en
Feedback
Nova'

Nova'

Open in Telegram

ከባርነት ነፃነት ትከብዳለች። ብዙዎች ነፃነትን ሽጠው እስትንፋስ ይገዛሉ። እኔ ግን እስትንፋሴን በነፃነት እለውጣታለሁ። !

Show more
526
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1730 days
Posts Archive
Let's get fun guys ዛሬ ምሽቱ ደመቅ ይላል። ቫዮሊን ካለ ደግሞ ይበልጥ ያምራል። ም

ሚስቴ መቼ ነው እንደዚ ምትለኝ😭
ሚስቴ መቼ ነው እንደዚ ምትለኝ😭

ሃይማኖተኞች ከገንዘብ እና ከወሲብ ጋር ያላቸው ችግር ምንድነው? በአፋቸው ገንዘብ እና ወሲብ ይራገማሉ... ቁጥር አንድ ሌባ እና ልክስክስ ግን እነሱ ናቸው። ኤቲስት እኮ የራሱ የሞራል ሕግ አለው። ሃይማኖተኛ ግን ካላየኸው ውሻ ያስንቃል🥵 ኧረ ያሳፍራል..

Boss💙 ታላቁ ክለባችን ሊቨርፑል ሦስተኛ ሆኖ ጨርሷል! ከዚህ በላይ ይገባን ነበር ጥቂት ስህተቶች ዋጋ አስከፍለውናል። አሁን የምናዝነው ግን ዋንጫውን በማጣታችን ሳይሆን ታላቁን አሰልጣኛችንን የር
+1
Boss💙 ታላቁ ክለባችን ሊቨርፑል ሦስተኛ ሆኖ ጨርሷል! ከዚህ በላይ ይገባን ነበር ጥቂት ስህተቶች ዋጋ አስከፍለውናል። አሁን የምናዝነው ግን ዋንጫውን በማጣታችን ሳይሆን ታላቁን አሰልጣኛችንን የርገን ክሎፕ በመሰናበታችን ነው። YNWA Jurgen kloop. You make our dream real. You gave us good days. Kloop💙

እናት ሀገር ጃፓን እዚህ ሀገሬ ላይ መጥቶ ሴቶቻችን ከክቶ ላስወለደ 75,000 ዶላር እከፍላለሁ እያለች ትገኛለች የምትፈልገውም ወንድ ከአፍሪካ ብቻ ነው 😳 ሲንግል የሆናችሁ ጃፓን ኢምባሲ እየሄዳችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ ወላሂ ቀልዴን አይደለም ። "እኛ ባለትዳሮችን አይመለከትም"🙌

Promotion 🚸 በ Online ገንዘብ መስራት ትፈልጋላችሁ? በኢንተርኔት Dollar መሰብሰብ ይቻላል። ኑ እንስራ! 👇 https://t.me/+ZnOnMaiioXA2OGNk https://t.me/+ZnOnMaiioXA2OGNk

ታራስ ቡልባ ~ Taras Bulba ደራሲ - Nikolai Googol ተርጓሚ - ጋሽ በካፋ ሀይለየሱስ ዘውግ - ልብወለድ ( ታሪክ ቀመስ ) የህትመት ዘመን - 1976 እ.ኢ.አ የገፅ ብዛት - 192 ከ BBC የምንጊዜም ምርጥ 100 ክላሲኮች መካከል 56ኛው !! አዘጋጅ  @OLDBOOKSPDF አቅራቢ @ETHIO_PDF_BOOKS1

የመጽሐፍ ዳሰሳ መጽሐፍ 2 ታራስ ቡልባ : ኒኮላይ ጎጎል በዛሬው የመጽሐፍ ዳሰሳ በኒኮላይ ጎጎል የተጻፈው እና በጋሽ በካፋ ሃ/ ኢየሱስ ወደ አማርኛ በተተረጐመው ታራስ ቡልባ መጽሐፍ ላይ እናተኩራለን። ታራስ ቡልባ በ17 ኛው ክ/ ዘመን በኡክሬይን ( Ukraine ) ሀገር የነበረ የሁለት ልጆች አባት ነው። በዘመኑ ኡክሬን በፖላንድ ገዥዎች ስር ትተዳደር ነበር። በወቅቱ የኡክሬን - ሩስያውያን ለነፃነታቸው ከፖላንድ ሀገረ መንግሥት ጋር እየተፋለሙ ነበር። ብዙ የኡክሬን ዜጎች ሀገራቸውን ከጠላት ለመጠበቅ ሲሉ በኡክሬን ሰፋፊ ሜዳዎች ላይ ወድቀው ቀርተዋል። "ታራስ ቡልባ" የታሪኩ ባለቤት የሆነ ኡክሬናዊ አባት ነው። እንደ ሌሎች የኡክሬን ዜጎች ሁሉ በፖላንድ ስር የመተዳደር ፍላጎት የለውም። ታራስ ቡልባ በነበረበት ዘመን ኡክሬን በፖላንድ ወራሪዎች ብቻ አልነበረም ነፃነቷ የተደፈረው። በቱርኮች፣ በታታሮች እና በካቶሊክ ሮማውያን ነበር ተደጋጋሚ ጥቃት ይደርስባት የነበረው። በተፈጥሮ እልኸኝነት እና ቁጡነት የሚንፀባረቅባቸው ኡክሬናውያን ለፖላንድ ከመገዛት፣ በቱርክ ከመዘረፍ እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸውን ወደ ካቶሊክ ለውጠው ከመኖር ይልቅ ... የሩስያ - ኡክሬናዊነታቸውን እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸውን አጥብቀው የአርበኝነት ትግል ማድረግን መርጠዋል። በደቡባዊ ኡክሬን የሚገኘው " ዛፖሮዥያን ሴጅ " የተሰኘው ወታደራዊ ካምፕ የነፃነት ታጋዮቹ ታላቁ የጦር መነሃሪያ መሆን ችሎ ነበር። ዛፖሮዥያን ሴጅ ውስጥ ጦሩ ይመክራል፣ ይሰባሰባል፣ ይጨፍራል፣ ሰይፍ መዞ ይነሳል፣ መሪውን መርጦ ይሽራል። በአጠቃላይ ዛፖሮዥያን ሴጅ የኡክሬን የነፃነት ታጋዮች ዋና የጦር ካምፕ መሆን ችሎ ነበር። በአጠቃላይ በመጽሐፉ ውስጥ የታሪኩ ባለቤት "ታራስ ቡልባ" ከሁለት ልጆቹ ጋር በመሆን የሰራው ጀብዱ፣ ኡክሬናውያን ለነፃነታቸው የከፈሉት ዋጋ፣ መስዋዕትነት፣ ጦረኝነት፣ ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሲባል የተከፈለ ሃይማኖታዊ መስዋዕትነት እንዲሁም የ17 ኛው ክ/ ዘመን አውሮጳ ምን ትመስላለች የሚለውን እንድንቃኝ ይረዳናል። ደራሲው ኒኮላይ ጎጎል በታሪካዊ ልቦለድነት የጻፈው ይህ ድንቅ መጽሐፍ በምናብ ባሕር ከኡክሬን ሜዳማ ምድር ላይ አስቀምጦ ከዛፖሮዥያን ሴጅ ጀግንነት ... ከታራስ ቡልባ መንፈስ ውስጥ የሚከት ነው። እጅግ ወድጄዋለሁ ፤ ብታነቡት ታተርፋላችሁ። pdf ከስር ይለቀቃል። Nova.

ጠቢቡ ሰሎሞን በመጽሐፈ መክብብ ስለ ሕይወት ይሰብካል። በኢየሩሳሌም ጎዳናዎች ላይ "... ከፀሓይ በታች የተሠራውን ሥራ ዅሉ አየኹ እንሆም፥ዅሉ ከንቱ ነው፥ነፋስንም እንደ መከተል ነው።..." እያለ ይጮሃል። "... ከፀሓይ በታች በሚደክምበት ድካም ዅሉ የሰው ትርፉ ምንድር ነው፧..." ብሎ ይጠይቃል። ሰሎሞን በጥበቡ የደረበት ምስጢር ... የህይወትን ከንቱነት ነው። የአልጄሪያው ታላቅ ፈላስፋ አልበርት ካሙስ ... የጠቢቡን ሐሳብ ይጋራል። አልበርት ካሙስ ዕድሜያችንን በሙሉ ከሕልውና ከንቱነት ጋር ስንጋፈጥ እንኖራለን ... በተጋፈጥንም ቁጥር እየሸሸን ከራሳችን ጥያቄ እየተደበቅን ዕድሜያችንን እናሳልፋለን ብሎ ያምናል። ካሙስ  ይልቁንም የመኖርን ከንቱነት በመቀበል እና በውስጡም ትርጉምና ዋጋ የማግኘትን አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥቷል። እንደ አልበርት ካሙስ ፍልስፍናዊ እሳቤ ከሆነ ሕይወት ትርጉም አልባ ናት። ቢሆንም እኛ የራሳችንን የህይወት ትርጉም እየሰጠን... የሕይወትን ከንቱነትን ማስወገድ ባንችልም እንኳን ከንቱነትን መርሳት አለብን። ራሳችን ለሕይወት በሰጠናት ትርጉም የህይወት እርካታን እና ዓላማ ማግኘት እንችላለን። በመጨረሻም በጠቢቡ ይሁዲ ቃል እንዝጋ "... በጥበብ መብዛት ትካዜ ይበዛልና ዕውቀትንም የሚጨምር ሐዘንን ይጨምራልና።.." Nova

ወንጀል_እና_ቅጣት_ፊዮደር_ደስቶየቭስኪ_ተርጓሚዎች.pdf18.10 MB

በወንጀል እና ቅጣት መጽሐፍ ላይ ፊዮዶር ደስታየቪስኪ የታሪኩ ማዕከል ያደረገው ፍልስፍናዊ እሳቤ ምን ይመስላል? የመጽሐፉ ዋና ገጸ ባህሪይ " ራስልኒኮቭ " በታላላቅ እና በተራው ሕዝብ መካከል ያለውን ልዩነት መገንዘብ ችሏል። ተራው ሕዝብ የሕግ ቀንበር ተሸክሞ የሚኖር ... ከሕግም የማፈንገጥ ፍላጎት የሌለው በተጻፉም ሆነ ባልተፃፉ መርሆዎች ላይ ራሱን በራሱ ያሰረ ነው። እነዚያን ህጎች ተላልፎ ቢገኝ ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል። ህሊናውም ረፍት ይነሳዋል። በአንፃሩ ልዩ ሰዎች ( ታላላቅ ሰዎች ) ዓለም ታሪካቸውን የሚያነሳላቸው ጀግኖች ናቸው። ከሕግ እና ሥርዓት ይልቅ ዓላማቸውን ያስበልጣሉ። ታላላቅ መሪዎች እና የጦር ጄኔራሎች እልፍ አዕላፋትን የገደሉ እና ያስገደሉ ናቸው። ከሚገድሉት የሰው ፍጥረት ይልቅ በአዕምሮዋቸው ያስቀመጡት ዓላማ ይበልጥባቸዋል። ህሊናቸውን ደፍነው ዓላማቸውን መሳካት ከቻሉ ... ዓለም ለስማቸው ይዘምራል። የታሪኩ ባለቤት ናፖሊዮን ቦናፓርትን መሆን ተመኝቶ ነበር። ዋጋ ቢስ ናት ብሎ በገመታት ሴት ላይም እጁን አንስቷል። ከባዱ ነገር ግን ወንጀል መፈጸም ሳይሆን ከራሱ የህሊና ድምፅ ማምለጥ ሆኖ አግኝቶታል። የገዛ ህሊናው አሰቃይቶታል። የገዛ ህሊናው ተሸናፊ አድርጎታል። መግደል ችሏል አዕምሮውን ግን ዝም ማሰኘት አልቻለም። በመጨረሻ በፍትህ እግር ስር ወድቋል። ይህ መጽሐፍ ከፅሁፉ ውበት አንስቶ እስከ ታሪኩ ጥልቀት እፁብ ነው።ፍልስፍናዊ እሳቤው እጅግ የሚደነቅ ነው። ብታነቡት ትጠቅማላችሁ! Pdf ከስር ይለቀቃል!

መፅሀፍ 1 " ወንጀል እና ቅጣት " ደራሲ:- ፊዮዶር ደስታየቪስኪ ደራሲው በሩስያ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ስሙ ከማንም ቀድሞ ይነሳል። የእርሱ መጽሐፍ ያልደረሰበት የዓለም ጫፍ የለም። የትም ቦታ ሄዳችሁ ፊዮዶር ደስታየቪስኪ ብትሉ እሱን የሚያውቅ ሰው ማግኘታችሁ አይቀርም። ታዋቂ እና ተነባቢ ያደረገው ምንድን ነው? የሥነ ጽሑፍ ውበቱ እፁብ ነው። ፍልስፍናዊ እሳቤው ጥልቅ ነው። ምስል ከሳች እና በስሜት የታሪኩ አካል የሚያደርግ መንፈስ አለው። ደስታየቪስኪ Realistic ደራሲ ነው። የልቡን ፍላጎት በገጸ ባህሪዎቹ ላይ ከመጫን ይልቅ የዓለምን እውነታ እንዲኖሩ ያደርጋቸዋል። ከደስታየቪሰኪ መጽሐፍት መካከል የሆነው ወንጀል እና ቅጣት ( Crime and punishment ) ... ታሪኩ አንድ የዩንቨርሲቲ ተማሪ የነበረ ወጣት እና በእርሱ ዙሪያ ባሉ ግለሰቦች ላይ የሚያጠነጥን ነው። ዋናው የታሪኩ ባለቤት " ራስልኒኮቭ " ተብሎ የተጠቀሰ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረ ወጣት ነው። ቤተሰቦቹ ባሉበት ድህነት የተነሳ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ከሁለት ዓመት በላይ መቀጠል አልቻለም። በዕዳ የተዋጠ ወጣት ነው። የገንዘብ ማጣት ሕይወቱን አክብዶበታል። ከእርሱ አልፎ እናቱ እና እህቱ አደጋ ላይ ናቸው። እህቱ ቤተሰቧን ከድህነት ለመታደግ ስትል ከማትወደው ሰው ጋር ትዳር ለማሰር ቃል ተገባብታለች። ወጣቱ የእርሱንም የቤተሰቡንም ሕይወት ለመቀየር ጥቂት ገንዘብ ማግኘት በቂው ነው። ያንን ገንዘብ ለማግኘት ለወራት ያህል በአዕምሮው የተመላለሰበት መንገድ ከአራጣ አበዳሪዋ መዝረፍ ነው። ከዚያች ክፉ እና ተንኮለኛ አራጣ አበዳሪ አሮጊት መዝረፉ ቀላል ስለማይሆን ከዘረፋው አስቀድሞ አሮጊቷን መግደል አለበት። ፍዮዶር ደስታየቪስኪ ወንጀልን በተመለከተ በቀደመ ድርሰቱ የሚከተለውን ሃሳብ ያነሳል። "... አንድ ወንጀለኛ ብዙም የዓላማ ጽናት የለውም። ጤናማ አዕምሮም ይዟል ማለት አይቻልም። ስለሆነም ነው በአዕምሮው የሚመላለሰው አሳፋሪ ሃሳብ ወደ እኩይ ተግባር በፍጥነት የሚመራው። ወንጀለኛው ወንጀሉን እንደፈፀመ ወዲያውኑ የፀፀት ስሜት በልቡ ይናኛል። የሚሞተውም ወንጀሉን በመፈጸሙ ሳይሆን ፤ ሰው የሚያሰኘውን በውስጡ ያዘለውን የራሱን ምርጥ ባህሪ በማውደሙ ነው።..." ወንጀል እና ቅጣት የሚዳስሰው ... ጥቂት ገንዘብ ለማግኘት ሲል በተጨማሪም እንደርሱ ላሉት ምንዱባን ውለታ ለመስራት ሲል በጭካኔ አንድ አራጣ አበዳሪ ክፉ አሮጊት የገደለ ወጣት ወንጀሉን ለማዳፈን በማሰብ ሌላ ምስኪን ለፍቶ አዳሪ ሴት ላይ የግድያ በትሩን በመዘርጋቱ... የሚደርስበትን የህሊና ቅጣት ላይ የሚያተኩር ነው። በመጽሐፉ ላይ የህሊና ቅጣት፣ ጓደኝነት፣ ወንጀልን በተመለከተ ፍልስፍናዊ እሳቤዎች፣ ህመም፣ ሱስ፣ ለቤተሰብ የሚከፈል ዋጋ ይዳስሳል። በመጨረሻም የፍትህን ታላቅነት ይሰብካል። የድሃ ሰዎች አስከፊ ሕይወት ከአስከፊ ሞት ጋር በመጽሐፉ ያስገነዝበናል። ገንዘብ ሃይል የሆነበት ዓለም በድሃ ሰዎች ላይ የሚያሳርፈው የጭካኔ በትር ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ቦታው ላይ ያለን እስኪመስለን... በስሜት እስክንፈተን ድረስ ያሳየናል።

ጓዶች ከዚህ በኋላ በሳምንት አንድ ወይ ሁለት ቀን የመጽሐፍ ዳሰሳ ይኖረናል። የምዳስሰውን መጽሐፍ በpdf እጋብዛችኋለሁ! ዘላንነቱን ትተን ዕውቀትን ከቀደሙት አዋቂዎች እንማር!

መንግስት አሁንም ድራማ እየሰራ ይለቃል ግን ለዛ አዋርድ ላይ ሲታጭም ሲያሸንፍም ሰምቼ አላውቅም! ምናልባት የለዛ ቢሶች አዋርድ ሲጀመር ጠራርጎ ይበላው ይሆን?! ማን ያውቃል! Copied from Fb

" ... ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰማኋቸው። እኔ በግንቡ በአንደኛው በኩል ስሆን እነሱ ደግሞ በሌላኛው አቅጣጫ ናቸው። አንድ ጋት የማይሞላ ውፍረት ያለው ጭቃና እንጨት ብቻ ይለያየናል። ንግግራቸው ጭካኔ የሚያንፀባርቅበትና ለግድያ ቆርጠው መነሳታቸውን የሚያሳይ ነው። እዚህ ነች ... እዚህ የሆነ ሥፍራ እንዳለች እናውቃለን። ፈልጓት ... ፈልጓት ... ልጅቷን ፈልጓት እንግደላት። አካባቢው በሁካታ ተሞላ። ብዙ ገዳዮች መጥተዋል። በአይምሮዬ ይታዩኛል። ሁልጊዜ በፍቅር እና በደግነት ሰላምታ ይሰጡኝ የነበሩ የቀድሞ ጎረቤቶቼ እና ወዳጆቼ በቤቱ ውስጥ ጦርና ገጀራ ይዘው ሰሜን እየጠሩ ይዘዋወራሉ።..." " 399 በረሮ ቱትሲዎችን ገድያለሁ።" ይላል አንዱ ገዳይ። " ኢማኪዩሌ 400ኛ ሟች ትሆነኛለች። ይህን ያህል ሰው ከገደልኩ ምን እፈልጋለሁ።" ሁቱትሲ : ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ይህ መፅሀፍ የእውነት ድንቅ ነው። የሰው ልጅ ምን ያህል ክፉ መሆን እንደሚችል ቦታው ላይ ሆናችሁ ታዩበታላችሁ። ምን ያህል ደግ መሆን እንደሚችልም ትገነዘባላችሁ። ከሁሉም በላይ ክፋት እና ደግነት ከልብ ይልቅ ከአዕምሮ ለመመንጨት ቅርብ ሆነው ታገኟቸዋላችሁ።

የፍልስጤም የነፃነትና ፍትህ ጥያቄ.pdf9.14 MB

ማልከም ኤክስ - ሙሉቀን ታሪኩ.pdf17.42 MB

የብልህነት_መንገድ_ግሬሺያን_ባልታሳር.pdf20.63 MB

ሁቱ ትሲ.pdf1.75 MB

የመኖር ክህሎት - ዴል ካርኒጌ [@zionbook].pdf21.77 MB