en
Feedback
Alex Sahilie

Alex Sahilie

Open in Telegram

INFORMATION IS POWER!

Show more
481
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1130 days
Posts Archive
" ተፈታኞች በአካልም ይሁን በስነልቦና እራሳችሁን ዝግጁ አድርጉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መርሃ ግብርን ይፋ አድርጓል። በዚህም ፥ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሐምሌ 16 እና 17/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም ገልጻ ይሰጣቸዋል። ከሐምሌ 19 እስከ 21/2015 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ። ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎች ወደመጡበት ይመለሳሉ። የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች  ደግሞ ሐምሌ 22 እና 23/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ገለጻ ይሰጣቸዋል። ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ።  ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎች ወደመጡበት ይመለሳሉ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን በሚውስዱበት ጊዜ የፈተናውን ህግና ስርዓት እንዲያከብሩ በጥብቅ አሳስቧል። ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ግልጋሎት ከሚሰጡ የፅህፈት መሳሪያዎች እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ እና ስክቢቶ ውጭ ወደ ፈተና ክፍል ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን እንዲያውቁት ብሏል። ተማሪዎቹ ከቤታቸው ሲወጡ፦ - መታወቂያ ፣ - አድሚሽን ካርድ - የት/ቤት ዩኒፎርም መያዛቸውን እንዳይረሱ ፤ ወላጆችም ይህንን እንዲያስታውሷቸው ጥሪ ቀርቧል። ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ የመሳሰሉ ደረቅ ምግቦችን ይዞ መግባት የሚፈቀድ ሲሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ የመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ነው። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተፈታኞች በአካልም ይሁን በስነልቦና እራሳቸውን ዝግጁ እንዲያደርጉ አሳስቧል። የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን ይፋ መደረጉ አይዘነጋም።

Barattootni maqaan keessan armaan gaditti maqaan keessan erame 12NS1 1. Eyerusalem Iriste Zeleke 2. Nebiya Moaz Lumi 3. Moaz Amin Isa 12NS2 1. Asia Dese Menza 2. Ayano Weyesa Haji 3. Bereket getachew bogale 4. Yasin haji harka 12NS3 1. Friye Tasew Alem 2. Fuad Mohammed Umer 3. Kamil Abadir Mama 4. Misra Jemal Doni 12NS4 1.Saron Yohanis Fikru 12NS5 1. Abdi Nasir Amin 2. Adnan Mohammed Sheko 3. Gezali Mustefa Aliyi 4. Mohammed Abduljelil Aman 12Ns6 1. Abreham Gebeyehu Tesema 2. Adisalem Tadesse Delesa 3.Bezawit Tazeb Gebre 4.Lamrot Ejigu Kebeds 5. Yeabsira Girma Negash 12Ns7. 1. Elias Moges Atlabachew 2. Imran Mohammed seid 3. Kaleab Mesfin Tadesss 4. Negash Girma Gugsa 12NS8 1. Beza Negash Geme 2. Dawit Asrat Wolde 3. Leyla Mohammed husen 4. Umer Kemal Haji 12NS9 1. Elias Abdel Gerbi 2. Hana Elias Mohammed 3. Iman Adem Beyan 12NS11 1. Beken Andualem Tarekegn 2. Milki Tasew Eshetu

bara 2015 Seemisteera 2ffaa Barattootni barnoota ICT qoruumsa waliigalaa ykn final exam hin fudhanne har'a 20/10/2015 sa'aatii 8:00- 9:00tti dhuftanii akka nadubbistan 2015 ዓም የ2ኛ Sem.ICT ማጠቃለያ ፈተና ያልወሰዳችሁ ተማሪዎች ዛሬ 20/10/2015 ዓም ከቀኑ 8:00-9:00 ሰዓት መጥታችሁ እንድታናግሩኝ

photo content

new
new

unit three handout for g12 2ndsem.pptx1.03 KB

የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜ   ተገለፀ። ----------------------- ግንቦት 10/2015 ዓም. (የትምህርት ሚኒስቴር) በ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ሁኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ  ተማሪዎች ፈተናና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ  እስከ ሰኔ 30/2015ዓ.ም ድረስ እንዲጠናቀቅ በትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ተቀምጧል። ፈተናውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በተሰጠው ትምህርት መሠረት ከማዕከል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ  ተብሏል ። በዚህም መሰረት በሴሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት የተቋማት የውስጥ ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንዲሁም በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና ውጤት 50 ከመቶ  ይይዛል ተብሏል። ተማሪዎችም በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን ለመከታተል ብቁ ሆነው ለመገኘት የሁለቱ ድምር አማካይ 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋልም ተብሏል። ዩኒቨርሲቲዎችም ፈተናውን በማስተዳደርና ውጤት በመግለጽ በ2016 የፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ የሆኑ ተማሪዎችን  ለይተው እስከ ሰኔ 30/2015ዓም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ የ2016 የትምህርት ካሌንደር የተስተካከለ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ  ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

12th grade national exam time has been announced. May 10/2015 (Ministry of Education) The Ministry of Education has announced the date of the 2015 National End of Grade 12 Examination. The 12th grade final exam will be held from July 19 to July 30, 2015 in government universities. The minister urged the universities to complete their work and prepare themselves for the 12th grade exam that will be held from July 15/2015.

photo content

ሀገር ከቀፍ ፈተና " የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችና  ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችጋር ውይይት አካሄደ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡ ፈተናው ልክ እንደባለፈው አመት በሁለት ዙር የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመጀመሪያው ዙር የነበሩ የፈተና ችግሮችን ዘርዝረው ለቀጣዩ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥና ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው የ2015 ዓ.ም ፈተናን ለማስፈፀም ልዩ ልዩ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑንና የተፈታኞች መረጃ በአግባቡ እየተደራጀ መሆኑን  አብራርተዋል። ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍና አመለካከቱን ለመቀየር፣ ብቁና አገር ተረካቢ ትዉልድ ለመፍጠር አሁን ያለው ባለድርሻ አካል ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም በ2016 ዓ.ም የሚካሄደው ፈተና እንደአካባቢው ሁኔታ ኦን ላይን እንደሚሆን ገልጸው የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡ ምንጭ፦ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

How did you understand the test method?
How did you understand the test method?

Iid Mubaarak// ኢድ ሙባረክ! ሙስሊም ወንድሞችና እህቶች እንኳን ለኢድ-አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም, የደስታና የፍቅር ይሁንላችሁ! Obboleeyyan Musiliimaa baga
+1
Iid Mubaarak// ኢድ ሙባረክ! ሙስሊም ወንድሞችና እህቶች እንኳን ለኢድ-አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም, የደስታና የፍቅር ይሁንላችሁ! Obboleeyyan Musiliimaa baga Ayyaana Iid Alfaxiriin isin gahe! Ayyaanni kan nagaa, gammachuu fi jaalalaa isiniif haa ta'u!

The new mid exam program
The new mid exam program

ማስታወቂያ #Ethiopia | የተባበሩት ኤምሬትስ የሰጠውን ስኮላርሽፕ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ሁሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው
ማስታወቂያ #Ethiopia | የተባበሩት ኤምሬትስ የሰጠውን ስኮላርሽፕ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ሁሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል ለመስጠት በፈቀደው መሰረት ቀደም ሲል በተማሪዎች ቃል የተገባላችሁ ተማሪዎችና በዕድሉ ለመጠቀም ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች Application Form link: http://survey.ethernet.edu.et/index.php/518562?lang=en -- በመግባት ከዛሬ 09/08/15 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 ቀናት ከላይ በተቀመጠው ሊንክ በመግባት፡- 1. የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት ኮፒ (Grade 12 Result) copy 2. ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኮፒ (Grade 9-12 transcript) copy 3. CV/ Curriculum Vitae copy 4. የልደት የምስክር ወረቀት ኮፒ (Birth Certificate) copy እና ሌሎች በሊንኩ የተጠቀሱ መረጃዎችን እንድትሞሉ እናሳስባለን ። መረጃዎች ተጣርተው ለፈተና የሚቀረቡ ተማሪዎችን ስም ዝርዝር በቀጣይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የምናሳውቅ መሆናችንን እንገልጻለን። የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አበባ

MID EXAM I have recieved information that the mid term exam will start next week on wednesfay

ቲቶ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ የማይታዘዙና ከንቱ የሚናገሩ የሚያታልሉ ይልቁንም ከተገረዙት ወገን የሚሆኑ ብዙ ናቸውና፤ ¹¹ እነዚህም ስለ ነውረኛ ረብ የማይገባውን እያስተማሩ ቤቶችን በሞላው ስለ ሚገለብጡ፥ አፋቸውን መዝጋት ይገባል። 1. የማይታዘዙና 2. ከንቱ የሚናገሩ የሚያታልሉ 3. ነውረኛ ረብ የማይገባውን      የሚያስተምሩ አፋቸው መዝጋት ያለበት

photo content

በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የስኮላር ሺኘ እንደተመቻቸላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ። ................................................... ትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ተፈትነው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እና 20 ትምህርት ቤቶች እውቅና ሽልማት ሰጥተዋል። በእውቅና መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን አበረታትተዋል። ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው የላቀ አድማጭ እና አስቀማጭ ስለሆናችሁ መምህራኖቻችሁ ያስተሟሯችሁን በትክክል ማየት ችላችኋል ያሉ ሲሆን ይህን ወደ እውቀት መቀየር ይጠበቅባችኋልም ብለዋል። ተማሪዎች በቀጣይ በሚኖራቸው የትምህርት ቆይታ እውቀትን ብቻ ሳይሆን ጥበብን አብዝተው መፈለግ እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ዐቢይ ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀው በተለይ ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል፤ እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁም ብለዋል። በመጨረሻም ለ 273  የላቀ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ  በማብሰር ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም  አሳስበዋል።