራ ቀን ስለመፆም
✨እመት አዒሻ ረዲየሏሁ ዐንሀ❝ ሠይደልዉጁድﷺ ረመዷን ሳይደነገግ በፊት ዐሹራን ይፆሙ ነበር። ረመዷን ከተደነገገ ቡኋላ የፈለገው ይፆመው ያልፈለገው ደሞ ይተወው ነበር❞አሉ።
የዐሹራ ፆም የሚፆምበት ምክንያት ሙሀረም 10 ነብዩላህ ሙሳ ዐለይሂ ሠላም ከፊርዐውን ጭቆና ነፃ የወጡበት ቀን ነው።
ኢብኑ ዐባስ ረዲየሏሁ ዐንሁ፦❝🦋ሰይደልዉጁድ ﷺ ወደ መዲና ሲገቡ አይሁዶችን በአሹራ ቀን ሲፆሙ አገኟቸውና ይህን ቀን ምንድነው ምትፆሙት ብለው ሲጠይቋቸው ...
እነርሱም፦❝ይሄ ታላቅ ቀን ነው።አሏህ ሙሳን እና ተከታዮቹን ከፊርዐውን እና ሠራዊቱ በማዳን እነርሱን በባህር ያሠጠመበትቀን ስለሆነ ሙሳም ለአሏህ ምስጋናን ለማድረስ ፆሞታልና እኛም እንፆመዋለን❞ ብለው መለሡ።
ሰይደልውጁድምﷺ ❝ ለሙሳ ወዳጅነት ከእናንተ ይልቅ እኛ የቀረብን ሠዎች ነን 🩵እኮ በማለት እሳቸውም ፆሙት ፣ ሶሀባዎችም እንዲፆሙ አዘዙ❞።
🦋የዐሹራ ፆም 9ኛው ሰኞ 10ኛው ደግሞ ማክሰኞ ነው🦋
ከሰኞ እስከ ሰኞ‼
=============
✍ ተከታታይ ወርቃማ ቀናት ከፊታችን፦
√ ሰኞ: የሙሐረም 9ኛ ቀን፣(የነብያችን ሰ.ዐ.ወ ውልደት )
√ ማክሰኞ: የሙሐረም 10ኛ ቀን → የዐሹራእ ጾም፣
√ ረቡዕ : የዐሹራእ ቀጣይ ቀን፣
√ ሐሙስ: ሥራዎች ወደ አላህ የሚቀርቡበት ቀን፣
√ ጁሙዓህ: የአያሙልቢዽ የመጀመሪያ ቀን (ሙሐረም 13)
√ ቅዳሜ: አያሙልቢዽ፣
√ እሁድ: አያሙልቢዽ፣
√ ሰኞ: ሥራዎች ወደ አላህ የሚቀርቡበት ቀን፣(የነብያችን ሰ.ዐ.ወ ውልደት )
አላህ አላህ!
እንኳን ተጨማሪ ሰበብ ኖሮት ሙሐረምን ሙሉውን መፆም ይወደዳል።
የቻልን እንጹም፣ ሌላውንም እናመላክት። አላህ ያግራልን።
✍اللهم صل على سيدنا محمد سيد السادات صلاة تتجلي بها يارحمن علي قلوبنا بالرحمات كما تجليت علي من اخترتهم علي جبل عرفات فتغفر لنا بها الذنوب والزلات وتعيننا بحولك وقوتك علي تجنب المعاصي وعمل الطاعات وتختم لنا بالباقيات الصالحات
🌹ሰደቃ ባበዛህ ቁጥር ሪዝቅህ ይጨምራል
በሶላት ውስጥ እርጋታ መተናነስ ሲበዛ ደስታ ይጨምራል
ወላጆችህን እንክብካቤ ስታበዛ በህይወት ስኬታማነትህ ይጨምራል !
እንኳን ለ 1446ኛው አመተ ሂጅራ አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ!
ኢናሊላሂ ወኢና ኢላይሂ ራጂዑን 💔
የምኖዳቸው እ ምንሳሳላቸው የኡስፉርያ መንዙማ ማዲህ አንጋፉው ሸይኽ አህመድ ቡራቅ ወደ ማይቀርበት ሀገር ሄደዋል 😓
إنا لله وإنا إليه راجعون አልፋቲሐ!
" ሰላትና ፆም ማብዛት ያመለጠው ሰለዋት ዐለ ነቢ ﷺ በማውረድ ይጠመድ ፤ በህይወት ሙሉ ጥሩ የተባለን ስራ ሁሉ ብትሰራና ከዛ ግን አላህ አንድ ሰላት (እዝነቱን) ቢያወርድብህ እቺ ከአላህ የሆነችው ሰላት እድሜ ልክህን የሰራኸውን ጥሩ ስራ ትበልጠዋለች ፤ ምክንያቱም አንተ ሰለዋት እምታወርደው በችሎታህ ልክ ነው ፤ አላህ ደሞ ሰላት የሚያወርድብህ በጌትነቱ መጠን ነው ፤ ይሄ አንድ ብቻ ቢያወርድብክ ነው ፤ ሀዲሱ ላይ እንደመጣው በእያንዳንዱ ሰላት አስር ሲያወርድብህስ ?! አላህን በሰለዋት ዐለ ነቢ ﷺ እየተገዛህ የምትኖረው ህይወት ምን ያህል ያምራል ?! "
📿📿📿📿📿📿📿📿📿📿📿
📗 ታጁል ዐሩስ ሊተህዚብ አን-ኑፉስ
📿📿📿📿📿📿📿📿📿{ﷺ}×🌹
#اللهم_صل_على_سيدنا_محمد_وعلى_آله_وصحبه_وسلم
«የዐረፋ ቀን ሙሐመዳዊ ነው!»
:
«ፋይዳ: ‐ የዐረፋ ጾም የሁለት ዓመት ወንጀል የሚያሰርዝ ምንዳ ኖሮት የዓሹራ ጾም የአንድ ዓመት ወንጀል የሚያሰርዝበት ምክንያት ዐረፋ ሙሐመዳዊ ቀን በመሆኑ ነው። ጾሙ በሰይዲና ሙሐመድ [ﷺ] ህዝብ የተገደበ ነው። ዓሹራ ደግሞ ሙሳዊ ቀን ነው። ሰይዳችን ሙሐመድ [ﷺ] ከነቢያት ሁሉ በላጭ ናቸው። ስለዚህ የርሳቸው ቀን በሁለት ዓመት ምንዳ ተባዛ።»
📚 ሙጝኒል‐ሙሕታጅ፥ አል‐ሺርቢኒ፥ ቅፅ 2፥ ገፅ 572/571
ሸይኾቹ እጅግ የፈሩት አላህን ሳንፈራን አለቅጥ ያጠበቁትን ሸሪዓ ሳናጠብቅ መለያቸው የሆነው ዒልም ላይ ተዘናግተን ሶላትን ችላ ብለን አጥብቀው የከለከሉት አጅነቢ ጋር እየተቀማመጥን አደራ ያሉትን አማና እየበላን ኹሉቃችን ብልሹ መለያችን ውሸትና ጅህልና ሆኖ ሳለ መንዙማቸውን እየቀራን ስላሸቅን ብቻ ሙሪድ ነን ማለታችን ድፍረት እንዳይሆንብን
ሸይኾቻችንን የሀቂቃ መከተል እንከተል:: ከደጋጎቹ ጋር እንመሳሰል::
Repost from Katbare pro ቃጥባሬ ፕሮ
·
የዙል ሒጃህ 10 ቀናት ልቅና
**
✅ የዙል ሒጃህ ወር በኢስላም " አሽሁር አል ሑሩም " የተከበሩ ወራት ተብለው በመሰየም ደረጃ ከተሰጣቸው 4 ወራት መሀከል አንዱ ሲሆን ፤ የመጀመሪያዎቹ 10 ቀናት ደሞ ልዩ ቦታ እና ክብር የሚሰጣቸው ውድ ቀናቶች ናቸው ።
✅ እነዚህ 10 ቀናት የሚጀምሩት የዙል ሒጃህ ወር ከምትጀምርበት የመጀመሪያዋ ለሊት ሲሆን የሚጠናቀቀው ደሞ በዒድ አን–ነህር ቀን ነው ።
✅ አላህ (ሱብሐነሁ ወተዓላ) በአል–ፈጅር ምዕራፍ ውስጥ የእነዚህን ቀናት ታላቅነት የሚያስጨብጡ አንቀፆችን አውርዷል
وقال الله تعالى ...
وَالْفَجْرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
وَلَيَالٍ عَشْرٍ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
✅ " በአስር ሌሊቶችም" በመባል ተጠቀሱት አስሩ የዙል ሒጃህ ቀናት እንደሆኑ ኢብኑ ዐባስ ፣ ኢብ ዙበይር እና ሙጃሂድን ጨምሮ ሌሎች የቁርአን ተፍሲር ሊቃውንቶች ይናገራሉ ።
✅ አሏህ (ሱብሐነሁ ወተዓላ) እጅግ ውድ በሆኑ’ና ፋኢዳቸው በበዙ ነገራቶች እንጂ እንደማይምል የሚታወቅ ሲሆን ፤ በነዚህ 10 ቀናት መማሉ ለቀናቶቹ ታላቅነት አስረጂ ሆነው መቅረብ ይችላሉ ።
✅ በነዚህ 10 ቀናት የሚፈፀሙ መልካም ተግባሮች አላህ ዘንድ ያላቸው ተወዳጅነት በምንም ጊዜ ከሚፈፀሙ ዒባዳዎች ጋር መስተካከል እንደማይችሉ ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) በቀጣዩ ሐዲስ እንደሚከተለው አስቀምጠውታል ።
2/ عن ابن عباس رضي اللَّه عنه قال : قال رسول اللَّه صلى اللَّه عليه وسلم (( ما من أيام العمل الصالح فيها أحب إلى اللَّه من هذه الأيام )) يعني العشر من ذي الحجة قالوا يا رسول اللَّه ولا الجهاد في سبيل اللَّه ؟ قال (( ولا الجهاد في سبيل اللَّه إلا رجلٌ خرج بنفسه وماله فلم يرجع من ذلك بشيء ))
*
✅ ሓፊዝ ኢብኑ ሀጀር በፈትሑል ባሪ ኪታባቸው ውስጥ እንዲህ ይላሉ
" የዙል ሒጃ 10 ቀናትን ልዩ ያደረጋቸው ከሌላው ወር በተለየ ዋና ዋና የሚባሉ የመልካም ስራ አይነቶች (ሶላት ጾም ሐጅ እና ሶደቃ) በአንድ የሚሰበሰቡበት ወር በመሆኑ ነው ይላሉ "
✅ ሓፊዝ ኢብኑ ረጀብ በእነዚህ ቀናት የሚፈጸሙ የግዴታ ዒባዳዎች ከሌላው ጊዜ በተሻለ እጥፍ ድርብ ምንዳን እንደሚያስገኙ ይናገራሉ
✅ ኢማም አን–ነወዊይ በእነዚህ 10 የዙል ሒጃህ ቀናት መጾም በሸሪዐ እጅግ የጠበቀ ተወዳጅነት እንዳለው ይናገራሉ ።
⬇️⬇️⬇️⬇️
👉 እናም በእነዚህ ውድ ቀናት የተለያዩ አይነት ዒባዳዎችን በማብዛት’ና ጊዜያችንን ሊሚያባክኑ’ና ወደ አላህ ከሚያቃርቡ ተግባራቶች ሊያዘናጉን ከሚችሉ ነገሮች በመራቅ ልናሳልፈው ይገባል ፣ በተመሳሳዩም እነዚህ ቀናቶች ታላቅ የመሆናቸውን’ና በውስጣቸው የሚፈፀሙ ዒባዳዎች እጥፍ ድርብ ምንዳ የማስገኘታቸውን ያህል በእነዚህ ቀናቶች ወንጀልን መዳፈርም ከሌላወ ጊዜ በተሻለ ቅጣቱን የበረታ እንደሚያደርገው በመገንዘብ ከማንኛውም ጊዜ በተሻለ ከዬትኛውም የወንጀል ተግባር በመታቀብ ልናሳልፈው ይገባል ።
,
• ከመሞትህ በፊት በጀነት መበሸር ከፈለግክ ሰላዋት አዉርድ
• ሲራጥን በሰላም መሻገር ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• የሰይዳችንን ﷺ ሸፋዓ ማግኘት ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ከዕለተ-ትንሳኤ ጭንቅ መገላገል ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ወንጀልህ እንዲማርልህ ፣ ነዉርህ እንዲሰተርልህ ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ከጭንቅ መገላገል ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• አላሕ ﷻ ዘንዳ ደረጃህ ከፍ እንዲል እና ለሰዪዳችን ቅርብ መሆን ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ቸር ፣ ለጋስ መሆን ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ሀጃህ እንዲወጣ ፣ የተመኘኸዉን እንድታገኝም ሰላዋት አዉርድ
• ድህነትን ማስወገድ ፣ መብቃቃት እና አስተማማኝ ሪዝቅ ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• የአላሕ ﷻ ረህመት እንዲዘንብብህ ፣ በረካ እንዲኖርህ ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ሰዪዳችንን ﷺ የመዉደድ ጫፍ መድረስ ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
• ኢማንህ ተጠብቆ መቆየት ከፈለግክም ሰላዋት አዉርድ
* * *
اللهم صل على سيدنا محمد صلاة تنجينا بها من جميع الأهوال والآفات، وتقضي بها جميع الحاجات، وتطهرنا بها من جميع السيئات، وترفعنا بها عندك أعلى الدرجات، وتبلغنا بها أقصى الغايات من جميع الخيرات في الحياة وبعد الممات، وعلى آله وصحبه وسلم تسليما كثيرا.
ምርጥ ነገር ልጠቁምህ ...
ከፈጅር በፊት ንቃ ውስን ረከዓ ስገድ ከገፍላ ዓለም ትወጣለህ። የፈጅርን ቀብሊያ ስገድና ከአላህ ጋር አውራ ልብህ ያበራል፣ ፈጅር መስጂድ ውጣ በሕብረት ስገድና ጥበቃን ከአላህ አግኝ፣ ከፈጅር በኋላ ጥቂት ብቻ ተቀመጥ በመስጂድ ውስጥ የዛኪሮችና የቃሪኦች ዜማ ውስጥህን በሐሴተ ይሞላዋል። ምን እርሱ ብቻ ስትወጣ ንጹሑ አየርና ከነአዕዋፋቱ በዜማቸው አላህ አላህ ሲሉ ትሰማለህ። በቃ የዚህች ምድር ትልቁ ሐብት ትልቁ ፍቅር አላህ ነው ሌላ ምን አልለ። ሁሉም ፍቅር ወደርሱ አድራሽ ነው። ወደርሱ የማያደርስ ምንም ነገር ዋጋ ቢስ ነው።
ሰይድና ሩሚ (ቀደሰላሁ ሲረሁ) እንዲህ ይላሉ፦ « የሕይወትን ምስጢር ብታውቅ ኖሮ ከፍቅር ውጭ ወዳጅ አድረገህ የምትይዘው ምንም ነገር የለም ነበር።»
ያ አላህ ♥
ትንሽ ስለ አቡ የዚድ አልበስጣሚይ ረ.0
ልጅ ሆነው አባታቸውን በሞት ቢያጡም ታላቅና ጀግና እናት ነበረቻቸው።
ለአቅመአዳም በደረሱ ግዜ በደስታ ወደ እናታቸው መጡና "እናቴ ረጁል ሆንኩኝ (እድሜዬ ደረሰ)"
እናት "ረሱልን አይተኻቸዋል ወይ?"
ልጅ "እሳቸውን ካላየሁ ረጁል አልሆንም ማለት ነው?"
እናት "አዎ አትሆንም!" አለቻቸው
(የጀግንነት ረጁልን ማለቷ ነው)
ልጅ "ታዲያ እንዴት ነው ላያቸው የምችለው?"
እናት "ሰለዋት አብዝተህ አውርድባቸው" አሉ።
ልጅም የእናታቸውን ንግግር በመስማት ሰለዋት ላይ በረቱ። የሆነ ግዜም ነቢን በመናም ማየት ቻሉ።
ብስራቱንም ለእናታቸው ነገሩ።
"እናቴ ነቢን አየሁኮ!"
እናት "በመናም ወይስ በእውን?"
ልጅ "በመናም"
እናት "በእውን እስካላየሀቸው ድረስ ከሪጃሎች አትሆንም" አለቻቸው።
ልጅ "እንዴት ሆኖ በእውን ሊታዩ ይችላሉ?" ሲሉ ጠየቁ
እናት "በየቀኑ በሰላት ላይ አስ-ሰላሙ ዐለይከ አዩሀን ነቢዩ
(ሰላም ለአንተ ይሁን አንተ ነቢይ ሆይ) በማለት ሰላምታ ታቀርብላቸው አደል? ታዲያ ይህ ሰላምታ አጠገብህ ላለ እንጂ ሩቅ ያለን ሰው በዚህ መልኩ ሰላም ትለዋለህ ወይ?"
ልጅ ምክሩን ተቀብለው ሰላታቸውን በኹሹዕ መስገድ ተያያዙ።
"...አስ ሰላሙ ዐለይከ አዩሀን ነቢዩ (ሰላም ለአንተ ይሁን አንተ ነቢይ ሆይ)" የሚለው ቦታ ሲደርሱ እንባ ይቀድማቸው ነበር። በመጨረሻም ነቢ ሠላምታውን ሲመልሱላቸው ሰላታቸው ውስጥ ሆነው ተመለከቱ።
እናትም "አሁን ከሪጃሎች ሆነሀል ከዛሬ ጀምሮ ፍርሀት የሚባል የለብህም" አሏቸው
በኃላም እኚህ የእናታቸው ሙተረቢ ከዛሂዶች ከዐሪፎች ከሙተቂኖች ሆኑ 💚
ጀግኖች ይፈጠሩ የነበረው በጀግና እናቶች ነበር 💚
💥وصلي اللهم علي الحبيب المصطفي سيدنا محمد وعلى آله وصحبه وسلم 💥
Repost from Katbare pro ቃጥባሬ ፕሮ
🌹 ሰዪዲ ሐቢብ አብዱልቃድር ቢን አህመድ አልሰቃፍ ረሒመሁላህ ሰይዳችን ﷺ ላይ ሰለዋት የማውረድ ፋይዳዎች ብለው የጠቀሷቸው :
1. ለዱዓችን መልስ የማግኘት ሰበብ ነው ።
2. በ ላ ኢላሀ ኢለሏህ ለመሞት ምክንያት ነው ።
3. ሰይዳችንን ﷺ የማየት እድል ምክንያት ነው።
4. በዚች ህይወት ውስጥ ስኬታማ ለመሆን ምክንያት ነው ።
5. በልጆች ላይ የበረከት ምክንያት ነው
6. ኑሮን ለማመቻቸትና የሪዝቅ መግራት ምክንያት ነው።
7. በዚች ህይወት ውስጥ ከሚያጋጥሙ አደጋዎች መጠበቂያ ምክንያት ነው።
8. ወደ ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የምንቀርብበት ምክንያት ነው።
9. ከሁሉን ቻይ አምላካችን አሏህ ታላቅ እንክብካቤን የምናገኝበት ምክንያት።
10. የጌታችን አላህ እና የነቢዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ውዴታን የምናገኝበት ምክንያት ነው
ያአላህ ሰይዳችን ﷺ ላይ ሰለዋትን ከሚያበዙ ባርያዎችህ አድርገን
ያረቢ ..አሚን
