cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ባህረ ጥበባት

"ህዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል" ት. ሆሴዕ 4:6 አለማወቅ እያጠፋን ነውና እንወቅ። ለማንኛውም አስተያየትና ጥያቄ @Filoppader

Show more
Advertising posts
1 164Subscribers
+124 hours
-37 days
-130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Show all...
ሰዎች ይጠሉኛል፤ ብናገር አልደመጥም፤ ብማር አይገባኝም? ጨርሳችሁ አዳምጡት ታተርፉበታላችሁ

ተናግረን የማንደመጠው፣ ሰርተን የማናተርፈው፣ ትዳር ጀምረን የማንጨርሰው፤ተምረን የማይገባን፣ በልተን የማንጠግበው፣ ነግደን የማናተርፈው ለምን ይሆን??

👍 2
🙏 10🥰 3
Show all...
🛑ጥያቄና መልስ (ከናንተው የመጡ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው

👍 9
Show all...
ብዙዎቻችን ለምን ተስፋ እንቆርጣለን፤ መፍትሔውስ

ይህ ትምህርት በገጠመኝ የቴሌግራም የጸሎት እና የስግደት ማኅበር በቀጥታ ስርጭት የተላለፈ ሲሆን። ዘወትር ረቡዕ በኢትዮጵያ ሰዓት ከምሽቱ 1:30 ላይ የሚተላለፍ ሲሆን። በሌሎቹም ቀናት የተለያዩ መርሃ ግብራት ስለሚተላለፉ፤ እንዲሁም በጸሎት እና በስግደት መበርታት ከፈለጋችሁ እና እርኩሳን መናፍስትን እንዴት መዋጋት እንዳለባችሁ መማር ከፈለጋችሁ ከስር ባለው ሊንክ ተቀላቀሉ 👇

https://t.me/getemegn12

ለበለጠ መረጃ +251941317410 ይህን ስልክ ይጠቀሙ

🥰 11
በ9 ደቂቃ ነፍሳችሁን አድሷት
Show all...
15🥰 3👍 1
Show all...
ከሴተኛ አዳሪነት ወደባህር ላይ እስከመራመድ ቅድስና

ሚያዚያ 6 ቅድስት ግብፃዊት ማርያም እረፍቷ ነው +++++ቅድስት ማርያም ግብጻዊት~ የተወለደችው በግብጽ ሲሆን ገና የ12 አመት ልጅ እያለች ነበር ወደ እስክንድርያ በመሄድ ድንግልናዋን ያፈረሰችው:ከዚያም የዝሙት ፍቅር አድረባት:ለ17 አመት ያህል ሰዎችን በሚያቃጥል የሃጥያት እሳት ታስፈጃቸው ነበር ዝሙት እያሰራች:ብዙዎችንም ታስት ነበር። ዝሙት ከመውደድ የተነሳ ገንዝብ እንኳን ልስጥሽ ሲሉ አትቀበልም ነበር:በእግዚአብሄርም አታምንም ነበር። በዛው ፋንታ እንደፈለገች ትሆን ነበር። በልቧ ከዚህ ሲራዬ ማንም አይከለክለኝም ትል ነበር:: አንድ ቀን ሊቢያውያን እና ግብጻውያን ወደ ባህር እየተቻኮሉ ሲሄዱ አይታ ወዴት እንደሚሄዱ ብጠይቃቸው የከበረ የጌታችንን መስቀል በዓል ለማክበር ወደ እየሩሳሌም እንደሚሄዱ ሲነግሯት እና የሚሄደው ሰው ብዙ መሆኑን ሲታይ: ብዙ ዘመዶችን አገኛለው ብላ ከነሱ ጋር ለመሄድ ተነሳች:ለጉዞዋ ወይም ለምግብ የሚሆን አንድም ገንዘብ አልያዘችም ነበር። በሁኃላም በሰውነቷ ማማር ብዙዎችን በዝሙት ምክንያት አጠመደች ወደ ተቀደሰ ቦታ የሚሄዱቱን ሰዎች በማሳት ዋና የሰይጣን መረብ ሆና ነበር:በዚህም ስራዋ እየተኩራራች ለሰው ሁሉ ትናገር ነበር። የሃጥያተኛን ሞት የማይወድ እግዚአብሄር መመልሷን እየጠበቀ ይታገሳት ነበር። በመጨረሻም እየሩሳሌም ደርሰው ከበዓሉ በፊት እንደለመደችው እንደውም በከፋ መልኩ ዝሙትን አብዝታ ትሰራ እና ሰውንም ታስት ነበር። የበዓሉ ዕለት ጠዋት ብዙ ተሳላሚዎች ጌታችን መቃብር ላይ ወደ ተሰራችው ቤተ-ክርስቲያን ሊሳለሙ ሲሄዱ አየችና እዛ ሄደው ምን እንደሚያደርጉ ለማወቅ ፊላጎት አደረባት እናም ህዝቡ በሚገቡበት በር እየተጋፋች ለመግባት ትሞክር ጀመር በኃላም በሩ ጋር ስትደርስ የሆነ ሃይል ሲገፋት ይታወቃት ጀመር። ሌሎችን ሰዎች ስታይ በቀላሉ ይገባሉ እና መጀመሪያ ላይ ምንድን ነው እያለች ትስቅ ነበር?! ደጋግማ ስትሞክር አልቻለችም በኃላም ዝም ብላ በሩ ላይ ቆመች እንደገናም ደጋግማ ሞከረች በኃላም ሲደክማት ግዜ እልፍ ብላ ከበሩ አጠገብ ቆመች። በህሊናዋም በብዙ መከራ ምን እንደሆነ ታስብ ጀመር: ቅዱስ መስቀሉን ለማየት እሷ ያልቻለችበትን ምክንያት ታስብ ጀመር:የድህነት ቃል የልቦናዋን አይኖች ነካቸው እና እንዳልገባ የከለከለኝ የራሷ የግል ሃጥያት መሆኑን ተረዳች። በኃላም በማልቀስ እና ደረቷን እየደቃች ከውስጣዊ ልቧማዘን ጀመረች:"ለምን አልገባም? እንዳልገባ የከለከለኝ የኃጢአቴ ብዛት ነው?" እያለች ደጋግማ እራሷን ትጠይቅ ጀመር:ያን ግዜ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ስዕል (ስዕል አድኖ)ከበሩ ላይ አየችና ሄዳ ስዕሏ ፊት ቆማ የስዕሏን ግርማና ውበት ባየች ግዜ ያለፈ የራሷ ሃጥያት ወለል ብሎ ታያት እና አፈረች። በኃላም በብዙ ለቅሶ ስዕሏ ስር ወድቃ "ከእንግዲህ በኃላ ጌታየን አገለግል እና ያንቺ ባርያ እሆን ዘንድ እድል አገኝ ይሆን ?" እያለች ታለቅስ እና ትለምን ጀመር። ጌታችንንም ካለችበት ስቃይና መከራ እንዲያድናት እና በመንገዱ እንዲመራት ለመነችው:"ቅዱስ መስቀሉን ካየው በኃላም አለም እና ደስታዋን እንደምክድ ቃል ገባለው" ብላ ቃል ገባች። ከጸለየችም በኃላ የመተማመን ስሜት ተሰማትና ወደ መስቀሉ ቦታ ወደሚያስገባው ቦታ ሄደች ከዚያም ያለችግር ገባች። በኃላም መስቀሉ ጋር ደርሳ በመንቀጥቅጥ እና በብዙ እምባ ሳመች የእግዚአብሄርን ሚስጥር እና ንስሃን እንዴት እንደሚቀበል አየች:ከዚያም ወታ ቃል ወደ ገባችበት ወደ እመቤታችን ስዕል ጋር ሄዳ "የሃጥአንን ንሰሃ ባንቺ አማላጅነት የሚቀበል እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን:የከበርሽ እመቤቴ ሆይ ኃጥእት እኔ ምን እላለው?"አለችና "አለቀስች ወደ ሥዕሏም ተመልሳ አለቀሰች፡፡ ከሥዕሏም ድምፅ ወጣና ‹‹ወደ ዮርዳኖስ በረሃ ሂጂ›› አለቻት፡፡ ዮርዳኖስን ተሻግራ ሄዳ 47 ዓመት በበረሃ ብቻዋን ስትጋደል ኖረች፡፡ ሰይጣንም በዝሙት ጦር ይዋጋት ነበር፡፡ 40 ጾምን ሊፈጽም ቅዱስ ዞሲማስ ወደ በረሃው መጣ፡፡ በዚያ በረሃ ውስጥ የሚጽናናበትን ነገር እንዲሰጠው ወደ ጌታችን ጸለየና ማርያምን ገለጠለት፡፡ ሲጠጋት ሮጣ አመለጠችውና ‹‹ዞሲማስ ሆይ ጨርቅ ጣልልኝ›› ብላ በስሙ ስትጠራው እጅግ ደነገጠ፡፡ ልብሱንም ከሰጣት በኋለ ሰገደላት፡፡ ገድሏንም እንድትነግረው በብዙ ለመናትና ነገረችው፡፡ በዓመቱ ሥጋ ወደሙን አምጥቶ እንዲያቆርባት ጠየቀችው፡፡ በዓመቱ መጥቶ አቆረባት፡፡ አሁንም በዓመቱ ይመጣ ዘንድ ለመነችው፡፡ ድጋሚም ሲመጣ ዐርፋ አንበሳ አስክሬኗን ሲጠብቀው አገኛት፡፡ አንበሳውም መቃብሯን ቆፍሮ አሳየውና ገንዞ ቀበራት፡፡ ገድሏንም ለመነኮሳቱ ሁሉ ነገራቸው፡፡ አባ ዞሲማስም ከደጋግ ክርስቲያን ፍልስጤማውያን ወላጆች የተገኘ ጻድቅ ነበር፡፡ ለመምህርም ሰጥተውት በሚገባ ተምሮ ካደገ በኋላ መነኮሰ፡፡ ሲሠራም ሆነ ሲበላ እንኳን ምስጋናን ከአፉ የማያቋርጥ ደገኛ አባት ከሆነ ከ45 ዓመት በኋላ ቅስና ተቀበለ፡፡ ተጋድሎውንም ጨምሮ 13 ዓመት ከቆየ በኋላ ሰይጣን በልቡ ክፉ ሀብን አሳደረበት፡፡ በልቡም ከበጎ ሥራዎች ሁሉ እኔ ያልሠራሁት ምን ነገር አለ?›› ይል ጀመር፡፡ ጌታችንም ሊተወው አልወደደምና መልአኩን ልኮ ወደ ዮርዳኖስ አቅራቢያ ወዳለው በረሃ እንዲሄድ ነገረው፡፡ በዚያም ሌሎች ደጋግ አባቶችን አገኘና ከእነርሱ ተማረ፡፡ በዚያም ሳለ ወደ በረሃው ገብቶ የሚጽናናበት ነገር ይገልጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን በጸለየ ጊዜ ነው ማርያምን ያገኛት፡፡ ዞሲማስ ብሔረ ብፁዓንም ድረስ ሄዶ የቅዱሳንን አኗኗራቸውንና ገድላቸውን አይቶ የጻፈልን ታላቅ አባት ነው፡፡ የቅድስት ማርያም ግብፃዊት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን። አሜን!

10
ሚያዚያ 6 ቅድስት ግብፃዊት ማርያም እረፍቷ ነው +++++ቅድስት ማርያም ግብጻዊት~ የተወለደችው በግብጽ ሲሆን ገና የ12 አመት ልጅ እያለች ነበር ወደ እስክንድርያ በመሄድ ድንግልናዋን ያፈረሰችው:ከዚያም የዝሙት ፍቅር አድረባት:ለ17 አመት ያህል ሰዎችን በሚያቃጥል የሃጥያት እሳት ታስፈጃቸው ነበር ዝሙት እያሰራች:ብዙዎችንም ታስት ነበር። ዝሙት ከመውደድ የተነሳ ገንዝብ እንኳን ልስጥሽ ሲሉ አትቀበልም ነበር:በእግዚአብሄርም አታምንም ነበር። በዛው ፋንታ እንደፈለገች ትሆን ነበር። በልቧ ከዚህ ሲራዬ ማንም አይከለክለኝም ትል ነበር:: አንድ ቀን ሊቢያውያን እና ግብጻውያን ወደ ባህር እየተቻኮሉ ሲሄዱ አይታ ወዴት እንደሚሄዱ ብጠይቃቸው የከበረ የጌታችንን መስቀል በዓል ለማክበር ወደ እየሩሳሌም እንደሚሄዱ ሲነግሯት እና የሚሄደው ሰው ብዙ መሆኑን ሲታይ: ብዙ ዘመዶችን አገኛለው ብላ ከነሱ ጋር ለመሄድ ተነሳች:ለጉዞዋ ወይም ለምግብ የሚሆን አንድም ገንዘብ አልያዘችም ነበር። በሁኃላም በሰውነቷ ማማር ብዙዎችን በዝሙት ምክንያት አጠመደች ወደ ተቀደሰ ቦታ የሚሄዱቱን ሰዎች በማሳት ዋና የሰይጣን መረብ ሆና ነበር:በዚህም ስራዋ እየተኩራራች ለሰው ሁሉ ትናገር ነበር። የሃጥያተኛን ሞት የማይወድ እግዚአብሄር መመልሷን እየጠበቀ ይታገሳት ነበር። በመጨረሻም እየሩሳሌም ደርሰው ከበዓሉ በፊት እንደለመደችው እንደውም በከፋ መልኩ ዝሙትን አብዝታ ትሰራ እና ሰውንም ታስት ነበር። የበዓሉ ዕለት ጠዋት ብዙ ተሳላሚዎች ጌታችን መቃብር ላይ ወደ ተሰራችው ቤተ-ክርስቲያን ሊሳለሙ ሲሄዱ አየችና እዛ ሄደው ምን እንደሚያደርጉ ለማወቅ ፊላጎት አደረባት እናም ህዝቡ በሚገቡበት በር እየተጋፋች ለመግባት ትሞክር ጀመር በኃላም በሩ ጋር ስትደርስ የሆነ ሃይል ሲገፋት ይታወቃት ጀመር። ሌሎችን ሰዎች ስታይ በቀላሉ ይገባሉ እና መጀመሪያ ላይ ምንድን ነው እያለች ትስቅ ነበር?! ደጋግማ ስትሞክር አልቻለችም በኃላም ዝም ብላ በሩ ላይ ቆመች እንደገናም ደጋግማ ሞከረች በኃላም ሲደክማት ግዜ እልፍ ብላ ከበሩ አጠገብ ቆመች። በህሊናዋም በብዙ መከራ ምን እንደሆነ ታስብ ጀመር: ቅዱስ መስቀሉን ለማየት እሷ ያልቻለችበትን ምክንያት ታስብ ጀመር:የድህነት ቃል የልቦናዋን አይኖች ነካቸው እና እንዳልገባ የከለከለኝ የራሷ የግል ሃጥያት መሆኑን ተረዳች። በኃላም በማልቀስ እና ደረቷን እየደቃች ከውስጣዊ ልቧማዘን ጀመረች:"ለምን አልገባም? እንዳልገባ የከለከለኝ የኃጢአቴ ብዛት ነው?" እያለች ደጋግማ እራሷን ትጠይቅ ጀመር:ያን ግዜ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ስዕል (ስዕል አድኖ)ከበሩ ላይ አየችና ሄዳ ስዕሏ ፊት ቆማ የስዕሏን ግርማና ውበት ባየች ግዜ ያለፈ የራሷ ሃጥያት ወለል ብሎ ታያት እና አፈረች። በኃላም በብዙ ለቅሶ ስዕሏ ስር ወድቃ "ከእንግዲህ በኃላ ጌታየን አገለግል እና ያንቺ ባርያ እሆን ዘንድ እድል አገኝ ይሆን ?" እያለች ታለቅስ እና ትለምን ጀመር። ጌታችንንም ካለችበት ስቃይና መከራ እንዲያድናት እና በመንገዱ እንዲመራት ለመነችው:"ቅዱስ መስቀሉን ካየው በኃላም አለም እና ደስታዋን እንደምክድ ቃል ገባለው" ብላ ቃል ገባች። ከጸለየችም በኃላ የመተማመን ስሜት ተሰማትና ወደ መስቀሉ ቦታ ወደሚያስገባው ቦታ ሄደች ከዚያም ያለችግር ገባች። በኃላም መስቀሉ ጋር ደርሳ በመንቀጥቅጥ እና በብዙ እምባ ሳመች የእግዚአብሄርን ሚስጥር እና ንስሃን እንዴት እንደሚቀበል አየች:ከዚያም ወታ ቃል ወደ ገባችበት ወደ እመቤታችን ስዕል ጋር ሄዳ "የሃጥአንን ንሰሃ ባንቺ አማላጅነት የሚቀበል እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን:የከበርሽ እመቤቴ ሆይ ኃጥእት እኔ ምን እላለው?"አለችና "አለቀስች ወደ ሥዕሏም ተመልሳ አለቀሰች፡፡ ከሥዕሏም ድምፅ ወጣና ‹‹ወደ ዮርዳኖስ በረሃ ሂጂ›› አለቻት፡፡ ዮርዳኖስን ተሻግራ ሄዳ 47 ዓመት በበረሃ ብቻዋን ስትጋደል ኖረች፡፡ ሰይጣንም በዝሙት ጦር ይዋጋት ነበር፡፡ 40 ጾምን ሊፈጽም ቅዱስ ዞሲማስ ወደ በረሃው መጣ፡፡ በዚያ በረሃ ውስጥ የሚጽናናበትን ነገር እንዲሰጠው ወደ ጌታችን ጸለየና ማርያምን ገለጠለት፡፡ ሲጠጋት ሮጣ አመለጠችውና ‹‹ዞሲማስ ሆይ ጨርቅ ጣልልኝ›› ብላ በስሙ ስትጠራው እጅግ ደነገጠ፡፡ ልብሱንም ከሰጣት በኋለ ሰገደላት፡፡ ገድሏንም እንድትነግረው በብዙ ለመናትና ነገረችው፡፡ በዓመቱ ሥጋ ወደሙን አምጥቶ እንዲያቆርባት ጠየቀችው፡፡ በዓመቱ መጥቶ አቆረባት፡፡ አሁንም በዓመቱ ይመጣ ዘንድ ለመነችው፡፡ ድጋሚም ሲመጣ ዐርፋ አንበሳ አስክሬኗን ሲጠብቀው አገኛት፡፡ አንበሳውም መቃብሯን ቆፍሮ አሳየውና ገንዞ ቀበራት፡፡ ገድሏንም ለመነኮሳቱ ሁሉ ነገራቸው፡፡ አባ ዞሲማስም ከደጋግ ክርስቲያን ፍልስጤማውያን ወላጆች የተገኘ ጻድቅ ነበር፡፡ ለመምህርም ሰጥተውት በሚገባ ተምሮ ካደገ በኋላ መነኮሰ፡፡ ሲሠራም ሆነ ሲበላ እንኳን ምስጋናን ከአፉ የማያቋርጥ ደገኛ አባት ከሆነ ከ45 ዓመት በኋላ ቅስና ተቀበለ፡፡ ተጋድሎውንም ጨምሮ 13 ዓመት ከቆየ በኋላ ሰይጣን በልቡ ክፉ ሀብን አሳደረበት፡፡ በልቡም ከበጎ ሥራዎች ሁሉ እኔ ያልሠራሁት ምን ነገር አለ?›› ይል ጀመር፡፡ ጌታችንም ሊተወው አልወደደምና መልአኩን ልኮ ወደ ዮርዳኖስ አቅራቢያ ወዳለው በረሃ እንዲሄድ ነገረው፡፡ በዚያም ሌሎች ደጋግ አባቶችን አገኘና ከእነርሱ ተማረ፡፡ በዚያም ሳለ ወደ በረሃው ገብቶ የሚጽናናበት ነገር ይገልጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን በጸለየ ጊዜ ነው ማርያምን ያገኛት፡፡ ዞሲማስ ብሔረ ብፁዓንም ድረስ ሄዶ የቅዱሳንን አኗኗራቸውንና ገድላቸውን አይቶ የጻፈልን ታላቅ አባት ነው፡፡ የቅድስት ማርያም ግብፃዊት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን። አሜን!
Show all...
👍 6🙏 1
Show all...
የዝሙት መንፈስ መንስኤ እና መፍትሔ

የዝሙት አይነቶች ምን ምን ናቸው? የዝሙት አይነቶችን ከነቅጣታቸው በሙሴ ላይ አድሮ ነግሮናል። (ኦሪ ዘሌ 20፥7-22) 1. በስጋዊ ፍትወት እና ስሜት እየተቃጠሉ ዘርን በምድር ላይ ማፍሰስ፤ (ኦሪ ዘፍ 38፥6-11) 2. ከምድር ከድንጋይ ጋር መዘሞት፤ (ኦሪ ዘሌ 20፥15) 3. ከዕፅዋት ጋር መዘሞት ፣ ከእንስሳት ጋር መዘሞት፤ (ኦሪ ዘሌ 20፥15) 4. በስጋ ተዛምዶ ከሚቀርቡን ዘመዶቻችን ጋር መዘሞት፤ (ኦሪ ዘሌ 18፥6 እና 17) 5. ወንድ ከወንድ ጋር መዘሞት፤ (ኦሪ ዘፍ 19፥9) (መሳፍ 19፥22) 6. ሴት ከሴት ጋር መዘሞት፤ (ኦሪ ዘሌ 20፥15) 7. ከስርዓተ ጋብቻ ውጪ የሆነና በጋብቻ ያልተመሰረተ ሴትና ወንድ የሚፈፅሙት ዝሙት (ኦሪ 23፥17) 8. ከራስ ጋር መዘሞት፤ (1ቆሮ 6፥18) 9. በሚጠጣ፣ በፍቅረነዋይ፣ በሌሎቹም ስጋዊ ሃሳቦች መዘሞት፤ (1ኛ ቆሮ6፥13) 10. በአምልኮ ጣኦት መዘሞት፤ (የሐ 21፥25) 11. በመብል እየጎመጁ ወይም ወንድምን ሃብቱን ንብረቱንና ጉልበቱን ሚስቱን እየተመኙ መጎምጀትም ዝሙት ነው። ዝሙት️ በመፅሐፍ ቅዱስ ዝሙትን የሚፈፅም በገዛ ስጋው ላይ ሀጢያትን ይሰራል፡(1ኛ ቆሮ 6÷18) ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው፡ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት! (1ኛ ቆሮ 7÷2) በዚህ በአለንበት ዘመን ሰውን ያንበረከከ ትልቁ ሀጢያት "ዝሙት" ነው፡ ዝሙት ሰውን ከእግዚአብሔር ይለየዋል፡ ዝሙትን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን ህግ ይጥሳልና፡(ዘዳ 5÷18) ዝሙት ሀጢያት ነው! የሀጢያት ደሞዝ ደግሞ ሞት ነውና፡(ሮሜ 6÷18) እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብ ነው! ከሀጢያት መራቅ ማስተዋል ነው። አስተዋይ የሆነ ሰው ከእግዚአብሔር መንግስት እንዳይለይ ራሱን ከአመንዝራ ሊጠብቅ ይገባዋል። ዝሙት ከክፉ ልብ የሚወጣ፡(ማቴ 15÷19) የክርስትያኖችን ህብረት የሚረብሽ፡(1ኛ ቆሮ 5÷9-11 ) ዝሙት ከእግዚአብሔር የሚለይ ለሰው ልጅ ️መንፈሳዊ እድገት እንቅፋት የሆነ ሀጢያት ነው፡(1ኛ ቆሮ 6÷9) Like Share Subscribe በማድረግ ለሌሎች ያድርሱ ትምህርቱ ከጥታ በገጠመኝ መንፈሳዊ የቴሌግራም ማኅበር የተላለፈ ነው። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ዘወትር ረቡዕ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 1:30 ላይ ይጀምራል። የቀጥታ ስርጭት ቅጂ ስለሆነ ለድምፅ መቆራረጥ እና ጥራት ይቅርታ እንጠይቃለ ገጠመኝ መንፈሳዊ የቴሌግራም ማኅበር ለመቀላቀል ይህንን

https://t.me/getemegn12

ሊንክ ተጠቀሙ

🙏 5
እስከመጨረሻው ብታዳምጡት ታተርፉበታላችሁ
Show all...
🥰 9