የተስፋ ቃል - Ye Tesfa Qal
Open in Telegram
819
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-1730 days
Posts Archive
ንጉሡ ዳዊትም ገባ በእግዚአብሔርም ፊት ተቀምጦ እንዲህ አለ፦ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ እስከዚህ ያደረስኸኝ እኔ ማን ነኝ
2 ሳሙኤል 7:18
Share♻️
@yetesfa_qal
እግዚአብሔር ፀሎታችንን መቼ ይመልሳል? /መምህር እዮብ ይመኑ👇👇👇👇
https://youtu.be/mqUIlIRGcM0?si=pFEFVoBJEyadKwwg
እግዚአብሔር የኃይል እና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሀት መንፈስ አልሰጠንምና
2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:7
Share♻️
@yetesfa_qal
ከእናንተ ኀጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት አላቸው። ዮሐንስ 8:7
የራስን ድካማ ማወቅ መላዕክትን ከማየት የበለጠ ጸጋ አለው።
ሶርያዊው ቅዱስ ይስሐቅ
Share♻️
@Yetesfa_qal
ጸሎታችን ያልተመለሰበት ምክንያት ይህ ነው!
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ #ጸሎት👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/qDXBj93RUjo?si=hqV84RSHWe-V2Ngb
ጌታ ቅርብ ነው።በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋራ በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።
ፊልድስዩስ 4:6
Share♻️
@yetesfa_qal
ጸሎታችን ያልተመለሰበት ምክንያት ይህ ነው!
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ #ጸሎት👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/qDXBj93RUjo?si=hqV84RSHWe-V2Ngb
እናንተ ደካማዎች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ
ማቴዎስ 11:28
Share♻️
@yetesfa_qal
➲ ➳ አንድ ምድራዊ ንጉሥ "ጠላቱን ያልወደደ ሰው በሞት ይቀጣል" ብሎ አዋጅ ቢያውጅ ሁሉም ሰው በአካለ ሥጋ ላለመሞት ሲል ሕጉን ለመጠበቅ የሚፋጠን አይደለምን?
ወዮ! ምድራውያን ነገሥታት በሥጋዊ ሞት እንዳይቀጡን ብለን ፈርተን የሚያወጡትን ሕግ ለመፈፀም የምንፋጠን ሆነን ሳለ፥ ለነገሥታት ንጉሥ ለእግዚአብሔር ሕግ አለመታዘዛችን እንደ ምን ያለ ወቀሳ ያመጣብን ይሆን?
( #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ )
@yetesfaqal
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኀቱ፣
ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፣
አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ፣
አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡
(ማኅሌተ ጽጌ)
"በፈተና ጊዜ፥ ደካማው ሰው "እንደዚህ የደረሰብኝ'ኮ" እያለ የሚያመካኝበት ሌላ ሰውን ይፈልጋል፤ ብርቱው ሰው ግን በፈተናው ይጸና ዘንድ እግዚአብሔርን ይፈልጋል፡፡"
ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
@zeekeranio
"ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም በቀቢጸ ተስፋ ሊያዝ አይገባውም፡፡ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡
እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኩሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንኼድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡
ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቆርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል። ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን (እንዲመጣ) የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ወደ ኦሎምፒያስ ከላከው መልእክት የተቀነጨበ
@zeekeranio
ተወዳጆች ሆይ! ማለፍ መለወጥ በሌለባት በመንግሥተ ሰማያት ጸጋንና ክብርን እናገኝ ዘንድ በምግባር በትሩፋት እናጊጥ፡፡ በዚህ ዓለም የሚኖረን ውበትና ጌጥ ድንገት ታይቶ የሚጠፋ ነው፡፡ የማይቻል ቢኾንም ምንም በሽታ፣ ኀዘን፣ ብስጭት፣ ይህም የመሳሰለ ኹሉ ባያገኘን እንኳን የዚህ ዓለም ውበትና ጌጥ ሃያ ዓመት ነው፡፡ በወዲያኛው ዓለም የሚሰጠው የሚገኘው ክብር ግን በዝቶ ሲሰጥ ይኖራል እንጂ መቼም ቢኾን መች አያልፍም፡፡ አይለወጥም፡፡ እርጅና የለምና ቆዳው አይጨማደድም፡፡ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስ አያገኘውም፡፡ ኀዘን አያወይበውም፡፡ በዚያ የምናገኘው ክብር፣ ውበት፣ ጌጥ ከዚህ ኹሉ የተለየ ነው፡፡ በዚህ ዓለም የምናገኘው ክብርና ውበት ግን የሚጠፋው ገና ከመምጣቱ ነው፡፡ ቢመጣ እንኳን አድናቂዎቹ ብዙ አይደሉም፡፡ ትሩፋትን ጌጥ ያደረጉ ሰዎች አያደንቁትም፡፡ የሚያደንቁት አመንዝሮች ናቸው፡፡
ስለዚህ ከዚህ ዓለም ከኾነው ክብር ልንለይ ይገባናል፡፡ መንግሥተ ሰማያትን እንወርስ ዘንድ ልንፈልገው የሚገባን ትሩፋትን ነው፡፡
_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_
@Zeekeranio
+1
ነሐሴ 24
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
የጻድቁ በረከት አይለየን🙏
