ነገረ ሃይማኖት
Open in Telegram
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን መሰረት የደረጉ ✔የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ✔የቅዱሳን አባቶቻችን ገድል ✔የኢትዮጵያ ገዳማት ታሪክ ✔መጽሐፍት ዳሰሳ ✔የነገረ ሃይማኖት ትምህርቶች...ይቀርባሉ
Show more389
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+830 days
Posts Archive
389
ክርስቶስን ባንድ ነገር እንዋሐደው።
ሰማዕታት ደሙን አፍሶ ሲዋሐዳቸው አይተው ደማቸውን አፍሰው ተዋሐዱት።
መነኮሳትም ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቶ ሲዋሐዳቸው አይተው መንነው ገዳም ገብተው ተዋሐዱት።
ሰብአ አለምም በቃና ዘገሊላ አንድ አድርጎ ሲዋሐዳቸው አይተው ባንድ ተወስነው ተዋሐዱት።
መምህራንም ሲያስተምር አይተው እያስተማሩ ተዋሐዱት።
ዘካርያንም አምስት እንጀራ አበርክቶ ሲያጠግብ አይተው ያላቸውን እየሰጡ እየመጸወቱ ተዋሐዱት።
ትሁታን ትህትናን ሲሰራ አይተው ትሁታን ሁነው በትህትና ተዋሀዱት።
ስዱዳን ሲሰደድ አይተው በስደት ተዋሐዱት።
ኮነነ በኩረ ወጥንተ.... ለበጎው ነገር ሁሉ አርአያ ሆነንእንዲል።
ጻዕ ውስተ ሐሠሣሁ ለዘመጽአ ለሐሲሶትከ
ሊፈልግህ የመጣውን ለመፈለጥግ ውጣ።
እንዲል? ማር ይስ።
"ከእኔም ተማሩ፤" እንዲል።
ማቴ 11:29
ክርስቶስን እንዴት እንወሐደው?
እስከ አሁን እንዴትስ ተዋሐድነው?
ከርዕሱ በርዕሱ ለርዕሱ ለመሆን እንዴት እንብቃ?
አለመዋሐድ ዕሩቅ ብእሲነት ነውና።
ዕውቀት የሰጠው ሕይወት የነሳው እንዳንሆን።
ዕቀት የሌለው አዋቂ
ልብ የለው ልበኛ
ሕይወት የሌለው ሕይወተኛ ማን ነው? የለምና።
# ግን ለመሆኑ እኛን እየተዋሐደን ያለው ማን ነው?
ምኞትእና ፍላጎት ሲዋሐደን። መንፈሳዊነት እና የቤተክርስቲያን የሆነውን ከመዋሐድ ግን ነጻ እየሆን ከመጣን ዕሩቅ ብእሲነት ነው።
ከሁሉም የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታዎች መራቆት ሕያው ሁኖ ግዑዝ ዕቃ መሆን ነው።
ስለዚህ የታችኛውን የዓለምን ተንኮል እና ሴራ አጋልጠን አራግፈን ፦የላይኛውን ዓለም መናፈቅ ይጠይቀናል።
ከአእምሮ ጠባያዊ ብቻ ከማሰብ እና ከመኖር ወጥተን በአእምሮ መንፈሳዊ መሳብ አለብን።
የበለጠ ከፍ ስንል የበለጠ ከፍታ አለና።
የበለጠ ክርስቲያን ስንሆን የበለጠ ፍቅረ ክርስትና ይሰጠናል።
ስርር በአክናፊከ እምነ ምድር ወዕርግ ኀበ ሀገሪትከ..
"ከምድር ተነስህ በክንፍ በረህ ወደሀገርህ ግባ"።
ማር.ይስ.እንዲል።
በዚያም በረሩ በዚያም በረሩ መገናኛው ኮሩ እንዲሉ በዚያም በዚያም ብለን ለመንግሥቱ ያብቃን።
የንታ ገብረመድኅን እንየው
389
✝"ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም በቀቢጸ ተስፋ ሊያዝ አይገባውም፡፡ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡
እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኩሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንኼድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡
ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቆርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን (እንዲመጣ) የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
389
✝ "አጠገብህ ስለሌለ ሰው ድክመት በተናገርክ ቁጥር ሰይጣን ይዘፍንበት ዘንድ ምላስህን በገና አድርገህ እንደሰጠኸው ቁጠር። ጥላቻ በልቦናህ ነግሶ ከሆነ የዲያቢሎስ እርዳታ እጅግ ታላቅ ይሆናል።"
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
389
✝ "ጌታችን ራሱን ለትዕቢተኛ ሰው አይገልጥም። ትዕቢተኛ ሰው ምንም ያህል መጻሕፍትን ቢያነብ እንኳ እግዚአብሔርን በጭራሽ አያውቅም ምክንያቱም እብሪት ለመንፈስቅዱስ ቦታ አይሰጥም። እግዚአብሔር በትሑት ነፍስ ብቻ የሚታወቅ ነው።"
አባ ሲሎዋን
389
✝ " የተባረከ ሰው ማለት የራሱን ድክመት የሚያውቅ ሰው ነው። ምክንያቱም ይሄ የእውቀቱ መሠረትና የሁሉም መልካም ነገሮች መጀመሪያ ይሆንለታልና።"
ማር ይስሐቅ
389
Online Self-Development training ለወጣቶች!
በፍሎሪሽ የጤና እና ጤና ነክ የማማከር አገልግሎት የተዘጋጀ። እንዳያመልጦ!!
Topic: Introduction to Creating Flourishing People and Organizations.
ስልጠናው የተዘጋጀው
-ለፍሬሽ ተመራቂዎች
-ለሁለተኛ ደረጃና እና የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች
-ለወጣት እና ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች እንዲሁም ለተቀጣሪዎች
-ስልጠናውን መውሰድ የሚፈልግ በሙሉ ተጋብዛችኋል።
👉የስልጠናው ቀን እና ሰዓት
ሃሙስ ህዳር 27, 2016 ዓ.ም ምሽት (1:00-3 O'clock LT) በonline ስለሚሰጥ በፈለጉት ሰዓት መርጠው ይሰልጥኑ
🎁 prize: Online certificate with minimal cost
👉የስልጠናው ክፍያ=200 ብር
👉ለመመዝገብ እንዲሁም ክፍያ ለመፈጸም የሚያስችሎትን መረጃ ለማግኘት ከታች ያለውን የጎግል ፎርም ሊንክ በመጫን ይመልከቱ፤ይመዝገቡ
https://forms.gle/amu3B5EjZMMuvgqC7
👉ለበለጠ መረጃ ከታች በተቀመጡት የስልክ አድራሻዎች ማግኘት ይችላሉ።
☎️ 0966324009/0978206620
👉የቴሌግራም ቻናላችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!! መረጃዎችን ያግኙ!!
https://t.me/flourish_consultancies
389
✝ "ቅዱሳን አባቶቻችን ሁል ጊዜ ከወደቃችሁ በኋላ ወዲያውኑ መነሳትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ አስፈላጊ ነው ይሉናል፡፡ ሁላችንም ያለማቋረጥ ኃጢአትን እንሠራለን፤ ተንሸራተንም እንወድቃለን፡፡ ምንም እንኳን በቀን መቶ ጊዜ ብንወድቅም ወደ ኋላ ዞር ብለን ሳናይ ተነስተን ወደ እግዚአብሔር መመለስ አለብን የሆነው ሆኗል፤ ያ ጊዜም አልፏል፡፡ ከእግዚአብሔር እርዳታ እንጠይቅ፤ ተስፋችንን ከውስጣችን ሊያጠፋ ለሚፈልገው ዲያብሎስ፤ 'እግዚአብሔር ከእኔ በላይ እኔን ይወደኛል ይቅርም ይለኛል' እንበለው፡፡"
አረጋዊ ታዴዎስ
389
✝"አዳም ወደነበረበት ምግብን ያልተመረኮዘ ኑሮ ምን እንደሚመስል ለማየት የምትፈልግ ከሆነ ብቸኛው መንገድ ጾም ነው። አብዝቶ የሚጾም ሰው ከምግብ ምርኮኝነት ወጥቶ የጥንተ ተፈጥሮ ማንነቱን ለማግኘት የሚታገል ሰው ሲሆን በዚህም ብዙዎች ተጠቅመው በሕይወት ሳሉ የገነትን ኑሮ ምንነት ተረድተዋል። እንደነ አባ እንጦንስ ያሉትን ጾመኞች ሰይጣን 'ከመጀመሪያው ሰው አዳም ወዲህ እንዲህ ያለ ሰው አልገጠመኝም' ብሎ የተደነቀባቸው ለዚህ ነው።"
የብርሃን እናት
በዲ/ን ኄኖክ ኃይሌ
@bahiretibebat21
389
✝ ጾም በአንተ ውስጥ የሆነ አንድ ነገር መለወጡን ተመልከት
"ከጾም የምታገኝው ነገር የምግብ ለውጥ መሆኑን ብቻ አትመልከት። ለተሻለ ህይወት የሚደረግ ለውጥ መሆኑን ተመልከት። ይህም ማለት በአንተ ውስጥ ያለ ጉድለትንና በውስጥህ እንዳለ የሚሰማህን ከእግዚአብሔርና ከሰዎች ጋር የሚሆን ድክመት ተመልከት ማለት ነው። ይህ ሳይሆን ከቀረ በሃምሳ አምስቱ የሁዳዴ ጾም ቀናት ውስጥ ራስህን አሸንፈህ ከቆየህ በኋላ ከእግዚአብሔር ጋር የፍቅር ዝምድና እና የተረጋጋ ግንኙነት ሳትፈጥር ከጾሙ አስቀድሞ የነበረህን አቋም ሙሉ ለሙሉ ይዘህ ለመውጣት ከሆነ የነፍስህ ጥቅም ምን ሊሆን ነው? አንተ ምንም ዓይነት ለውጥ ሳታመጣና አስቀድመህ በነበርህበት ሁኔታ ውስጥ እያለህ እስከ አሁን ድረስ ስንት አጽዋማት እንዳለፉህ አስብ!
በሁሉም አጽዋማት ውስጥ ፈቃድህ ደካማ ጎንህን ለማሸነፍ ስኬታማ እንድትሆን አድርጎህ ቢሆን ኖሮ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር እንድትታረቅ አድርጎህ ቢሆን ኖሮ ወይም የእርሱን ፈቃድ ጣፋጭነት እንድትቀምስ አድርጎህ ቢሆን ኖሮ ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖርህ ዝምድና እስከ አሁን ድረስ እንደምን የሰፋና የጠለቀ ይሆን ነበር!
ስለዚህ ንስሃ በመግባት ጾምህን ጀምር። ጾምህን በጸሎት በምጽዋት በስግደት በመንፈሳዊ ንባባት በቅዳሴ በኪዳን ጸሎቶች አጅበው። እነዚህን ሁሉ በማድረግህ ከእግዚአብሔር ጋር ትወዳጃለህ የሁዳዴ ጾም የያዛቸው በረከቶች ብዙ ናቸውና። እኒህን ካደረክ በመጨረሻ ላይ ውጤቱን ከአምላክህ ትቀበላለህ።"
ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
389
✝ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ለማን?
"ሰው ወደሚበዛበትና የዚህን ዓለም ፍርድ ወደሚሰጡ ቦታዎች አለመኼድ ስለማልችል፣ የምመራው ትልቅ የንግድ ድርጅት ስላለኝ፣ ሥራዬ ጥበበ እድ ስለሆነ፣ ጊዜ ስለሌለኝ፣ ትዳር ስላለኝ፣ ልጆችን ስለማሳድግ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆንኩ፣ እኔ የዓለም ሰው ስለሆንኩ መጻሕፍትን ማንበብ አይጠቅመኝም፤ "መጻሕፍትን ማንበብ በገዳም ለሚኖሩ መነኮሳት ነው" ብለህ አትንገረኝ። "አንተ ሰው! ምን ማለትህ ነው?" "ብዙ የዚህ ዓለም አሳብ ስላለብኝ መጻሕፍት ማንበብ ለእኔ አይደለም" ትለኛለህን? እንዲያውም ልንገርህ! አንተም ስማኝ! ከእነዚያ መነኮሳት ይልቅ ማንበብ ያለብህ አንተ ነህ:: መጻሕፍትን በብዛት ማንበብ የሚገባቸው ብዙ የዓለም አሳብ ያላቸው ሰዎች እንጂ በምግባር በትሩፉት የተጠመዱ መነኮሳት አይደሉምና::
ምንጭ፦
"የክርስቲያን መከራ" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ትርጉም፦ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
389
✝ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ፣ ኀጢአትን ከመሥራት ለመጠበቅ ዓይነተኛው መንገድ ነው፤መጻሕፍትን አለማወቅ ግን ጥልቅ ጉድጒድ እና ታላቅ ገደል ነው፤
ስለ መለኮታዊው ሕግ አለማወቅ ደግሞ ታላቅ የድኅነት ክህደት ነው።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደ ሰበከው
(ሀብታም እና ደሀ)
389
✝ ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው
" ይህን ያህል ትሕትና እንደምን ያለ ትሕትና ነው።ይህን ያህል ትዕግሥት እንደ ምን ያለ ትዕግስት ነው።ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው።
ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው።
ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው።
ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው። በደል የሌለበትን እንደ በደለኛ ሰቀሉት ሕይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት። አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተሸነከሩ፣ ወዮ! በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ፣ ወዮ። በአዳም ፊት የሕይወት መንፈስን እፍ ያለ አፍ ከሐሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መጻጻን ጠጣ ወዮ።
የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው ምን ከንፈር ነው ምን አንደበት ነው። የፍቅር የጌታ ሕማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል ኅሊናም ይመታል ነፍስም ትንቀጠቀጣለች ሥጋም ይደክማል።
የማይሞተው ሞተ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ።"
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ
389
✝ አበው ስለ እመቤታችን እንዲህ አሉ
"አምላክ ከንጉሥ ሔሮድስ ሴት ልጅ ቢወለድ ኖሮ አልጋ ወራሽ በሆነና ባልተሰደደ ነበር። እርሱ ግን የድሆች ልጅ የሆነችውን ድንግል መረጠ"
#አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ
"ታላቁ ተራራ ሆይ ታናሽዋ ብላቴና የተሸከመችህ ራስህን በሚቻላት መጠን አድርገህላት ነው ፣ ታላቁ እሳት ሆይ ታናሽዋ ብላቴና ተሸክማህ ያልተቃጠለችው ኃይልን ትችል ዘንድ አጽንተሃት ነው "
#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ
"ይህ ዓለም የእግዚአብሔርን ልጅ በቀጥታ ከእግዚአብሔር አብ እጅ ለመቀበል የተገባ ሆኖ ስላልተገኘ ፣ ዓለም ከእርስዋ ይቀበል ዘንድ አንድያ ልጁን ለድንግል ማርያም እናት ትሆነው ዘንድ ሠጣት"
#ቅዱስ_አውግስጢኖስ
"ሔሮድስ የማይያዘውን ይይዝ ዘንድ ተነሣ ፣ ዓውሎ ነፋስንም በቤቱ አስገብቶ ሊዘጋ ታገለ"
#አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ
"ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??"
#ቅዱስ_ኤፍሬም
(በ ዲ/ን ኄኖክ ኃይሌ የተሰባሰበ)
389
✝ ሕሊናህን ለነፍስህ ከማይጠቅም ወሬ መጠበቅ
"ክርስቲያናዊ ፍጹምነትን ለማግኘት የምትፈልግ ከሆነ ሕሊናህን ለነፍስህ ከማይጠቅም ወሬ መጠበቅ አለብህ፡፡እንደ አጋጣሚ ሆኖ ዘመኑ የመረጃና የመረጃ ጥበብ ዘመን ነው፡፡ዓለም በቲቪ፡ በመጻሕፍት፡ በጋዜጦች ብቻ ሳይሆን በመረጃ መረብ ጭምር የሚያጥለቀልቅ መረጃን ከምንግዜው በላይ እያቀረበችልን ነው፡፡ነገር ግን ይህ ጥቅም የለሽ መረጃ እኔ የአእምሮ ብክለት ብዬ ለምጠራው ችግር ይዳርጋል፡፡በዚህ ዘመን ለሥራቸው ውጤታማነት ቢጠቅምም ባይጠቅምም መረጃን በመረጃነቱ ብቻ የሚፈልጉ የመረጃ ሱሰኞች አሉ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በ 1ቆሮ 2፡2
እንዲህ ይለናል፡-
"በመካከላችሁ ሳለሁ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ ነገር ላላውቅ ቆርጨ ነበር"
ምንጭ፡- ተግባራዊ ክርስትና
አዘጋጅ፡- አቡነ አትናቲዎስ
ትርጉም: ሔኖክ ኃይሌ
389
✝ የምግባር ጉድለት
"የምግባር ጉድለት የቆዳ በሽታ ነው፤
የሃይማኖት ጉድለት ግን የልብና የኩላሊት፣ የሳንባና የጉበት፣ የሆድና የአንጀት ደዌ ስለሆነ፣ ከዚያ (ከቆዳው በሽታ) ይከፋል፤
ሆኖም ለውስጥ ሰውነት መከላከያው ቆዳ እንደሆነ፣ ለሃይማኖት ምሽጉ ምግባር ነው፤
ምግባር ከተጣሰ፣ ሃይማኖት መናወጡ አይቀርም።"
'ሥነ ምግባር' ከወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ
@bahiretibebat21
389
✝ አሁን ንጽሕናዬን ያጣሁ እኔ ምን ላደርግ እችላለሁ?
"የክፋት አለቆች በኅጢአት ምኞት አሳወረውኛል፤ በተንኮላቸውም የልጅነት (የወጣትነት) ውበቴን ነጥቀውኛል። አሁን ንጽሕናዬን ያጣሁ እኔ ምን ላደርግ እችላለሁ? ወደ ክርስቶስ እጮኻለሁ፤ እርሱ ውበቴን ይመልስልኝ ዘንድ - ያን ጊዜ የክፋት ሠራዊት ያፍራሉ።
መድኃኒቴም ወደ እኔ ወደ ደቀ መዝሙሩ እንዲህ ብሎ ይመልስልኛል፦ ለመዳን ተስፋ አትቁረጥ፤ ወደቀደመ ሥፍራህ እመልስሃለሁ፣ ኀጢአትህንም ይቅር እላለሁ። አልተውህም ፈልጌ አግኝቼሃለሁና፤ በገዛ ደሜም ዋጅቼሃለሁና።
አንተ ኀጢአተኛ! በሙሉ ኃይልህ በአንደበትህ ሳትሰስት ጩኽ
ጌታህ መሐሪ በንስሐ የሚመለሱትንም የሚወድ ነውና። በተመለስህ ጊዜ ወዲያውኑ እርሱ አባትህ ቀድሞ በፊትህ ሊቀበልህ ይወጣል። የሰባውን ፍሪዳ ያርዳል፣ ያማረውን ካባ ያለብስሃል፣ በአንተም ደስ ይለዋል።"
ቅዱስ ኤፍሬም
