VECOD GLOBAL LEADERS
Open in Telegram
Vision Ethiopian Congress for Democracy Official Channel VECOD GLOBAL LEADERS. Contact Us:0911605873
Show more1 824
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+1030 days
Posts Archive
1 824
Vision Ethiopian Congress for Democracy (VECOD) would like to wish you and your beloved family a HAPPY ETHIOPIAN NEW YEEAR !!!
1 824
የሰው ልጅ በማንነቱ ብቻ ከአልማዝ ይልቅ እንቁ ነው!
❖ የሰው ልጅ በማንነቱ ብቻ ከአልማዝ ይልቅ እንቁ ነው፡፡
❖ በዓለም ላይ አንተን መሳይ ለማግኘት በባህር፣ በውቅያኖስ፣ በምድርም፣ ከምድርም በታች፣ በሰማይም ሁሉ ቢፈለግ ከቶ አይገኝም፡፡ አንተነትህ ያለው አንተ ጋር ብቻ ነው፡፡ ውበትህም በራሱ እጅግ ልዩ ነው፡፡
❖ ለዚህ ዓለም የምትሰጠው ጥቅም እንደ ልዩ ማንነትህ መጠን ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
29/12/2017
1 824
ወቅትህን ለይተህ እወቅ የመማር እና የማዳመጥ ጊዜህን በመታየትና በመናገር ጊዜህን አትፍጀው።
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
29/12/2017
1 824
ባለማስተዋላችን ነው እንጂ ሳያስተምረን የሚያልፍ አንድም ቀን የለም።
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
29/12/2017
1 824
ራስን ማወቅ ራስን ለመምራት መሰረት ነው፡፡
❖ ወደ ምድር የመጣኸው ሌሎችን ለማዳመቅ አይደለም! እምቅ ችሎታህን ለይ! በእግሮችህ ሩጥ! በአእምሮህ አስብ! በጆችህ ሥራ! በእግዚአብሔርታመን! ያን ጊዜ ድሉ ያንተ ይሆናል::
❖ በሕይወት ውስጥ የምትመኘውን ሃሳብ ሁሉ መሆን በፍፁም የማይቻል ነገር ነው፡፡
❖ ወደዚች ምድር የመጣኸው አሯሯጭ ወይም አጨብጫቢ እንድትሆን አይደለም፡፡ ሩጫው ተጀምሯል፡፡ በአንተ ውስጥ እግዚአብሔር ታላቅ ዓላማ አለው፡፡ ተነስተህ ሩጥ፤ ድሉ ያንተ ነው፡፡
❖ በዓላማ የሚሮጥ መስመሩን ያውቃል በመስመሩም ይሮጣል፡፡
❖ አሸናፊነት የዘር፣ የቀለም እና የፆታ ጉዳይ ሳይሆን ራስን አውቆ፤ ራስን ሆኖ እንዲሁም ራስን ገዝቶ፤ ራዕይን ከወደ ፍፃሜው ማድረስ ነው፡፡
❖ ሰው የራሱን ትክከለኛ ማንነት በማወቁ ራሱንም ሳይጎዳ ሌሎቹንም ሳይረብሽ ሥርዓትና ዓላማ ያለው ኑሮ እንዲኖር ይረዳዋል፡፡
❖ ራስን የማወቅ ችሎታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የሚሄድ እንጂ በውልደት የሚገኝ አይደለም፡፡
❖ ሰው ማለት ከሌላ ፕላኔት የሚመጣ አዲስ ፍጡር አይደለም፤ አንተው ::
❖ የሰው ማንነቱ የሚመዘነው ስሜቱን፣ እውቀቱን እና ፍቃዱን በመጠቀሙ ነው፡፡
❖ ራስን ማወቅ ስነ-ሥርአት ያለውን ሕይወት በዓላማ እንድንኖር ያደርጋል፡፡
❖ ራስን ማወቅ ባለሙሉ አቅም ያደርጋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
21/12/2017
1 824
ከውድቀት ተነስተክ ድጋሜ ለመጀመር አትፍራ አሁን ከምንም ሳይሆን ከልምድ ነው የምትጀምርው!
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
21/12/2017
1 824
ጀበና ቢነገፍል እራሱን ነው የሚያበላሸው እንዲሁም የሚያቆሸሸው። ህይወትን ሁሌ በብስጭት ብታማርራት የሚጎዳህ እራስህን ነው!
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
21/12/2017
1 824
❗️❗️❗️Job Vacancy: Finance Officer
We are seeking a qualified Finance Officer to join VECOD.
Requirements:
• Bachelor's degree in Accounting
• Minimum of 1 year of relevant work experience
• Proficiency in computer skills
• Both English and Amharic skills are required
For more details, please refer to the attached document.
If you have any questions, feel free to contact us at 0911-605-873.
August 20, 2025
1 824
አንተም ሰው ነህ!
❖ የሰው ልጅ በምድር ከማንም በላይ በአካላዊ ማንነቱ ውስብስብ ፍጡርና በአቅሙም ኃያል ነው፡፡ አንተም ሰው ነህ!
❖ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ትንሽ ብርሃን ብትገኝ ለአካባቢው ተስፋን እንደምትለግስ ሁሉ _ አንተም በስፍራህ ተገኝተህ በመልካም ሥራህ ብርሃንህን ማሳየትህ ለሌሎች የሕይወትን ተስፋን ታጎናጽፍበታለህ፡፡
❖ የጨው መገኛዋ በማንኛውም ሰው ቤት ነው፡፡ ጥቅሟም ራስዋን መስዋእት በማድረግ ጣእም እና ፈውስን መስጠት ነው፡፡ አንተ ጎበዝ ለዚህ ዓለም በተለይም አሁን ላለህበት ቦታ ጣእምና ፈውስን እንድትሰጥ ነው የተፈጠርኸው ፡፡
❖ ምንም ፀሐይ ብትደምቅ፤ ጨረቃና ከዋክብትም ቢያሸበርቁ፤ ለሰውነት የዓይን ብርሃን ከሌለው ሁሌም በጨለማ እንደሚጓዝ ሁሉ፥ ሰው በምድርሲኖር ለሕይወቱ ራዕይ ከሌለው ሁልጊዜ በጨለማ እንደሚጓዝ ነው።
❖ በምድር የመኖር የሕይወት ዓላማ ለተፈጠሩለት መኖር እና መሞት ነው፡፡
❖ የምድር ሕይወት ቀልድ ወይም ፌዝ አይደለም፡፡
❖ የሰዎችን ምሳሌነት ወይም የሕይወት ተሞከሮ መመልከት ተገቢነት አለው፡፡
❖ ራዕይን በህልም ልንቀበል እንችላለን ነገር ግን በህልም ያየነው ሁሉ ራዕይሊሆን አይችልም።
❖ ራዕይ ማለት ግልጽ የሆነ ለዓላማችን ማስፈፀሚያ የምንደርስበት ከፍተኛ ቦታ ነው፡፡
❖ ራዕይ በጊዜ እና በሰዓት ልዩነት በሰውም ሆነ በራሱ በእግዚአብሔር አይጨመርም አይቀነስም፡፡
❖ ሰው የሚመራው በስሜቱ ሳይሆን በአእምሮው እውቀትን__ በልቡም ማስተዋልን በመያዝ ነው፡፡
❖ ለራዕዩ መሥራት ያልወደደ ባለ ራዕይ የያዘው ራዕይን ሳይሆን ቅዠትን ነው፡፡
❖ ራዕይን መቀበላችንም ሆነ መፈፀማችን ለመወለዳችንም ሆነ ለመሞታችን ምክንያት አይሆንም፡፡ ስለዚህ ዋናው ነገር ራዕያችንን ወደ ዓላማችን፣ ግባችንንም ወደ _ ዓላማችን፣ ባጠቃላይም መኖራችንን ወደ ዓላማችን ማድረሱ ላይ ነው፡፡
❖ ብዙ ጉዞ የተጓዝንበንት እና ብዙ መስዋእት የከፈልንበትን፡፡ ራዕይበጨበጥነው ጊዜ ዓላማውን ለመፈፀም እንጂ ለመኩራራት አይደለም።
❖ ሰው ራዕይ ብሎ ብዙ የሮጠበት ጉዳይ ለዓላማ ማስፈፀምያ ከፍተኛ ቦታ እንጂ በራሱ መጨረሻ አይደለም፡፡
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
08/14/2017
1 824
"አካላችን ምንም ያህል ደካማ ነው ብንል አዕምሮአችንን ካሳመንነው እና ካበረታነው ምንም ነገር ማድረግ እንችላለን አይቻልም የሚባል ነገር አይኖርም"
ለበለጠ መረጃ የቪኢኮድን የስልጠና ማዕከል ይጎብኙ
08/14/2017
