cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Teddy afro fans

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
320
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

"እንዴት ታምሪያለሽ ሩቢ መሳይ፣ ውበትሽ ወጥቶ ለዓለምይ.."
Show all...
​​ኔልሰን ማንዴላ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የህግ ትምህርት በሚማሩበት ጊዜ ነጭ ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው። ስሙም ፒተር አንድ ቀን ፕሮፌሰር ፒተር በአንድ ምግብ ቤት ምግባቸውን እየበሉ ሳለ ማንዴላ በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ። ዘረኛው ፒተርም "አቶ ማንዴላ! አሳማና 'ርግብ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" ሲላቸው ብልሁ ማንዴላም "አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ እሄዳለሁ" ብሏቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ። በዚህ የተናደደው ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣበት ያስባል። አንድ ቀንም ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ " ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳዎችን ብታገኝና በአንደኛው ቦርሳ 'ገንዘብ' በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ 'ጥበብ' ቢኖር የትኛውን ትወስዳለህ?" ብሎ ማንዴላን ሲጠይቀው ማንዴላም"ገንዘቡን እወስደዋለሁ" …ብሎ መለሰለት። ፕሮፌሰሩም በድል አድራጊነት "አንተ ሞኝ ነህ እኔ አንተን ብሆን ኖሮ ጥበብ ያለበትን ቦርሳ እወስድ ነበር" ሲለው ማንዴላ ፈገግ እያለ "ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው" አለው። በዚህ ሁሉ ነገር የተበሳጨው ፕሮፌሰር ፒተር የማንዴላ የፈተና ወረቀት ላይ 'ደደብ' ብሎ ይፅፋል። ሌሎች ተማሪዎች የታረመላቸውን የፈተና ወረቀት ሲያዩ ማንዴላ ደደብ የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አየና ተገረመ ከዛም ወደ ፕሮፌሰሩ ሄዶ "ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥክልኝ ውጤቴን ረስተኸዋል" ብሎት እርፍ ፡፡ ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19
Show all...

ክቡር ዶክተር አርቲስት ሻምበል ለማ ጉያ ዛሬ ግብዓተ መሬታቸው ተፈጽሟል። ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለሙያ አድናቂዎቻቸው በጠቅላላ መፅናናትን እንመኛለን! እግዚያር ነፍሣቸውን ከጻድቃን ማረፊያ ያድርግልን!
Show all...
መታደል እኮ ነው ጎበዝ! አትግደል ብሎ ሲጽፍ ገዳይ ካህን እንዳየ አጋንንት እንዲህ ሲጮኽ ማየት! ኧረ ምኑን ሞገስ ቢሰጠው ነው..? እንደው ምኑን ግርማ ቢያለብሰው ነው..? ተው ሲል ሺ የሚንጫጫለት..? ለማንኛውም አስታዋሽ ያሻቸዋልና ከስድብ ውጪ እንዲያው እንደ ቆርቆሮ ከመጮኽ ባለፈ ለወገናቸው ቅንጣት ታክል ውለታን ላልዋሉ ግለሰቦች /ቆርቆሮዎች/ ይኼንን ፅሑፍ ጀባ ለማለት ወደድኩ..! ቴዲ አፍሮ ከዚህ በታች የዘረዘርኳቸውን ተግባሮች ፈፅሞም ያልፈፀመ ያህል የሚሰማው ሩሩህ ሰው ነው። የቴዲ አፍሮ ገንዘቦች በተለያዩ ቦታ ተበልተው የሚቀሩ ሲሆኑ ከኮንሰርት ስራ አንስቶ እስከ ሲዲ አከፋፋዮች ድረስ በአግባቡ ገንዘቡን ከፍለውት አያውቁም። ይኼም ሆኖ ቴዲ አፍሮ ለገንዘብ ብሎ ፍርድ ቤት መቆምን የማይወድ ሰው ነው። ሌላው የቴዲ አፍሮ አስደናቂ ነገር በአጋጣሚዎች የተቸገሩ ሰዎችን ሲያገኝ ከ10 ሺ እስከ 100 ሺ ብር በቼክና በጥሬ ተቆጣሪ ገንዘቦችን ሸጎጥ አድርጎ የመሄድ ብዙ ልምድ አለው። ብዙ ብዙ ያልተሰሙ ለመፃፍም አመቺ ያልሆነ ቸርነቶችን አድርጓል። እስኪ ከብዙ በጢቂቱ እንመልከታቸው... ✔ ሐምሌ 30,1998 ዓ.ም በድሬዳዋ ደርሶ በነበረው የጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ30 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል። ✔ ጥቅምት 1,2002 Elshaday Relief and Development ባዘጋጀውና ከ50 ሺህ በላይ ህዝብ በተገኘበት የአዲስ አበባ ስታዲየም ኮንሰርት ከ 1 ሚሊየን ብር በላይ አሰባስቦ ሙሉ ገቢውን ለእርዳታ ድርጅቱ ገቢ ያደረገ ሲሆን በእለቱ ለአበበች ጎበና ሕፃናት ማሳደጊያ 100 ሺህ ብር እና ለታላቁ ደራሲ ለይልማ ገ/አብ የወርቅ ብዕር ሸልሟል። ✔ጥቅምት 23,2002 በህመም ላይ ትገኝ ለነበረችው ማንአልሞሽ ዲቦ መታከሚያ ይሆን ዘንድ 20 ሺህ ብር አበርክቷል። ✔ ጥቅምት 17,2004 የወጣት አስመሮም ኃይለ ሥላሴን ነፍስ ለማዳን ለሶማሊያ ሽማግሌዎች 700 ሺህ ብር ከፈሎ የወገኑን ህይወት አተረፈ። ይህ ወጣት 700 ሺ ብሩን ካልከፈለ ስቅላት ተፈርዶበት ነበር። ቴዲም መረጃውን በመፅሄት ላይ ነበር አንብቦ ፈጥኖ የደረሰለት። እጅግ አስደናቂው ነገር ደግሞ እጁ ላይ የነበረው ገንዘብ እጅግ ጥቂት ከመሆኑ የተነሳ ከጓደኞቹ ተበዳድሮ ነው ብሩን ያሟላው። ✔ጥቅምት 17,2004 ለኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞች ማህበር የ200 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጎ ለማህበሩ ያለውን አጋርነት አሳየ። ማህበሩም የምስጋና ምስክር ወረቀት ሰጥቶታል። ✔የአራት ኪሎ ወጣቶች ከአልባሌ ሥፍራ ይርቁ ዘንድ በአባቱ ስም ተቋቁሞ ለነበረው የእግር ኳስ ቡድን ለአራት አመታት በየአመቱ ግማሽ ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል። ✔በራሱ አነሳሽነት ለአበበ መለሰ ኮንሰርት በማዘጋጀት የአርቲስቱን ህይወት ከህልፈት ታደገ። ✔ጥቅምት 2005 ቀድሞ ይማርበት ለነበረው ቤቲልሄም ት/ቤት የኮምፒውተር እና የሙዚቃ መሣሪያ ድጋፍ አደረገ። ✔በተለያየ ግዜያት በተዘጋጁ ዝግጅቶች ላይ እንደዚሁም እዛው ድረስ በመሄድ ለወ/ሮ አበበች ጎበና ህፃናት ማሳደጊያ ከመቶ ሺ ብር በላይ የገንዘብ እርዳታ በተደጋጋሚ አበርክቷል። ✔ባለቤቱ አምለሰት ሙጬ ባስመረቀችው አረንጋዴ መሬት ዶክመንተሪ ፊልም ምርቃት ላይ በእንጨት ለቀማ ይተዳደሩ ለነበሩ እናት የ 20ሺብር ቼክ ሰጧቸዋል። ✔እንደዚሁም ለተለያዩ ድምፃዊያን ግጥም እና ዜማ በነፃ አድሏል። ✔መስከረም 10,2011 ዓ.ም ከቡራዩ የተፈናቀሉ ወገኖችን ሄዶ በመጎብኘት የ1 ሚሊዮን ብርም ድጋፍ አድርጓል። ✔ከሶስት አመታት በፊት ሊቢያ ላይ በአሸባሪው isis ሰማዕትነትን የተቀበሉ ወገኖቻችንን ቤተሰቦች ከባለቤቱጋ ለቅሶ በመድረስ የብርም ድጋፍ አድርጓል። ✔በሰለሞን ቦጋለ እና በሳምሶን /ቤቢ/ ለሚመራው "ህብረት ለበጎ ለአንድነት" ለተሰኘው የመረዳጃ ማህበር ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ አበርክቷል። ✔በአዲስ አበባ በተለይም የኳስ ሜዳ ልጆችን እና የሌላ አከባቢ ስራ አጥ ወጣቶችን አሰባስቦ በማደራጀት ስራ የሚጀምሩበትን ግማሽ ሚሊየን ብር አብርክቶላቸዋል። ✔አርቲስት ጌዲዮን ዳንኤልን እና የደጃች ባልቻ ቤተሰቦችንም በገንዘብ እረድቷል። ✔በጥር ወር 2010 ዓ.ም ባህር ዳር ላይ ኮንሰርቱን ለማቅረብ ባቀና ጊዜ ገዳማቶችን ሲጎበኝ ለገዳሙ ገንዘብ አበርክቷል። እንዲሁም በዚሁ አመት ከባለቤቱ ጋ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በማቅናት 100 ሺ ብር ሰቷል። ✔በ2010 ዓ.ም ሚያዝያ ወር ላይ በዕለተ ትንሳኤ /ፋሲካ/ በዳግማዊ አጤ ምኒልክ ሆስፒታል ታመው የተኙ ወገኖችን ሙሉ ቤተሰቡን ይዞ በመሄድ የገንዘብ እርዳታ አድርጓል። ሁለቱ ህፃናት ሳይቀሩ ብር እና ፍራፍሬዎችን ለታማሚዎቹ በማበርከት በዚህ የመልካም ምግባር ላይ ተሳትፈዋል። ✔ቴዲ አፍሮ ለአድናቂዎቹም ቢሆን የኮንሰርት መግቢያ ትኬቶችን በገንዘቡ ገዝቶ /ከ200/ በላይ የሚያበረከት ነው። ይኼም አሁን በዋለው ገበያ ከ100 ሺ ብር የማያንስ ነው። ✔️የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የከተማ አስተዳደሩ ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ 1.2 ሚሊዮን ብር በድጋፍ ለዘመቻው ለተቋቋመው ኮሚቴ አስረክቧል። ✔️ የካቲት 14 በመስቀል አደባባይ ከታሪካዊው ግዙፍ ኮንሰርት ከተገኘው ገቢ አዲስ አበባ መስተዳድር ለሚያደርገው በጎ ተግባር እንዲውል ሙሉ የኮንሰርት ገቢውን ድጋፍ አድርጓል። ✔️ ከቡራዩ ለተፈናቀሉ የጋሞ ህዝቦች የተጠለሉበት ስፍራ ድረስ በመሄድ 1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። እነኚህ በመጠኑ ያስታወስኳቸው ሲሆኑ ከላይ ለመጥቀስ እንደ ሞከርኩት ቴዲ አፍሮ ብዙ ያልተሰሙ ግለሰቦች ብቻ የሚያውቋቸው እርዳታዎችን ያደርጋል። ለዛሬ በዚኽ እንቋጨው እና ሌሎች ቴዲ አፍሮ በህይወቱ የዋላቸውን መልካም ምግባሮች ለመዳስስ እንሞክራለን። ቴዲ አፍሮን የምንወደው በምክኒያት ነው። ይኼንን ሁሉ ሲያደርግ ብሔር አይቶ አልነበረም። ሰብዓዊነት አስገድዶት እንጂ! አሁንም ነገም ለህዝብ ድምፁን ያሰማል ያለውን ይሰጣል..! ✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Show all...