en
Feedback
ሃይማኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

ሃይማኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Open in Telegram
767
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እውን እመቤታችን ከኢየሱስ ውጪ ሌላ ልጅ አላትን? ግልጽ መልስ። " ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን?"(ማቴ13:55) ቅዱስ ስምዖን ( የጌታችን ወንድም ) የቅዱስ ዮሴፍ ወንድም የቀለዮጳ ልጅ ሲሆን እናቱ ደግሞ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እህት የምትባላዋ የቀለዮጳ ሚስት ማርያም ናት። የቤተክርስቲያን ታሪክ ጸሃፊ አውሳብዮስ እንደተናገረው ቅዱስ ስምዖን #የተወለደው ከጌታችን መወለድ 13 ዓመት አስቀድሞ ነው። ይህም ማለት ጌታችን ማስተማር በጀመረበት ዓመት የ43 ዓመት ጎልማሳ ነበር ማለት ነው። ቅዱስ ያዕቆብ ( የጌታችን ወንድም ) ይህም ሰው የቅዱስ ስምዖን ታናሽ ሲሆን የተወለደውም ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1BC ነው። ይህም ማለት ከክርስቶስ ልደት( ውልደት) በፊት ባሉት በመጨረሻዎቹ መቶ አመታት ውስጥ ነው። 1 ክፍለ ዘመን መቶ አመት ነውና። እንዲገባን ይህን ተመልከቱ 👉....., 9BC, 8BC, 7BC, 6BC, 5BC, 4BC, 3BC, 2BC, 1BC, 1AD, 2AD, 3AD,...2009, 2010,2011,2012.... BC ማለት ዓመተ ዓለም - AD ማለት የጌታ አመት ዓመተ ምህረት ማለት ነው። #ማስታወሻ ዮሳና ይሁዳም የትውልድ ዘመነኛቸው ከጌታችን ልደት በፊት ነው። ይህም የሚያሳየው ጌታችን በእድሜ ከ4ቱም የሚያንስ መሆኑን ነው። አብሯቸው ስላደገና የእናቱ እህት የምትባል ለማርያም ልጆችም ስለሆኑ በዝምድና ወንድሞቹ ተባሉ። አንባቢያን ሆይ : እንግዲህ ይሁዳ ስምዖን ዮሳና ያዕቆብ በእድሜ ከጌታችን ከበለጡ በምንም መልኩ የእመቤታችን የስጋ ልጆች ሊሆኑ አይችሉም። እመቤታችን የመጀመሪያና የመጨረሻ የበኩር ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ኢየሱስንም ከመውለዷም ከወለደችም በኃላ በድንግልናና በንጽሕና ጸንታ የኖረች ሰው ናት። ወንድሞች የተባሉት በትክክል ወንድሞች ከሆኑ ታናናሽ ወንድሞች ናቸው ማለት ነው ፡፡ እነዚህ ታናናሽ ወንድሞች ጌታን በአደባባይ ገስጸዋል፣ መክረዋል። /ዮሐ. 7፡2-5/ ፡፡ በአይሁድ ባህል ታናናሾች ታላቅ ወንድማቸውን በአደባባይ አይገስጹም ፣ አይመክሩም ፡፡ ወንድሞች መባላቸው ታናናሾች አለመሆናቸውን የሚያሳይ ነው ፡፡ ስለዚህ የድንግል ማርያም ልጆች አይደሉም ፡፡

አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ ወዮ፤በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ ወዮ፡፡ እንዲል ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ስቅለቱን በዲሜጥሮስ ቀመር አውጥተን የጌታን መከራውን አስበን በስግደት ህማማቱን እናስባለን በዝክረ ጥንተ ስቅለቱ በጥቅምት ፳፯ ደግሞ በመስቀል የተደረገልንን አስበን እናመሰግነዋለን፡፡ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ ጋር ቤተ ክርስቲያን በ15ኛው መ.ክ.ዘ የነበሩትን አቡነ መብዓ ጽዮንን ታስባለች፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮንን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹ በዕለተ ዓርብ የተቀበልከውን መከራ ግለጽልኝ ››ብለው በጸለዩ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ የተቀበላቸውን መከራዎች ሁሉ አሳያቸው፡፡ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ከርስቶስን መከራ ካዩበት ቀን ጀምሮ ሕማሙን መከራውን ግርፋቱን እስራቱንበጠቅላላ አስራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል በማሰብ ጀርባቸውን በአለንጋ ይገርፉ ፤ ራሳቸውን በዘንግ ይመቱ ነበር፡፡ የጌታችንን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ዘወትር ስለሚያለቅሱ ዐይናቸው ጠፍቶ ነበር፡፡ ነገር ግን እመቤታችንቅድስት ድንግል ማርያም የብርሃን ጽዋ ይዛ መጥታ ዐይናቸውን ቀብታ አድናቸዋለች፡፡ በዚህ የተነሳ ‹‹በትረ ማርያም›› እየተባሉ እንደሚጠሩ ገድላቸው ያስረዳል፡፡ በዚህ መሰረት ጥቅምት ፳፯ ቀን ለአቡነ መብዓ ጽዮን ቃልኪዳን የገባበት ቀን በመሆኑ በየዓመቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱ ጋር ይከበራል፡፡ የጻድቁ አቡነ መብዓ ጽዮን በረከትና ረድኤት ይደርብን፡፡

ጥቅምት ፳፯ "ተዝካረ ስቅለቱ ለእግዚእነ" ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜ ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ) @የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!! በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! እንኳን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል ዝክረ ጥንተ ስቅለት አደረሳችሁ አደረሰን! ከሁሉ አስቀድሞ ሃይማኖትን መመስከር እንዲገባ “ ከመዝ ነአምን ዘአልቦቱ እም በሰማያት፤ ወአብ በዲበ ምድር ” በሰማይ ያለእናት ከአብ መወለዱን፣ በምድርም ያለ አባት ከድንግል ማርያም መወለዱን እናምናለን። ይህንንም አባቶቻችን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ቅድመ ዓለም ከእግዚአብሔር አብ ያለ እናት፣ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አካላዊ ቃል ፤ ድኀረ ዓለም ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት፣ መለወጥ ሳያገኛት ዘር ምክንያት ሳይሆን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ የተወለደ፤ ወልደ እግዚአብሔር በመለኮቱ ወልደ ማርያም በትስብእቱ ብለው አምልተው እንዲያስተምሩን “ከመ አሐዱ ውእቱ ባሕቲቱ ውእቱ አምላክ ወሰብእ ኅቡረ” ትርጉሙም እርሱ በተዋሕዶ ሰው የሆነ አምላክ ነው ማለት ነው። ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎርዮስ ፴፭፥፳፩ መጋቢት ፳፯ በቃል መነገሩ በልብ መታሰቡ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሠቀለበት ጥንተ ስቅለቱ የሚታሰብበት ቀን ነው ፡፡ ይሁን እንጂ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በዲሜጥሮስ ቀመር መሠረት አጽዋማትን በጠበቀ መልኩ ከትንሣኤ በዓል በፊት ያለውን አርብ “ስቅለት” ተብሎ እንዲከበር ሥርአት ሠርተዋል፡፡መጋቢት ፳፯ ቀን በዓቢይ ጾም ስለሚውል በዓቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለ በዓል ማክበርም ስለማይፈቀድ፤ ወደ ጥቅምት ፳፯ ተዛውሮ ደስ ብሎን እንድናከብረው ቤተክርስቲያን ሥርዓት ሰርታለች ። ጥቅምት ፳፯ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱን ቤተክርስቲያናችን ጌታችን በመስቀሉ ስለፈጸመልን የማዳን ስራ “ በመስቀሉ ወበቃሉ አዕበዮሙ ለአበዊነ ” ። በመስቀሉና በቃሉ አባቶቻችንን ከፍ ከፍ አደረጋቸው እያለች እየዘመረች ታስበዋለች። ከዚህም በተጨማሪ ጥቅምት ፳፯ በወርኀ ጽጌ ውስጥ ያለ በመሆኑ “ …እስመ ውእቱ ክብሮሙ ለቅዱሳን መድኃኒቶሙ ለጻድቃን አሠርገዋ ለምድር በጽጌ ሮማን ስብሐተ ዋህድ ዘምስለ ምህረት በመስቀሉ ወበቃሉ አዕበዮሙ ለአበዊነ ” እያለች የቅዱሳን ክብራቸው የጻድቃን መድኃኒት የሆነው ጌታ ምድርን በአበባ የሚያስጌጣት እንደሆነ በመመስከር ትዘምራለች ። “እስመ አንተ ትክል አንጽሖትየ እግዚኦ ወበቃልከ እለ ለምፅ አንጻሕከ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጐከ ወበመስቀልከ ለጻድቃን አብራህከ ” ልታነጻኝ ይቻልሃል አቤቱ ለምጻሞቹን በቃልህ እንጽተሃልና እያሉ አባቶቻችን በመስቀሉ ለጻድቃን ማብራቱን እያሰቡ በዓሉን በመዝሙር በደስታ ያከብሩታል “ወበከመ ሙሴ ሰቀሎ ለአርዌ ምድር በገዳም ከማሁ ሀለዎ ለወልደ ዕጓለ እመሕያው ይሰቀል” ዮሐ ፫፥፲፬ ሙሴ እባብ በምድረ በዳ እንደሰቀለ የሰው ልጅ ክርስቶስ ይሰቀል ዘንድ አለው ብሎ እንደተናገረ የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት የተሰቀለው መጋቢት ፳፯ ቀን ነው ። ክርስቶስ ስለስቅለቱ ሲናገር ምሳሌ የሚሆነውን፣ ሙሴ በምድረ ባዳ የሰቀለውን፣ የነሐሱን እባብ “ሙሴ እባብ በምድረ በዳ እንደሰቀለ የሰው ልጅ ክርስቶስ ይሰቀል ዘንድ አለው” ብሎ ምሳሌውን ተናግሯል። የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እስራኤልን ከደመና መና አውርዶ፣ከጭንጫ ውሀ አፍልቆ ቢመግባቸው ከዚህ ምድሩ ብቅ፣ሰማዩ ዝቅ ቢልለት፣ ከደጋ ላይ ቢሆንለት የውርጭ ሰደቃ እያበጀ፣ ውሀውን እያረጋ፣ መና መገብኳችሁ ይላል እንጅ ይክልኑ እግዚአብሔር ሠሪዓ ማዕድ በገዳም። ቆላ በሆነማ ባልተቻለውም ነበር ብለዋል ።ጌታም ሊያስተምራቸው ፣ የርሱን ከሃሊነት ሊያሳያቸው፣ የእነርሱንም ሀሰት ሊገልጥባቸው ፣ ሙሴን ነቅዓ ማይ የሌለበት በርሐ ይዘሀቸው ውረድ ብሎት ቢሄዱ መናው ወርዶላቸዋል፣ ውሀውም ፈልቆላቸዋል ።ነገር ግን ነዘር የሚባል እባብ እየነከሰ ይፈጃቸው ጀመር።ከዚህ በኋላ እስራኤል ሙሴ ዘንድ ሂደው ከጌታ ምህረት ቸርነት ከሰው ስሕተት ኃጢአት አይታጣም በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ተናግረን በድለናል እባቦችን ከኛ ያርቅልን ዘንድ ወደ እግዚአብሔር አመልክትልን አማልደን አሉት።ሙሴም ስለሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር ቢጸልይ ጽሩዩን ብርት አርዌ አስመስለህ ሠርተህ ከሚገናኙበት አደባባይ ከእንጨት ላይ ስቀልላቸው አለው። ሙሴም እባብን ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የነሐሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ። (ኦሪ ዘኁ ፳፩ ፥፩፡፱) ይህንም ምሳሌ አባቶቻችን በትርጓሜ ወንጌል ቅዱስ እንዳስቀመጡልን አርዌ ምድር የዲያብሎስ፤አርዌ ብርት የጌታ ምሳሌ ነው ። በአርዌ ምድር(እባብ) መርዝ እንዳለበት በዲያብሎስም ፍዳ ኃጢአት አለበት።በአርዌ ብርት መርዝ እንደሌለበት በጌታም ፍዳ ኃጢአት የለበትም ።አርዌ ብርት በአርዌ ምድር አምሳል መሰቀሉ ጌታ በአምሳለ እኩያን እንደወንጀለኛ ተቆጥሮ ለመሰቀሉ ምሳሌ ነው። ዳግመኛም “ተኈለቈ ምስለ ጊጉያን” ከዐመፀኞችም ጋር ተቈጥሯልና ኢሳ ፶፫፥፲፪ የሚለውን ትንቢት ፈጽሟል። ምሳሌውን አውቆ አስመስሏል ትንቢቱንም አውቆ አናግሯል ። ጲላጦስ አይሁድን ከሁለቱ ማናቸውን ላድንላችሁ ትወዳላችሁ ቢላቸው በርባንን ፍታልን ክርስቶስ የተባለ ኢየሱስን ግን ስቀለው አሉ ።ጲላጦስም በዚህ ሰው ደም ከመጣ ፍዳ ሁሉ ንጹሕ ነኝ ብሎ ባደባባይ እጁን ታጠበ። አይሁድ ደሙ በኛም በልጅ ልጆቻችንም ይሁን አሉ። እርሱም በርባንን ፈታላቸው ጌታንም አሳልፎ ሰጣቸው። ማቴ ፳፯ ፥፳፭ ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ “ሊቃነ መላእክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤ ኃጢያትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፤ በመኳንንት በሚፈርደው በርሱ ፈረዱበት” ፡፡ እንዲል ክርስቶስን አይሁድ ስቀለው ብለው ፈረዱበት አክሊልን የሚያቀናጀውን የነገሥታት ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስን አነገስንህ ብለውታልና ጭፍሮች በፍና ተሣልቆ የእሾህ አክሊል ታተው ደፉለት “ወጸፈሩ ሐራ አክሊለ ዘሦክ ወአስተቀጸልዎ ዲበ ርእሱ” ዮሐ ፲፱፥፪ ። ኢየሱስ ክርስቶስ የእሾኽ አክሊል በመቀዳጀቱ ዕፀ በለስን በልቶ “ምድር እሾኽንና አሜከላን ታበቅልብኻለች” ዘፍ ፫፥፲፰ ብሎ የፈረደበትን አዳም ስለርሱ ክሶ መርገሙን ደምስሶለታል ። መጋቢት ፳፯ ቀን ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ፤ የተሰቀለው የክብር ባለቤት ሰማይን የፈጠረ ነውና ፀሐይ ጨልማለች፣ ጨረቃ ደም ሆኗል፣ ከዋክብት ረግፈዋል። የተሰቀለው የክብር ባለቤት ምድርንም የፈጠረ ነውና በምድር የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለኹለት ተቀዷል፤ ምድር ተናውጣ ዐለቶች ተሠንጥቀዋል፤ መቃብራት ተከፍተዋል፤ ከ፭፻ በላይ ሙታን ተነሥተዋል (ማቴ ፳፯ )፡፡ ኦ አእዳው እለ ለሐኳሁ ለአዳም ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል ፤ ኦ አእጋር እለ አንሶሰዋ ውስተ ገነት ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል

ከዘረኝነት አስተሳሰብ ነጻ ሳንወጣ እግዚአብሔር ጸሎታችንን ሊሰማ አይችልም። ክርስቶስ ዘርን፤ መልክን ለይቶ አልሞተልንም። ክርስቲያን ነኝ የምንል ክርስቶስን እንምሰለው። ክርስቶስ ፍቅር ነው። እንዋደድ። (1ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕ. 2) ---------- 8፤ ዳግመኛ አዲስ ትእዛዝን እጽፍላችኋለሁ፥ ይህም ነገር በእርሱ በእናንተም እውነተኛ ነው፤ ጨለማው ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን አሁን ይበራል። 9፤ በብርሃን አለሁ የሚል ወንድሙንም የሚጠላ እስከ አሁን በጨለማ አለ። 10፤ ወንድሙንም የሚወድ በብርሃን ይኖራል ማሰናከያም የለበትም፤ 11፤ ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና። እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ሰላም ያድርግልን።

ሶስቱ እግዚአብሔር ጸሎትን በቶሎ የሚሰማበት መንገዶች። 1. ስግደት ሰግደህ ላብህ በፈሰሰበት ቦታ ( መስገጃው ) ላይ መተኛት - ያኔ እግዚአብሔር በህልም ወይም በራእይ የምትፈልገውን ነገር ያሳይካል።  2. ጸሎት ጸልየህ አልቅሰህ እንባህ በፈሰሰበት ቦታ ላይ መተኛት - ያኔ እግዚአብሔር በህልም ወይም በራእይ የምትፈልገውን ነገር ያሳይካል።  3. የተመረጡና ቅዱስ ተብረው ከሚጠሩ እጽዋቶች አንለ የወይራ እንጨት ነው። የእሱን እንጨት ቆርጠህ በፊትህ አስቀምጠህ ጸሎት መጸለይ ለ3 ቀን ወይም ለ1ቀን ስትጨርስ እንጨቱን ማቃጠል አመዱንም በአልጋህ ላይ መበተን በዛም አልጋ ላይ መተኛት - ያኔ እግዚአብሔር በህልም ወይም በራእይ የምትፈልገውን ነገር ያሳይካል።  @WwEotc

የእናታችን ሐና በረከትና ምልጃ አይለየን።

+ #እይታዬ - ፫ + ብዙ ጊዜ ሰዎች እኛ ኦርቶዶክሳውያንን '' እናንተኮ ለስዕል የምትሰግዱ ስዕል አምላኪዎች ናቹሁ '' ይሉናል። ግን እውነት ነው? አይደለም። እኛ ለስዕሉ ማለትም ስለዕሉ ለተሳለበት ቀለም፣ ስዕሉ ላረፈበት አቡጀዴ( ሸራ)ና ለፍሬሙ አንሰግድም። ግን በስዕሉ በኩል ለስዕሉ ባለቤቱ እንሰግዳለን። ይህም ስግደት የአምልኮ ወይም የጸጋ (የክብር) ተብሎ ይከፈላል። የአምልኮው ስግደት ለአብ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ብቻ የሚቀርብ ነው። የጸጋ ስግደት ደግሞ ለቅዱሳን መላእክትና ሰዎች የሚቀርብ ነው። ቅዱሳን ስዕላት ከሌሎች ስዕላት የሚለዩት ቅዱስ በሚለው ስማቸው፤ በመንፈሳዊ አገልግሎታቸና ፈውስን በመስጠታቸው ነው። የእግዚአብሔር መንፈስ በቁስ ላይ አድሮ ተኣምር እንደሚሰራ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ እውነት ነው። ለምሳሌ ጌታችን በልብሱ እንዱሁም ቅዱስ ጳውሎስም በልብሱ በሽተኛዎችን እንደፈወሱ ስንመለከት የእግዚአብሔር መንፈስ በቁስ ላይ እያደረ ተአምራትን እንደሚሰራ እንገነዘባለን። በቁስ ደረጃ ደግሞ ስዕልም ጨርቅም አንድ ናቸው ፤ የተሰሩበት ግብአት ቢለያይም። ስለዚህ የእግዚአብሔር መንፈስ በስዕል ላይ አድሮ ተአምር አይሰራም ማለት ስህተት ነው። ለመሆኑ በስዕል የተፈወሰ ሰው ከመጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት እንችላለን? አዎ እይታችንን ካስተካከልን እንችላለን። ለምሳሌ እንዲህ የሚል ቃል አለ :-: " ስለዚህም ጴጥሮስ ሲያልፍ #ጥላውም ቢሆን ከእነርሱ አንዱን #ይጋርድ ዘንድ ድውያንን ወደ አደባባይ አውጥተው በአልጋና በወሰካ ያኖሩአቸው ነበር። ደግሞም በኢየሩሳሌም ዙሪያ ካለችው ከተማ ድውያንንና በርኵሳን መናፍስት የተሣቀዩትን እያመጡ ብዙ ሰዎች ይሰበስቡ ነበር፤ ሁሉም ይፈወሱ ነበር።" (ሐዋ 5:15-16) ቅዱስ ጴጥሮስ በጥላው በሽተኛ ይፈውስ ነበረ። ጥላ ምንድነው? ጥላ በመሰናክል አካል ምክንያት ብርሀን የማያገኝ ቦታ ነው። ይህ ቦታ ብርሀን አስተላላፊ ካልሆነ አካል በስተጀርባ ይገኛል። #ይህ_ጥላ_የሚፈጥረው_ቅርፅ_ብርሀን_እንዳያልፍ_ያደረገውን_አካል_ግልብጥ_ምስል_ነው ። ማለትም ራስኑን ቅርጽ በጥቁር ቀለም መልክ ማለት ነው። ጥላን ወደ ስነ-ጥበብ ስንመጣው ደግሞ Shadow Art በሚባል የአሳሳል ጥበብ እናኘዋለን። ጥቁር ቀለምን ብቻ በመጠቀም አንድን አካል አስመስሎ የመሳል ጥበብ ነው። የቅዱስ ጴጥሮስ ጥላ ልክ እንደ Shadow art ነው በተፈጥሮ ብርሃን በምደር ላይ የተሳለ ፥ ይህንን ጥቁር ጥላ ከነቅርጹ በደንብ ሙያ ተጨምሮበት በቀለም አሳምሮ በመሳል የባለቤቱን ገጽታ ማምጣት ይቻላል። በመሬት ላይ ያረፈው ጥላ መፈወሱ ፤ በክብር በሸራና በተለያዩ አካላት ላይ ምሥጢርን፥ ሥርአትን ጠብቀው የተሳሉ ስዕላት እንደሚፈውሱ የሚያሳይ በቂ ማስረጃ ነው። ይቆየን።

🔷 ከተወደደችው እመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ ነው። ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ሲያበስራት ከእርሷ የሚወለደው እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ነግሯታል። የእግዚአብሔር ልጅ ምን ማለት ነው ካላችሁ የሰው ልጅ ሰው እንደሚባል የእግዚአብሔር ልጅም እግዚአብሔር ይባላል " መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት... ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።" (ሉቃ 1:35)። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስም ስለ ሚወለደው ቅዱስ ሕጻን ድንቅ በሆነ ምሥጢር አሰምቶ ተናገረ " ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" (ኢሳ 9:6) 💠 ከእመቤታችን የሚወለደው 💟 አለቅነት በጫንቃው የሆነ 💟 ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሆነ 💟 የሰላም አለቃ የሆነ ነው። 🔷 በግልጥ ከዚህ የምንረዳው ከእመቤታችን የተወለደው ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር መሆኑን ነው። ቅዱስ ኢሳይያስ ከእመቤታችን የሚወለደው ሕጻን እግዚአብሔር እንደሆነ ሲነግረን አማኑኤል ብሎ ከሩቁ ጠራው። አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው። ከእመቤታችን የተወለደው ከእርሷ ጋር የተሰደደው፣ የተሰበከው፣ ከሐዋርያት ጋር ዞሮ ስብከቱን ያቀናው፣ የሞው የተነሳው የተሰቀለው፣ ወደ ሰማይ ያረገው ተመልሶም የሚመጣው እርሱ ከእኛ ጋር የሆነው እግዚአብሔር/አማኑኤል ነው " እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።" (ማቴ 1:23) ፍቅሩ ይደርብን።

[ ትምህርተ ተዋህዶ!] • ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው፡፡ በመለኮቱ የእግዚአብሔር ልጅ ፥ በስጋ የማርያም ልጅ እንደ ሆነ እናምናለን፡፡ ሰው ባልሆነ አካል የሰውነትን ስራ አይሰራም ሥጋን ከርሷ ከእመቤታችን የነሳ፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም ሞት የሚሥማማት ስለሆነች ሞት የሚሥማማውን ሥጋ ተዋህዶአልና፡፡ ስለዚህም የተቀበለው ልቅሶ ፣ ሕማም ፣ ሞት ከድንግል የነሣው የሥጋ ገንዘብ ነው፡፡ አዘነ አለቀሠ ሲል ብትሠማ ያዘነ ያለቀሠ አምላክ ቃል እንደሆነ አታሥብ ይህ ሁሉ ሥጋ በመሆኑ ነው እንጂ፡፡ • ይህ ወልድ ለአንዱ የምንሰግድለት ለአንዱ የማንሠግድለት ባህርይ የምንል አይደለም፡፡ ሠው የሆነ የእግዚአብሔር ቃል ባህርይ አንድ ሥለሆነ ሥጋው ጋር አዋህደን አንዲት ሥግደት እንሠግድለታለን እንጂ፡፡ • ከድንግል በነሣው ሥጋ ሞተ በማለት ፋንታ እግዚአብሔር አምላካችን ሥጋ በሌለው ባህርይ ታመመ ሞተ ይሉት ዘንድ አይገባም፡፡ • ክርስቶሥ ፈጣሪ እግዚአብሔር መሆኑን እናምናለን! ሥለሆነም ፍጡር ነው የሚሉትንና ዛሬም በአብ ቀኝ ተቀምጦ ለእኛ ያማልዳል የሚሉትን እንቃወማለን! እናወግዛለን! • ወልድ ከአብ ከመንፈስ ቅዱሥ አንድነት ሣይለይ በምልአት ሣለ ሥጋ መሆኑ እንደምን ነው? ቢሉ የዓይን ብርሃን ከአይን ብሌን ሣይለይ ከብርሃነ ፀሀይ ጋር ተዋህዶ ምሉዕ እንደሆነ ጌታም በመልአተ ባሕርዩ ሣለ በመኀፀነ ድንግል አድሮ ከመቅጽበት ዓይን ሠው ሆነ፡፡ የማይለይ የማይነገር የማይመረመር ተዋህዶ ሆነ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወወላዲቱ ድንግል ወለመሥቀሉ ክቡር!!!

እርሶስ ጥያቄ ካሎት ይጠይቁ

💠 #ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነው። 💠 ✧ በወንጌልም ሆነ በተለያዩ የሀዲስ ኪዳን የመልእክት ክፍሎች ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተጠቅሶ ይገኛል። እንደውም ማንኛውም ክርስቲያን፥ ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ማመን መቀበል እንዳለበት አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡ ✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቂሳርያ ሀዋርያቱን ሰብስቦ ሰዎች ማን እንደሚሉት በጠየቃቸው ጊዜ አንዳንዶች ኤልያስ ከነብያት አንዱ እንደሆነ እንደሚናገሩ ሲነግሩት እናንተ ማን እንደሆንኩ ትላላችሁ ብሎ ቢጠይቃቸው ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ ተናግሯል ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን አመስግኖ ስጋና ደም እንዳልገለጠለት የሰማዩ አባቱ እንደገለጠለት በመናገር በዚህ በቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር ቤተክርስቲያኑን እንደሚመሰርት ጌታ ተናግሯል ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚለው የቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር የቤተክርስቲያን መሰረት ነው። የጌታን ማንነት የሚገልጽ እምነታችን መሰረት ነው፡፡ ✧ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የማያምን እንዲሁም ብሎ የማይመሰክር ሰው ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ አይችልም ምክንያቱም የክርስትና መሰረት ይህ ስለሆነ ‹‹ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እርሱም፦ አንዳንዱ #መጥምቁ_ዮሐንስ ፥ ሌሎችም #ኤልያስ ፥ ሌሎችም #ኤርምያስ ወይም #ከነቢያት_አንዱ ነው ይላሉ አሉት። እርሱም፦ #እናንተስ #እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ #ክርስቶስ_የሕያው_እግዚአብሔር_ልጅ ነህ አለ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ #በሰማያት ያለው #አባቴ እንጂ #ሥጋና #ደም ይህን #አልገለጠልህምና #ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።››ማቴ 16፡13-19 ቅዱስ ገብርኤልም እመቤታችንን ለማብሰር በተላከ ጊዜ ከእርሷ የሚወለደው <<ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ>> እንደሚባል ነግሯታል እሷም ይህንን በእምነት ተቀብላ ስግው ቃል/ሰው የሆነ አምላክ/ እግዚአብሄርን በስጋ ወልዳዋለች ስለዚህም ወላዲተ አምላክ ብለን እንጠራታለን፡፡ የሉቃስ ወንጌል 1፡35 ‹‹መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።›› ✧ በተለያየም ቦታ አጋንንት እኳን ሳይቀሩ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መስክረዋል፡፡ ማቴ 8፡29 አይሁድም የእምነታችን መሰረት የሆነውን የእግዚአብሔር ልጅነቱን አልተቀበሉም ነበር፡፡ማቴ 26፡63 ይዘብቱበትም ነበር ማቴ 27፡43 ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ወንጌሉን ሲጀምር እግዚአብሔር ልጅነቱን መስክሮ ነው ማር1፡1፡፡ በተለያየ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ክፍል ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ ተጠቅሷል ይህንንም እናመን ዘንድ ወንጌል እንደተፃፈ ይነግረናል ዮሐ 1፡34 ፤1፡50 ፤6፡69 ፤ 10፡36 ፤11፡4 ፤11፡27 ፤ 19፡7 ፤ 20፡31፡፡ ✧ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ይህንን አምኖ እንደተጠመቀ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ሐዋ 8፡37፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱም ኢሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ተናግሯል ‹‹ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።››1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡15፡፡ ↪ እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መጽሀፍቅዱስ አፅንኦት ሰጥቶ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በእግዚአብሔር ልጅነቱም ማመን እንዳለብን ይናገራል... ??? ለመሆኑ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባል ምን ማለት ነው ??? ✧ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ሲባል መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። እኛ የሰው ልጆች ሰዎች እንደምንባል ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስም እግዚአብሔር ተብሎ ይጠራል፡፡ ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ሲባል አብን በመልክ የሚመስለው በባህሪ የሚስተካከለው ማለታችን ነው ዮሐ 1፡1-3 ፤ ዮሐ 10 ፡30 ፤ዮሐ 14፡8-10 ‹‹እኔና አብ አንድ ነን እኔን ያየ አብን አይቷል››፡፡ ልጅነቱም የባህሪ ልጅነት ነው ማለትም ከማንም ያልተቀበለው ማንም የማይወስድበት ዘላለማዊ ልጅነት ነው፡፡ ✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአብ ልጅ እንደሆነ ከአብ ጋር አንድ እንደሆነ እና አብ የሚያደርገውን ሁሉ እንደሚያደርግ ለአይሁድ ሲነግራቸው ድንጋይ አንስተው ሊወግሩት በማሰባቸው ጌታችን ስለምን ትወግሩኛላቻሁ ባላቸው ጊዜ ስለመልካም ስራህ አንወግርህም ስለስድብህ ነው ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለማድረግህ ነው ማለታቸው በወንጌል ተመዝግቧል እንግዲህ አይሁድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ገብቷቸዋል ማለት ነው ዮሐ 10፡25-38 ✧ ከዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው ጌታችን ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ብሎ መጥራቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ነው/ ሙሉውን የአይሁድ እና የጌታን ንግግር አንብቡት/፡፡በሌላም ቦታ አይሁድ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎ ራሱን መጥራቱን ተቃውመው ሊገሉት እንደነበር የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ ማለቱ ደግሞ እግዚአብሔር ነኝ ማለቱ እንደሆነ ተረድተውት ሊገሉት እንደሚፈልጉ ተገልጧል ‹‹እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ << እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር።››ዮሐ 5፡18 ✧ ስናጠቃልለው ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ ተብሎ መጠራቱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተመለከትነው አምላክ/እግዚአብሔር መሆኑን የሚገልጥልን ልጅነቱም ከማንም ያልተቀበለው ባህሪ ልጅነት እንደሆነ እግዚአብሄርንም የሚስተካከልበት ልጅነት በመልክ ሚመስልበት ልጅነት እንደሆነ ልንረዳ ያስፈልጋል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር

'' ጥያቄ ስለሆነብኝ ነው እና እንድታብራሩልኝ ነው። እሱም... ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባልና እኛም ፍጡራን ደሞ የእግዚአብሔር ልጅ ስንባል ያለውን ልዩነት ብትነግሩኝ 🙏 ከዚህ በፊት ጽፋችሁ ከሆነ Reply አርጉልኝ'' ( ከቤቱ የተጠየቀ ) ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባል እርሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። የኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅነት የባሕርይ ነው። ማለትም አምላክነትን፣ ፈጣሪነትንና ሁሉን ቻይነትን ያመለክልታ። እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ቢባል አብ በዘመን አልቀደመውም። እኛ የእግዚአብሔር ልጅ ስንባልን ግን በጸጋ የተሰጠን ነው። ይህም እንደ ኢየሱስ ያለ የባሕርይ አምላክነትን አያሳይም። በጥመቀት ባገኘነው ጸጋ የእግዚአብሔር ልጆቹ እንሆናለን። ይህም የመንግስቱ ወራሾቹ ሆነን ማለት ነው።

መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ‹‹አንተ ወንድሜ! ዛሬ ከራጉኤል ቤት እናድራለን፤ እርሱም ዘመድህ ነው፤ አንዲት ልጅ አለችው፤ ስሟም ሣራ ይባላል፡፡ ሚስት ትሆንህ ዘንድ ስለ እርሷ እናገራለሁ›› አለው፡፡ ጦብያም ‹‹ያች ልጅ ከዚህ በፊት ሰባት ሰዎች እንዳገቧትና ሰባቱም ባገቧት ሌሊት ሞተው እንደሚያድሩ ስለሰማ ለእርሱ ለአላባቱና ለእናቱ አንድ በመሆኑ እርስዋን አግብቶ ከዚህ በፊት እንዳገቧት ሰዎች የሞተ እንደሆነ አባቱንና እናቱን የሚረዳቸው የለም፤ ቢሞቱም የሚቀብራቸው አያገኙምና እንደሚፈራ ነገረው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ግን ‹‹ከዘመዶችህ ሚስት ታገባ ዘንድ አባትህ ያዘዘህን ቃል አታስብምን? አሁንም አንተ ወንድሜ ስማኝ፤ የጋኔኑን ነገርስ አያሳዝንህ፤ በዚህች ሌሊት ከዘመዶችህ ወገን እርሷ ሚስት ሆና ትሰጥሃለችና፤ ወደ ጫጉላ ቤትም በገባህ ጊዜ የዕጣን ዕራሪ ወሰድ፤ ከዚህም ዓሣ ሐሞትና ከጉበቱና ከልቡ ጨምረህ አጢስበት፡፡ ጋኔኑም በሸተተው ጊዜ ይሸሻል፤ ለዘለዓለሙም አይመለስም፡፡ ወደ እርሷም በገባህም ጊዜ ሁለታችሁ ይቅር ባይ ወደ ሆነው እግዚአብሔር ጸልዩ፤ እርሱም ያድናችኋል፡፡ ይቅርም ይላችኋል፤ እንግዲህ አትፍራ፤ ከጥንት ጀምሮ እርሷን አዛጅግቶልሃልና፤ አንተም ታድናታለህ፤ እርሷም ጃንተ ጋር ትሄዳለች›› አለው፡፡ ጦብያም ይህንን ቃል በሰማ ጊዜ ደስ አለውና ከእርሷ በስተቀር ሌላ እንዳያገባ በሙሉ አሳቡ ወሰነ፡፡ ከራጉኤል ቤት እንደ ደረሱም ሣራ በደስታ ተቀበለቻቸው፤ የሣራ አባትም ጦብያን ገና እንዳየው ሚስቱ አድናን ‹‹ይህ ልጅ ድንቅ ነው፤ ከዘመዶች ወገን የሆነ ጦቢትን ይመስለዋል››አላት፤ ከዚያም ‹‹ወንድሞቻችን! እናንተ ከወዴት ናችሁ?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ወደ ነነዌ ከተማረኩት ከንፍታሌም ልጆች ሀገር ነን›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹ወንድሜ ጦቢትን ታውቅታላችሁን?›› በማለት ጠየቃቸው፡፡ ጦቢያም የአባቱ ስም ሲጠራ ‹‹እናውቀዋለን››፡፡ እርሱም ‹‹በሕይወት አለ?›› እነርሱም ‹‹አዎ፤ ደኅና ነው›› አሉት፤ ጦብያም ‹‹አባቴ ነው›› አለው፡፡ ከዚያ በኋላ ራጉኤል ተነሥቶ ሳመው፡፡ አድናም ሳመችውና ሁሉም ተያይዘው ተላቀሱ፡፡ ራጉኤልም በግ አርዶ አበላቸው፡፡ ራት ከበሉ በኋላም ጦብያ ቅዱስ ሩፋኤል በመንገድ የነገረውን ዐስቦ ቅዱስ ሩፋኤልን በመንገድ የነገርከውን እንዲፈጽምለት ሲለምነው ሰምቶ ስለ ልጅቷ መሆኑን ስለ ገባው ራጉኤል ጦብያን ‹‹አንድ ጊዜ ብላ፤ ጠጣ፤ ደስም ይበልህ፤ ልጄ ለአንተ ትገባለችና፥ አንተም ታገባታለህ›› አለው፡፡ ሣራ ካለችበት የጫጉላ ቤት አግብተው ዘጉት፡፡ ጦብያም ሣራን ኑሮዋቸው እንዲቃናና ጋብቻቸው እንዲባረክ አስቀድመው ወደ ፈጣሪያቸው ጸሎት እንዲያደርጉ አሳሰባት፤ አብረውም ጸሎት ካደረጉ በኋላም ያንን የያዘውንና የዓሣ ጉበትና ሐሞት ከዕጣን ጋር ጨምሮ ቢያጤስበት በሣራ አድሮ ባሎችዋን ይገድልባት የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ከሣራ ለቆ ወጥቶ ሄደ ሁለተኛም ሊመለስ አልቻለም፡፡ እነርሱም በሰላምና በጤና አደሩ፡፡ የጦብያንና የሣራን ጋብቻ የባረከ ቅዱስ ሩፋኤል ስለሆነ ‹‹መልአከ ከብካብ›› ይባላል፡፡ ከዚያ በኋላ የሰርጉ ቀን የሚሆን የ፲፬ ቀን በዓል እስኪፈጸም ድረስ ጦብያ ወደ ሀገሩ እሄዳለሁ ብሎ እንዳያውከው አማሎ ካቆየው በኋላ የሰርጉ በዓል ተፈጽሞ ጥሬ ገንዘብና የከብት ስጦታ አድርጐ መርቆ ወደ ሀገሩ ላከው፡፡ ወላጆቹ ጦቢትና አድና በመዘግየቱ ልጃቸው ክፋት አግኝቶት እንዳይሆን ስግተው ነበር፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ግን ሚስቱንና ግመሎቹን ይዞ ወደ እነርሱ ሲመጣ በክብርና በደስታ ተቀበሉት፡፡ የጦብያ አባት ጦቢትም ልጅህ መጣ ተብሎ ሲነገረው ዓይነ ሥውር በመሆኑ እርሱን ለመቀበል በሚሄድበት ጊዜ ወደቀ፤ ጦብያም የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ይዞ ስለ ነበር ወዲያው የአባቱን ዓይን ቀባው፤ የአባቱ ዓይኖቹም ተከፈቱ፡፡ ጦብያም ከዚህ በኋላ አብሮት ለነበረው ለመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል የድካሙን ዋጋ ሊከፍለው ሽቶ ገንዘብ ለመስጠት በጠሩት ጊዜ ጦቢትንና ጦብያን እንዲህ አላቸው፤ ‹‹ፈጣሪያችሁን አመስግኑ፤ እናንተ እስከ ዛሬ ድረስ ከየት እንደመጣሁ ማን እንደ ሆንኩ አላወቃችሁኝም፡፡ የእግዚአብሔር ምሥጢር ግን በክብር ሊገለጥ ይገባል እንጂ ሊሰውሩት ስለማይገባ የእኔን ተፈጥሮና ስም ልነግራችሁ እፈልጋለሁ፤ ተፈጥሮዬ መልአክ ነኝ፤ ሥራዬም የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ›› በማለት ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለት፡፡ የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡ ዳግምም በጳጉሜ ሦስትም ቅዱስ ሩፋኤልም በግብጽ ሀገር የምትገኘውን በአንድ ዓሣ አንበሬ ላይ የታነጸችውን ቤተ ክርስቲያኑን ዓሣ አንበሬው እንዳይገለብጣት ያጸናበትም የተአምር ዕለት ነው። በዚህ ዕለት ቀላያተ ምድር ሁሉ በመልአኩ በበትረ መስቀሉ ይባረካሉ። ስለዚህም ስለ እኛ ይማለድልን ዘንድ የበዓሉን መታሰቢያ ልናደርግ ይገባል፡፡ ምንጭ፤ መጽሐፈ ጦቢት፣ ድርሳነ ሩፋኤል፣ መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ጳጉሜ

ጳጉሜን 3 ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥሎ በሦስተኛ ደረጃ ሊቀ መላእክት የሆነው ቅዱስ ሩፋኤል የተሾመበትና የከበረበት ዕለት ነው! ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜⚜ ጳጉሜን 3 ቀን 2015 ዓ.ም (ጅማ፤ ኢትዮጵያ) @የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን!! በመላእክት ዓለም በነገድ ተከፍለውና በሊቀ መላእክት ሹመት ቅዱሳን መላእክት ፈጣሪያቸው እግዚአብሔርን እያመሰግኑ ዘወትር ያገለግላሉ፡፡ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክትም ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥሎ በሦስተኛ ደረጃ ሊቀ መላእክት የሆነው ቅዱስ ሩፋኤል የተሾመበትና የከበረበት ዕለት ጳጉሜ ሦስት ታላቅ በዓል ነው፡፡ በመጽሐፈ ስንክሳር እንደተጻው ሐዋርያት የቅዱስ ሩፋኤልን ክብሩን ያስረዳቸው ዘንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በለመኑበት ጊዜ ከሦስተኛው ዓለም ውስጥ የመላአክት አለቆች ቅዱስ ሚካኤልን ቅዱስ ገብርኤልን እና ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲመጡ አዘዛቸው፤ እነርሱም መጥተው በታላቅ ደስታ ለክብር ባለቤት ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰገዱ፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲህ አለው፤ ‹‹የክብርህን ገናናት የባልንጀሮችህንም ልዕልናቸውን እንዲያውቁ ለሐዋርያት ንገራቸው፡፡›› ያንጊዜም ለጌታችን ሰገደ፤ እንዲህም አላቸው፤ ‹‹ደገኛው የመላእክት አለቃ ሚካኤል ለሁሉም መላእክት አለቃቸው ነው፤ ስሙም ይቅር ባይ ይባላል፡፡ ሁለተኛም የመላክት አለቃ ገብርኤል ይባላል፤ የስሙም ትርጓሜ አገልጋይም ጌታም የሆነ የዓለሙ ሁሉ እመቤት የሆነች አምላክን የወለደች ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሠራት ነው፡፡ የእኔም ስሜ ሩፋኤል ነው፡፡ ይህም ደስ የሚያስኝ ቸር መሐሪ ቅን የዋህ ማለት ነው፡፡ እኔም ኃጢአተኞችን በእግዚአብሔር ዘንድ አልከሳቸውም፤ ከኃጢአት በንስሓ እስኪመለሱ ስለ ቅንነቴ በእነርሱ ላይ እታገሣለሁ እንጂ፤›› በሃያ ሦስቱ የመላእክት ነገደ ሠራዊት ላይ እግዚአብሔር የሾመኝ እኔ ሩፋኤል ነኝ፤ እግዚአብሔር አብን ይቅር ባይ ልጁን አጽናኝና አዳኝ የሆነ መንፈስ ቅዱስን እናመሰግነው ዘንድ፤ በደብረ ጽዮን በሚደረገው የሺህ ዓመት ተድላ ደስታ የክብር ጽዋን በሚሰጣቸው ጊዜ ለቅዱሳኖቹ በጎ ነገርን እንድንሰጣቸው ያዘዘኝ ሩፋኤል እኔ ነኝ፡፡ ደግሞም በዚህች ቀን ከዕፀ ሕይወት ዐጽቅ ወስጄ ለተመረጡ ክርስቲያኖች በእጄ እንድንሰጣቸው እግዚአብሔር ያዘዘኝ ሩፋኤል እኔ ነኝ፡፡የሰማያት መዛግብትም ከእጄ በታች ተጠብቀው የሚኖሩ እኔ ሩፋኤል ነኝ፡፡ እኔም እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ እከፍታቸዋለሁ፤ እዘጋቸዋለሁም፡፡ በምድር ሰው ባልንጀራው ስለ ስሜ በጎ ነገር ቢያደርግ እኔ ከመከራው በችግሩ ረዳዋለሁ፤ ወይም የሹመቴን ነገር የሚጽፍ ወይም ከቅዱሳን ጋራ ስሜን የሚያስብ ወይም በስሜ ለቊርባን የሚሆነውን የሚሰጥ ወይም በበዓሌ ቀን ምጽዋትን የሚሰጥ ይኸውም እግዚአብሔር በሊቃነ መላእክት ክብር የሾመኝ ያከበረኝ ጳጉሜን ሦስት ቀን ነው፡፡ ወደ ኢየሩሳሌም ሰማየዊት እስከማስጋበው በብርሃን ሠረገላ እኔ እሸከመዋለሁ፡፡ በምድር ላይ ከቶ እንደርሱ ያለ የማይገኝ መዐዛው እጀግ ጣፋጭ በሆነ ሽቱ ነፍሶቻቸው እርሱን በማሽተት ደስ እንዲላቸው አደርጋለሁ፡፡ ሐዋርያት ሆይ በእግዚአብሔር ፊት እስክትቆሙ እጠብቃችሁ ዘንድ ከእኔ ርዳታ ሹ፡፡›› የዚህ የመላእክት አለቃ የከበረ መልአክ ሩፋኤል ተአማራቶቹ ብዙ ናቸው፡፡ በተከበረች በጳጉሜን ሦስት የጦቢትን ዓይን ያበራና የራጉኤልን ልጅ ተቆራኝቷት ከነበረው ጋኔን ያላቀቃት ይህ መላእክ ነው፤ በመጽሐፈ ጦቢት ታሪኩ እንደተጻፈው በፋርስ ንጉሥ በስልምናሶር ዘመን የተማረከ ከነገደ ንፍታሌም የተወለደ ጦቢት የተበላ ጽኑዕ እሥራኤላዊ ነበር፡፡ እግዚአብሔር በስልምናሶር ፊት የመወደድን ግርማና ባለሟልነትን ስለ ሰጠው አለቃ አድርጎ የሾመና ለወገኖቹ ምጽዋት የሚሰጠት በጎ ሰው ነበር፡፡ ሐና ከምትባል ሚስቱም አንድ ልጅ ነበረው፡፡ ንጉሥ ስልምናሶር ከሞተ በኋላ ግን በሰናክሬም ዘመነ መንግሥት ከሹመቱ ስለሻረው ወደ ምድያም ምድር መሄድ አልቻለም፡፡ በዚያን ጊዜ ሣራ የምትባል ራጉኤል ልጅ አስማንድዮስ የሚባል ጋኔን አድሮ ያገባችውን ሰው ገደለባት፤ ሌላም ባል ብታገባ ሞተባት፤ እንደዚህ እየሆነ በጠቅላላ ሰባት ድረስ ያሉትን ባሎችን ገደለባት፡፡ የራጉኤል ልጅ ሣራ በዚህ ሁኔታ በኀዘን ተውጣ ስትኖር ጦቢት ሸምግሎ ስለ ነበር ልጁ ጦብያን ጠርቶ በዚህ ዓለም እስካለ ድረስ ሊሠራው የሚገባውን መንፈሳዊ ሥራ እንዲሠራ አጥብቆ ከመከረው በኋላ በመጨረሻ ልጁ የኑሮ ጓደኛህን እንዲፈልግ ከአብርሃም የይስሐቅና የያዕቆብ ዘሮች ወገን የሆነችውን እንዲያገባ ከዚህም ሌላ ከገባኤል ዘንድ በአደራ ያስቀመጠው ገንዘብ ስለነበር እርሱ በሕይወት እያለ ቢያመጣው እንደሚሻል ነገረው፡፡ ጦብያም ያባቱን ምክር ሁሉ በጽሞና ካዳመጠ በኋላ የነገርከውን ነገር ሁሉ እንደሚፈጽም ቃል ገባለት፤ ሆኖም ግን ከገባኤል ጋር ስላለው ገንዘብ ማምጣት ስለማይቻለው ሀገሩን አያውቀውና የአባቱን ርድታ ጠየቀ፡፡ በዚህ ጊዜ ጦቢት ልጁ ጦብያን አብሮት የሚሄድ ሰው እንዲልግ እና ደመወዝ አንደሚሰጠው ቢሆን ከእርሱ ጋር የሚሄድ አንድ ሰው ግድ እንደሚያሰፈልገውና ሄደው ሰው እንዲፈልግ ነገረው፡፡ ጦብያም አብሮት የሚሄደው ሰው ለመፈለግም በሄደ ጊዜ አንድ መልከ መልካም ጐበዝ ሰው አገኘ፤ ይኸውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ነበር፡፡ ነገር ግን መልአኩ መሆኑን ፈጽሞ አላወቀም ነበር፡፡ ጦብያም መልአኩን ሰው መስሎ እንዳገኘው ‹‹ሀገሩን ታውቅ እንደሆነ ወደ ሜዶን ክፍል ወደ ራጌስ ከእኔ ጋር መሄድ ትችላለህን?›› በማለት ጠየቀው፤ ቅዱስ ሩፋኤልም ‹‹ከአንተ ጋር እሄዳለሁ፤ መንገዱንም ዐውቀዋለሁ፤ በገባኤል ቤት ነበርሁ›› አለው፡፡ጦብያም መልሶ ከአባቱ ጋር ወስዶ ካስተዋወቀው በኋላ ጦቢትም ከወዴት እንደ መጣ ማን ተብሎ እንደሚጠራ ጠየቀው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልም ‹‹እኔስ የወንድምህ ታላቁ አናንያ ዘመድ አዛርያ ነኝ›› አለው፡፡ ጦቢትም የወንድሙ ዘመድ መሆኑን ከሰማ በኋላ ‹‹አንተስ ወንድሜ ደህና ነህን፤ ብሎ ሰለምታ ከሰጠው በኋላ የልጁን የጦብያን ነገር አደራ ሰጥቶ ስንቃቸውን አስይዞ ሸኛቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አዛርያስ (ቅዱስ ሩፋኤል) በመንገድ ይመራው ነበር፤ በዚህም መላኩ ‹መራኄ ፍኖት› (መንገድ መሪ ) ይባላል፡፡ እነርሱም ሲሄዱ ውለው ማታ ጤግሮስ ከተባለው ታላቅ ወንዝ ደረሱና ከዚያ ለማደር ተቀመጡ፡፡ ከዚያም ጦብያ ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረደና ልብሱን አውልቆ መታጠብ ሲጀምር አንድ ዓሣ ሊውጠው ከባሕር ወጣ፡፡ ወዲያውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ዓሣውንም እንዳይዘው ነገረው፤ ጦቢያም ዓሣውን ይዞ ወደ የብስ አወጣው፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡ ‹‹ዓሣውን እረደው፤ ልቡንና ጉበቱን፣ ሐሞቱን ያዝ፤ አጥብቀህ ጠብቅ›› አለው፡፡ ጦብያም መልአኩ እንዳዘዘው ዓሣውን አርዶ ሐሞቱንና ጉበቱን ያዘ፤ ሌላውን ሥጋውን ግን ጠብሰው ራታቸውን በሉት፡፡ ጦብያም ያንን የዓሣውን ጉበትና ሐሞት ለምን እንዲጠነቀቅለት ለመረዳት ‹‹አንተ ወንድሜ አዛሪያ! የዚህ ዓሣ ልቡ፥ ጉበቱና ሐሞቱ ለምንድን ነው?›› በማለት ጠየቀው፤ ቅዱስ ሩፋኤልም ‹‹ልቡና ጉበቱ የሚያሳምም ክፉ ጋኔን ያደረበት ቢኖር ወይም ርኩስ መንፈስ ያደረበት ቢኖር ያን ጊዜ ለዚያ በፊቱ ቢያጤሱለታል፤ ሴትም ብትሆን ያጤሱባታል፤ ከዚያም በኋላ አይታመሙም፡፡ ሐሞቱን ግን በዐይኑ ላይ ብልዝ ያለበትን ሰው ይሉኩታል፤ እርሱም ይድናል›› ብሎ መለሰለት፡፡ እንደዚህም እያሉ ሲነጋገሩ ከቆዩ በኋላ

🌸🌸🌸 “ወንድሞቼ! አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ከሙታን ተለይታ ተነሥታ ስታርግ አግኝቻታለሁ” (ቅዱስ ቶማስ) 🌸🌸🌸 ◈ ቅዱስ ቶማስም የያዘውን ያውቃልና ጸጥ ብሎ የቅዱስ ጴጥሮስን ተግሳጽ ሲሰማ ቆየ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ተቈጥቶ የእመቤታችንን ክቡር ሥጋ ለቅዱስ ቶማስ ለማሳየት ሔዶ መቃብሯን ቢከፍት የእመቤታችንን ሥጋ ሊያገኘው አልቻለም፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ደንግጦ ቆመ፡፡ ✥ ቅዱስ ቶማስም ‹‹ወንድሞቼ! አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ከሙታን ተለይታ ተነሥታ ስታርግ አግኝቻታለሁ›› ብሎ እመቤታችን የሰጠችውን ሰበን ለሐዋርያት ሰጥቷቸዋል፡፡ ይህ ሰበንም ሊቁ በመልክዓ ማርያም ድርሰቱ “ ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ፣ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘአሣበ ሤጡ ዕፁብ …እመቤቴ ማርያም ሆይ ዋጋው እጅግ ብዙ በሆነና መዓዛው በሚጣፍጥ ሽቱ በሐዋርያት እጅ ለተገነዘው ንጹሕ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡” እንዳለው ቅዱሳን ሐዋርያት ሞገሳቸውን እመቤታችንን ለመቅበር የገነዙበት ነበር፡፡ ◈ እነርሱም በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት እየተደሰቱ ሰበኑን ለበረከት ተካፍለውታል፡፡ በየሀገረ ስበከታቸውም ሕሙማንን ሲፈውሱበትና ገቢረ ተአምርሲያደርጉበት ኖረዋል፡፡ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስተምሩን በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆኑ በሚይዘው መስቀል ላይ የሚታሠረው መቀነት መሰል ልብስ፤ እንደዚሁም አባቶች ካህናት በመስቀላቸው ላይ የሚያደርጉት ቀጭን ልብስና በራሳቸው ላይ የሚጠመጥሙት ነጭ ሻሽ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው፤ቅዱሳን ሐዋርያት ለበረከት ተካፍለውታልና፡፡ 🌸 እኔም ቅዱስ ቶማስ ነኝ እመቤታችን በክብር ስታርግ በመንፈሳዊ ዓይን ዛሬ ላይ ሆኜ አይቻለሁ።

እጨጌ  በጥንቱ ዘመን ኢትዮጵያውያን ይጠቀሙበት የነበረው የቤተ ክርስቲያን የማዕረግ አይነት ነው። ከፓትሪያርኩ ዝቅ ብሎ ግን ከተቀሩት ጳጳሳት ከፍ ያለ ነበር። ትርጉሙ ሲብራራ፦ እጨጌ ከወላይትኛው ጨጋ (ጮጌ) የመጣ ሳይሆን መሠረቱ ከግእዙ ሐፄጌ የመጣ ነው፤ ሐጼጌ ማለት የምድር ጠባቂ ማለት ሲሆን በአማርኛ ዐጨ (አጨ) ዕጮኛ ጠባቂ፤ አጨጌ የሃገር ጠባቂ የገዳማትና የአድባራት ዋና ሹም አቡን ማለት ነው፡፡ የአጼው ሁለተኛ ረዳት (ከእቴጌ ቀጥሎ) ያለ ባለሲሶ ድርሻ የሆነ ሹም የሚሰጥ የማዕረግ ስም ነው፡፡ አጨ ጠበቀ፥ እጮኛ ጠባቂ፤ ጌ፦ ስፍራ ቦታ ሃገር፤ (እቴጌ እጨጌ ሰላምጌ ንብጌ ቅዱስጌ ደረስጌ አምባላጌ አሸንጌ ሐረርጌ ጉራጌ እጅጌ አንገትጌ ወገብጌ እራስጌ ግርጌ ወዘተ…) በተገናኘ ጊዜ እጨጌ፦ የሃገር ጠባቂ፥ ባለአደራ፥ ይምድር ዕጮኛ ማለት ነው፤ በግአዝ ሐጼጌ (ሐፄጌ) ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው፡፡ (የቋንቋዎች መወራረስ ቢኖርም እንደ አካባቢው ማይት ይቻላል ለምሳሌ በአራዳ ጮጋ ዝም ማለት እንዲሁም ጮጌ (ጨጋ) በወላይትኛ አባት ማለት ሲሆን፤ ጌ በክስታኒኛ ቤት ማለት ነው ሁሉም ከእጨጌ ጋር በድምጽ እንጂ በትርጉም አይገናኙም፡፡) ተወራራሽ ድምጾች፦ ሐጼ አጼ (ዐፄ) አጤ አጨ (ዐጨ)፡፡ እጨጌ የተሰኘው ማእረግ ይሰጥ የነበረው ከግብጻዊው ሊቀ ጳጳስ ቅጥሎ ያለ ትልቁ ሹመት ሲሆን፥ እጨጌ ሆኖ የሚሾመው አባት የደብረ ሊባኖስም ገዳም አበምኔትም ነበር፡፡ ከመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳስና ኋላም የመጀመሪያው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስና ሁለተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ እጨጌነትንም ደርበው ይዘው ነበር፡፡ በመጀመሪያው የሃገራችን የመደብ አብዮት ዘመን በመንግስት የተሰየመው የተሐድሶ ምክር ቤት እጨጌነቱን ከፓትርያሪኩ በመቀማት የመንግሥት ተወካይ የሆነው የቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እንዲሠራው በመወሰኑ ሦስተኛውና አራተኛው ፓትርያሪኮች እጨጌ አልነበሩም፡፡ በሁለተኛው የዘውግ አብዮት ዘመን ከመንግሥት የሚመደበው ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ በመቅረቱና ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመርጠው ሊቀ ጳጳስ ጠ/ሥራ አስኪያጅ እንዲሆን በመወሰኑ አምስተኛውና አሁን በመንበሩ ላይ ያሉት ፓትርያሪክ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመሰኘት የእጨጌነትን መንበር የመሠረቱት ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም የስያሜው አካል ሆነዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ እጨጌነት የፓትርያሪኩ ሥልጣን ስለሆነ የደብረ ሊባኖስ አበምኔት ጸባቴ ተብሎ ይጠራል፡፡ ምንጭ፦ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፡፡ ዐዲስ የአማርኛ መዝገበ ቃላት፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፡፡ (ል.ሣ.)

#ጵጵስና ከክርስቶስ በክርስቶስ በትክክለኛው ሥርአትና መንገድ የሚሰጥ መንፈሳዊ ስልጣን እንጂ እንደ ችርቻሮ ዘይት በየቦታው የሚሰጥ ተራ ነገር አይደለም። አንድ መንበር - መንበረ ተክለሃይማኖት አንድ
#ጵጵስና ከክርስቶስ በክርስቶስ በትክክለኛው ሥርአትና መንገድ የሚሰጥ መንፈሳዊ ስልጣን እንጂ እንደ ችርቻሮ ዘይት በየቦታው የሚሰጥ ተራ ነገር አይደለም። አንድ መንበር - መንበረ ተክለሃይማኖት አንድ ሲኖዶስ አንድ ፓትርያርክ

➗➗➗#እንደ_ቁራ_ጠቁረው_አየኋቸው➗➗➗ የመጀመሪያው መነኩሴ እንጦንስ ነው። እንጦንስን ጌታ አመንኩሶ ቆብ ሰጥቶታል። ከዚያ በኋላ እንጦንስ አባ መቃርስን አመንኩሶታል። ይህ እንዲህ እያለ ምንኩስና ተስፋፍቶ አሁን ከዚህ ደርሷል። አባ እንጦንስ አባ ጳውሊን ሊጠይቀው በሔደ ጊዜ አባ ጳውሊን ፦ "እስኪ ይህ ሥርዓተ ምንኩስና ከእኔ በኋላ ይቀራል ወይስ ይቀጥላል የሚለውን ከእግዚአብሔር ጠይቅልኝ?" አለው። አባ ጳውሊም በጸሎት እግዚአብሔርን ጠየቀለት፡ ከጸሎቱ በኋላ የአባ ጳውሊ ገጽ በደስታ ተመላ። አባ እንጦንስም ፦ "ምን አየህ?" ብሎ ጠየቀው:: አባ ጳውሊም "ነጫጭ ርግቦች አንተ እየመራኻቸው በጠፈር ላይ ሲሔዱ አየሁ" አለው። አባ እንጦንስም ፦ "ምንድን ናቸው? ሲል ጠየቀው። "በቆብ የምትወልዳቸው ንጹሐን ጻድቃን መነኮሳት ናቸው" አለው። አባ እንጦንስም ፦ "እስኪ ደግመህ አመልክትልኝ" ብሎ ለመነው በድጋሚ ሲጸልይ የአባ ጳውሊ ፊቱ በሐዘን ተመላ። "ምነው?" ሲል አባ እንጦንስ አባ ጳውሊን ጠየቀው:: "በክንፋቸው ላይ ጥቁር መልክ የተቀላቀለባቸውን ርግቦች አየሁ" አለው። "እነዚህ ደግሞ ምንድን ናቸው?" ሲል አባ እንጦንስ ጠየቀ። "ጽድቅና ኃጢኣት እየቀላቀሉ የሚሠሩ መነኮስት ናቸው" አለው:: "እስኪ ለሦስተኛ ጊዜ አመልክትልኝ" አለና ለመነው:: አባ ጳውሊም ጸለየለት። በዚህ ጊዜ አባ ጳውሊ ድምፁን ከፍ አድርጐ ጮኾ አለቀሰ፡፡ አባ እንጦንስም ፦ "ምነው ምን ሆንክ?" አለው። "እንደ ቁራ ጠቁረው አየኋቸው" ሲል መለሰለት። "ምንድን ናቸው?" ቢለው "ሹመት ፈላጊዎች ፣ ገንዘብ ወዳጆች ፣ በጠዋቱ ከመኳንንቱ ጋር ለማዕድ የሚቀመጡ ፣ በፍጻሜ ዘመን የሚነሡ ኃጥኣን መነኮሳት ናቸው።" አለው። አባ እንጦንስም ፦ "ንስሐ ሳይገቡ በሞት እንዳይወስዳቸው እስኪ እግዚአብሔርን ለምንልኝ" አለው። የዚህ መልስ ግን ከአባ ጳውሊ አልመጣለትም። ዽዽስና ማለት የክርስቶስን መንጋ እንደ ባለቤቱ አድርጐ መጠበቅ ማለት ነው:: ሥልጣኑ በምድር 'ሸክም: ዕዳ' ሲሆን በሰማይ ግን 'ክብር' ነው:: ማንም በሥጋው ላይ ካልጨከነ በቀር ዽዽስናን አይመኝም:: +ቅዱስ ዻውሎስ "ሠናየ ግብረ ፈተወ-ማንም ዽዽስናን ቢመኝ መልካም ሥራን ተመኘ" (1ጢሞ. 3:1) ማለቱን ይዞ 'ሹሙኝ' ማለት ወደ ማይጠፋ እሳት የሚያስጥል ከባድ ውሳኔ ነው:: ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን የሚጠየቅ በራሱ ኃጢአት ሲሆን አንድ ካህን ደግሞ ስለ ልጆቹ ይጠየቃል:: የከፋው ግን የዻዻሱ ነው:: +አንድ ዻዻስ ቢጾም ቢጸልይም እንኳ ለድኅነቱ በቂ አይደለም:: ምክንያቱም በመንበሩ ላይ ያስቀመጠው መንጋውን እንጂ ራሱን እንዲያድን አይደለምና:: ጌታ እንዳለ መልካም እረኛ "ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግኢሁ-መልካሙ እረኛ ስለ በጐቹ ቤዛ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ ነው::" (ዮሐ. 10) ስለዚህም ክህነት / ዽዽስና ሐዋርያዊ አገልግሎት ከባድም ኃላፊነት ነው:: † † † ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አባቴ