en
Feedback
ነገረ ሃይማኖት

ነገረ ሃይማኖት

Open in Telegram

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን መሰረት የደረጉ ✔የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ✔የቅዱሳን አባቶቻችን ገድል ✔የኢትዮጵያ ገዳማት ታሪክ ✔መጽሐፍት ዳሰሳ ✔የነገረ ሃይማኖት ትምህርቶች...ይቀርባሉ

Show more
389
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+830 days
Posts Archive
✝ ስለ ምጽዋት "የምትነድ እሳትን ውኃ ያጠፋታል፡፡ ምጽዋትም ኀጢአትን ታስተሰርያለች፡፡ ምጽዋትን ለሚሰጥ ሰው በመጨረሻ ይታሰብለታል፡በሚሰነካከልበትም ጊዜ መጠጊያን ያገኛል፡፡"               መጽሐፈ ሲራክ  3:28-29

✝ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ትወዳለህን? "ወንድሜ ሆይ ወደ አግዚአብሔር መቅረብ ትወዳለህን? ከሐዋርያው ከቅዱስ ጳውሎስ ጋርስ እንዲህ ማለትን ትሻለህን? "..ልሄድ ከክርስቶስ ጋር ልኖር እናፍቃለሁ።ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና።" ፊል 1:23 ይህን ለማለት ከፈለግህ ያ በሰዎች ፊት ከፍ ከፍ የምታደርገው የምታመጻድቀውና ከእግዚአብሔር ይልቅ ታመልከው ዘንድ ከጀመርከው አንተነትህ ተላቀቅ!" ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ (የነፍስ አርነት)  @bahiretibebat21

✝ "ክርስቲያን ማለት በሚችለው አቅም ሁሉ ክርስቶስን በሃሳብ፣ በቃልና በተግባር የሚመስል ነው።"   ቅዱስ ዮሐንስ ዘቅሊማቆስ(ዘሰዋስው) @bahiretibebat21

✝ " ጸሎትን ቅዱሳን አባቶቻችን 'ጣዕመ መንግስተ ሰማያት' እንደሚሏት አንተም መጸለይን በእግዚአብሔር ሕብረት ደስ እንደምትሰኝበት ልዩ ነገር ቁጠረው። በእርግጥም ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ደስታ ነው። በአባቱ እቅፍ እንዳለና መታቀፉን ብቻ ከምንም በላይ እንደሚመርጥ፣ ሌላ ምንም ነገር እንደማይጠይቅ ሕፃን፤ ምንም የመጠይቅ ቃል ከአንደበትህ ባይወጣም፣ በሕሊናህ ምንም ሐሳብ ባይኖርም #ስትጸልይ በእግዚአብሔር ቸርነት እቅፍ ውስጥ ነህና እንዲሁ ደስ ይበልህ!"               ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ @bahiretibebat21

✝ " ጸሎትን ቅዱሳን አባቶቻችን 'ጣዕመ መንግስተ ሰማያት' እንደሚሏት አንተም መጸለይን በእግዚአብሔር ሕብረት ደስ እንደምትሰኝበት ልዩ ነገር ቁጠረው። በእርግጥም ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ደስታ ነው። በአባቱ እቅፍ እንዳለና መታቀፉን ብቻ ከምንም በላይ እንደሚመርጥ፣ ሌላ ምንም ነገር እንደማይጠይቅ ሕፃን፤ ምንም የመጠይቅ ቃል ከአንደበትህ ባይወጣም፣ በሕሊናህ ምንም ሐሳብ ባይኖርም #ስትጸልይ በእግዚአብሔር ቸርነት እቅፍ ውስጥ ነህና እንዲሁ ደስ ይበልህ! ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ @bahiretibebat21

....መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ግን አስቀድሞ በነበረው ትምህርቱ "ከእኔ በኋላ የሚመጣውን የእግሩን ጠፍር ልፈታ የማይገባኝ ነው" እያለ እንዳስተማረ ጌታችን ወደ እሱ ቀርቦ አጥምቀኝ ቢለውም "አነ እፈቅድ እምኀቤከ እጠመቅ" በማለት ደቀ መዝሙር በመምህሩ ይጠመቃል እንጂ እንዴት መምህር በደቀመዝሙሩ ይጠመቃል ሲል ራሱን ዝቅ በማድረግ ከለከለው። ጌታችን ግን መልሶ፦ "አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው።" ያን ጊዜም ቅዱስ ዮሐንስ ሊያጠምቀው ፈቀደለት (ማቴ3፥15)። ጌታችንም በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ጥር ፲፩ ከሌሊቱ አሥር ሰዓት በሠላሳ ዓመቱ ተጠመቀ። ቀዳማዊ አባቱ አብ በደመና ሆኖ "ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር- የምወደው ልጄ ይህ ነው" አለ። መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወረደ። አንድነት ሦስትነትም ተገለጠ። በዮርዳኖስ መጠመቁ እንደ እንግድዓ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ የሆነ አይደለም። በብሉይ ኪዳን አባታችን አብርሃም በኮሎዶጎሞር ድል ቀንቶት ሲመለስ በዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ካህኑ መልከጼዴቅን አግኝቶት ነበር። ካህኑ መልከጼዴቅም ኅብስተ አኮቴት ጽዋዕ በረከት ይዞ የእግዚአብሔር ሰው ሆይ በማለት ተቀብሎታል። በኋላ ዘመን እስራኤልም ወደ ተስፋይቱ ምድር የገቡት ይህን የዮርዳኖስ ወንዝ ተሻግረው ነበር። ነቢዩ ኤልያስም ወደ ተዘጋጀችለት ብሔረ ሕያዋን ያረገው ዮርዳኖስን ወንዝ በመጎናጸፊያው ከፍሎ ተሻግሮ ነው ። እነዚህና ሌሎች በብሉይ ኪዳን የተደረጉ ነገሮች በሐዲስ ኪዳን ስለሚሆነው የጥምቀቱ ነገር ከሩቅ ማሳያዎች ነበሩ። አብርሃም የምእመናን፣ ኅብሰተ አኮቴት ጽዋዕ በረከት ይዞ የጠበቀው ካህኑ መልከጼዴቅ ክቡር ሥጋውን ቅዱስ ደሙን እንካችሁ ብሎ የሰጠን የክርስቶስ፣ ዮርዳኖስ ደግሞ የጥምቀት ምሳሌዎች ናቸው። እስራኤልም ከባርነት ተላቀው ሲወጡ የተስፋይቱን ምድር ከነዓንን ያገኟት ዮርዳኖስን ተሻግረው መሆኑ የሐዲስ ኪዳን ምእመናን በጥምቀት በኩል የክርስቶስ አካል ሆነው ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን የሚያዩ የመሆናቸው ምሥጢር ነበር። ከዚህም ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት "ባሕርኒ ርእየት ወጎየት ወዮርዳኖስኒ ገባ ድኅሬሁ" በማለት ዮርዳኖስ አምላክን ለማጥመቅ የተመረጠ ወንዝ ስለመሆኑ ትንቢት ተናግሮለታል። ጌታችን የተጠመቀበት ቦታም ዮር እና ዳኖስ የሚባሉ ወንዞች በሚገናኛቸው ላይ ነው። ሕዝብና አሕዛብ ተጠምቀው አንድ ሆነው በአንድ መጠሪያ ክርስቲያኖች ተብለው የሚጠሩ ናቸውና።በዚህም መለያየት ጠፍቷል። ውድ ልጆቻችን፦ የጌታችን ወደዚህ ምድር መምጣትና መጠመቅ ብዙ ትምህርትና ተአምራት የታየበት ነው። ዋና ዓላማው አዳምን በተንኮል አሳስቶ ከልጅነት ጸጋ ያጎደለውን ጠላት ዲያብሎስን ድል ነሥቶ ወደ ቀደመው የልጅነት ጸጋው መመለስና አዳምና ልጆቹ ድል የሚነሡበትን መንገድ ማሳየት ነው። ሰይጣን ድል ከተነሣባቸው መንገዶች አንዱ ደግሞ የጌታችን ጥምቀት ነው። የአዳም የዕዳ ደብዳቤ የተደመሰሰው በጥምቀቱ ነውና። በሌላም በኩል ጌታችን ወደ ዮሐንስ ሔዶ ትሕትናን አስተምሮናል። ወደ ዮሐንስ ሔዶ መጠመቁም ነገሥታትም ቢሆኑ ምእመናንም ቢሆኑ ወደ ካህን ሔደው እንዲጠመቁ ሥርዓት ሲሠራ ነው። ባዕለጸጋ እና ድሃ እኩል በሚያገኙት በውኃ መጠመቁም ጥምቀት የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ ናትና መንግሥተ ሰማያት በገንዘብ ብዛት የማትገዛ ለሁሉም የተሰጠች መሆኗን ሲያሳይ ነው። በጥምቀቱ ትሕትናን ገንዘብ ብታደርጉ ታላቅነትን ታገኛላችሁ ሲል አስተምሮናልና ትሑት ልቡናን ገንዘብ ማድረግ ይገባል። ይህንም የትሕትና መምህር አምላካችን በትሕትና ወደ ዮሐንስ ተጉዞ አሳይቶናል። በጥምቀቱ መለያየት የጠፋበት ነው። ሕዝብና አሕዛብ መባባል አሁን የለምና። "አንተም እንዲሁ አድርግ..." እያለ በወንጌል የሚያስተምረን አምላክ እኛም ከመካከላችን መለያየትን አርቀን ፍቅርን አንድነትን አጽንተን መኖር ይገባል። መልከ ጼዴቅ ለአብርሃም ኅብስተ አኮቴት ጽዋዕ በረከት ይዞ መታየቱም ከጥምቀት ባሻገር ምእመናን እንዲቆርቡ ማስተማሩ ነውና ከሁሉም በላይ ይህን በዓል ስታከብሩ በዓላቶቻችን መጽደቂያ እንጂ መመጻደቂያ እንዳይሆን በምግብና መጠጥ ብቻ ሳንይሆን ክቡር ሥጋውና ደሙን በመቀበል፤ ከዘፈንና ከዳንኪራ ርቃችሁ በመዝሙርና በምስጋና እንድታከብሩ እናሳስባችኋለን። በመጨረሻም የተወደዳችሁ ውድ ልጆቻችን ኾይ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ እያልን አሁን ዓለማችንም አገራችንም ሰላም ያጣችበት ዘመን ላይ ነንና የአዳምን በደል ይቅር ብሎ የዕዳ ደብዳቤውን አጥፍቶ እውነተኛ ሰላሙን የመለሰለት የሰላም አምላክ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ሰላምን ለአገራችን ይሰጥልን ዘንድ ወደ አምላካችን እንድትጸልዩ አሳስባችኋለሁ። መልካም በዓል!!        አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

✝ "በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ።” (ማር 1፥9 ) አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ የመወለዱና በዚህ ምድር ሠላሳ ሦስት ዓመት የመኖሩ ዋና ዓላማ
✝ "በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ።”  (ማር 1፥9 ) አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ የመወለዱና በዚህ ምድር ሠላሳ ሦስት ዓመት የመኖሩ ዋና ዓላማ ሰውን ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ለማዳን ነው። በመወለዱም አምላክነቱን ሳይለቅ የሰውን ባሕርይ ባሕርይው አድርጓልና ለእናቱ ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደሰውነቱ እየታዘዘ እንደ አምላክነቱ ታምራት እየሠራ በየጥቂቱ አደገ። "ልኅቀ ከመ ሕፃን እንዘ ይትኤዘዝ ለአዝማድኢሁ ወለይእቲ እሙ ድንግል"  ዕድሜው ሠላሳ ሲሞላ የተነገረው ትንቢት፣ የተቆጠረው ሱባዔ ይፈጸም ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ አካባቢ "ነስሑ ወእመኑ እስመ ቀርበት መንግሥተ ሰማያት" እያለ የሚሰብከውን ዮሐንስን በዮርዳኖስ ወንዝ እንዲያጠምቀው ጠየቀው።

✝ "..እመኑኝ እግዚአብሔር የተጋለጥንባቸውን እና በእርሱ የተጠበቅንባቸውን አደጋዎች ሁሉ ቢገልጥልን ሕይወታችን ሁሉ እርሱን ለማመስገን አይበቃም ነበር።"     ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ

✝ "ነፍስህ ቃለ እግዚአብሔር ማንበብ ስትሰለች ቃለ እግዚአብሔርን ማንበብና መስማት ደስ የማይላት ሲሆንና መንፈሳዊ ተግሳፅን ስታቃልል ካየሃት በክፉ ደዌ ላይ እንደወደክ ተገንዘብ።ሰዎች የሞትን ፍሬ የሚቀጥፉበት የመጀመሪያው ይህ ነውና።"     ቅዱስ እንጦንስ

✝ "ኃጢአትን በሠራት ጊዜ ሕሊናህን በመክሰስ በራስህ ተስፋ እንድትቆርጥና ሕይወትህም ትርጉም እንደሌለው አድርገህ እንድታስብ የሚያደርገው ሰይጣን ነው። በምህረቱና በአባታዊ ፍቅሩ ወደ ንስሐ እንድታመራ በማሳሰብ የሚወቅስህ ግን መንፈስ ቅዱስ ነው።"

✝ " ፪ በሐሳቤም ሁሉ አንቺን አደንቃለሁ። እንዲህም እላለሁ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ምን ያህል ጸጋ ክብር ሰጠ፡፡ ፫ እግዚኣብሔር ከሰው ልጅ የማይተባበሩ ▣ ሦስት ልደታትን ተወለደ ። እኔም ዐውቄ አደነቅሁ ባራተኛው እንጂ የበጎ ዕረፍት አላገኘሁም። ፬ አዳም ከሕቱም ምድር የተወለደ በተፈጥሮ ነው፡፡ እኔን ግን የጠቀመኝ የለም። ሔዋንም ከአዳም ግራ ጐን ተወለደች። እርሷም በተፈጥሮ ነው፡፡ ለኔ ግን የጠቀመችኝ የለም፡፡ ፭ ቃየልም እንደ ሰው ሁሉ በዘር በሩካቤ ተወለደ፡፡ የጠቀመኝ የረባኝ የለም። ስንኳን እኔን እራሱንም አልጠቀመም። እሊህ ሦስቱ ልደታትም ለማንም ለማን አይረቡም አይጠቅሙም ። ፮ ክርስቶስ ግን ያለዘር ያለሩካቤ ከድንግል ተወለደ። ለሁሉ የሚረባ የሚጠቅም ሆነ፡፡ ፯ ለዚህ ልደት መስገድ መገዛት ይገባል። ክብር ምስጋና ለዚህ ልደት ይገባል። ጌትነትና ገናንነት ኀያልነት አዚዝነት፡፡ እልልታ ግርግታ ለዚህ ልደት ይገባል። ፰ ይህ ጥበብ ፍልስፍና ዕጹብ ድንቅ ነው። ለዚህ አንክሮ ይገባል። ይህም የሥጋዌ ምሥጢር ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ ለዚህ አንክሮ ይገባል። ይህም ሰው መሆን ሥጋ መልበስ እጅግ ዕፁብ ድንቅ ነው፡፡ ፱ የሔዋን ደኅንነቷ እመቤታችን ሆይ የድንግልናሽ ኃይል እጅግ የሚያስደንቅ ዕጹብ ነው። ፲ የአዳምን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያጠፋሽለት እመቤታችን ሆይ የማይመረመር ረቂቅ ምሥጢር ባንቺ ተደረገ፡፡ ፲፩ እሳትና ውሀም ባንድነት ተስማምተው መኖራቸው እጅግ ድንቅ ነው፡፡ የሚያስፈራውንም ያንበሳ ደቦል ፀዓዳ በግዕት በክንዷ እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ፲፪ ከድንግልም ብላቴና ጡቶች ወተት መፍሰስ እጅግ ድንቅ ነው። በበረትም ለድኆች ልጅ የሰማይ ሠራዊት መስገድ እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ፲፫ ዓለምን ሁሉ የመላ አምላክም ከበረት ተጥሎ በጨርቅ ተጠቅሎ መገኘቱ እጅግ ድንቅ ነው። በረት ከጽርሐ አርያም ቁመት ረዘመ ከሰማይም ዳርቻ ሰፋ፡፡ ፲፬. ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ፡፡ ይኽውም አደፍ ጉድፍ ሳይኖርበት ንጽሕት የወለደችው ንጹሕ በግ ነው። በረት ለንጹሑ መሥዋዕት ሽታ መሰብሰቢያ ሆነ፡፡ ፲፭ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው ወሰነውም በረት የተመሰገነ ነው፡፡ የኃያላን ጌታ በውስጡ ተገኝቷልና።"        አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ                (አርጋኖን ዘሰኑይ)

✝ " ፪ በሐሳቤም ሁሉ አንቺን አደንቃለሁ። እንዲህም እላለሁ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ምን ያህል ጸጋ ክብር ሰጠ፡፡ ፫ እግዚኣብሔር ከሰው ልጅ የማይተባበሩ ▣ ሦስት ልደታትን ተወለደ ። እኔም ዐውቄ አደነቅሁ ባራተኛው እንጂ የበጎ ዕረፍት አላገኘሁም። ፬ አዳም ከሕቱም ምድር የተወለደ በተፈጥሮ ነው፡፡ እኔን ግን የጠቀመኝ የለም። ሔዋንም ከአዳም ግራ ጐን ተወለደች። እርሷም በተፈጥሮ ነው፡፡ ለኔ ግን የጠቀመችኝ የለም፡፡ ፭ ቃየልም እንደ ሰው ሁሉ በዘር በሩካቤ ተወለደ፡፡ የጠቀመኝ የረባኝ የለም። ስንኳን እኔን እራሱንም አልጠቀመም። እሊህ ሦስቱ ልደታትም ለማንም ለማን አይረቡም አይጠቅሙም ። ፮ ክርስቶስ ግን ያለዘር ያለሩካቤ ከድንግል ተወለደ። ለሁሉ የሚረባ የሚጠቅም ሆነ፡፡ ፯ ለዚህ ልደት መስገድ መገዛት ይገባል። ክብር ምስጋና ለዚህ ልደት ይገባል። ጌትነትና ገናንነት ኀያልነት አዚዝነት፡፡ እልልታ ግርግታ ለዚህ ልደት ይገባል። ፰ ይህ ጥበብ ፍልስፍና ዕጹብ ድንቅ ነው። ለዚህ አንክሮ ይገባል። ይህም የሥጋዌ ምሥጢር ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ ለዚህ አንክሮ ይገባል። ይህም ሰው መሆን ሥጋ መልበስ እጅግ ዕፁብ ድንቅ ነው፡፡ ፱ የሔዋን ደኅንነቷ እመቤታችን ሆይ የድንግልናሽ ኃይል እጅግ የሚያስደንቅ ዕጹብ ነው። ፲ የአዳምን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያጠፋሽለት እመቤታችን ሆይ የማይመረመር ረቂቅ ምሥጢር ባንቺ ተደረገ፡፡ ፲፩ እሳትና ውሀም ባንድነት ተስማምተው መኖራቸው እጅግ ድንቅ ነው፡፡ የሚያስፈራውንም ያንበሳ ደቦል ፀዓዳ በግዕት በክንዷ እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ፲፪ ከድንግልም ብላቴና ጡቶች ወተት መፍሰስ እጅግ ድንቅ ነው። በበረትም ለድኆች ልጅ የሰማይ ሠራዊት መስገድ እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ፲፫ ዓለምን ሁሉ የመላ አምላክም ከበረት ተጥሎ በጨርቅ ተጠቅሎ መገኘቱ እጅግ ድንቅ ነው። በረት ከጽርሐ አርያም ቁመት ረዘመ ከሰማይም ዳርቻ ሰፋ፡፡ ፲፬. ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ፡፡ ይኽውም አደፍ ጉድፍ ሳይኖርበት ንጽሕት የወለደችው ንጹሕ በግ ነው። በረት ለንጹሑ መሥዋዕት ሽታ መሰብሰቢያ ሆነ፡፡ ፲፭ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው ወሰነውም በረት የተመሰገነ ነው፡፡ የኃያላን ጌታ በውስጡ ተገኝቷልና።" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ   (አርጋኖን ዘሰኑይ)

✝ " ፪ በሐሳቤም ሁሉ አንቺን አደንቃለሁ። እንዲህም እላለሁ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ምን ያህል ጸጋ ክብር ሰጠ፡፡ ፫ እግዚኣብሔር ከሰው ልጅ የማይተባበሩ ▣ ሦስት ልደታትን ተወለደ ። እኔም ዐውቄ አደነቅሁ ባራተኛው እንጂ የበጎ ዕረፍት አላገኘሁም። ፬ አዳም ከሕቱም ምድር የተወለደ በተፈጥሮ ነው፡፡ እኔን ግን የጠቀመኝ የለም። ሔዋንም ከአዳም ግራ ጐን ተወለደች። እርሷም በተፈጥሮ ነው፡፡ ለኔ ግን የጠቀመችኝ የለም፡፡ ፭ ቃየልም እንደ ሰው ሁሉ በዘር በሩካቤ ተወለደ፡፡ የጠቀመኝ የረባኝ የለም። ስንኳን እኔን እራሱንም አልጠቀመም። እሊህ ሦስቱ ልደታትም ለማንም ለማን አይረቡም አይጠቅሙም ። ፮ ክርስቶስ ግን ያለዘር ያለሩካቤ ከድንግል ተወለደ። ለሁሉ የሚረባ የሚጠቅም ሆነ፡፡ ፯ ለዚህ ልደት መስገድ መገዛት ይገባል። ክብር ምስጋና ለዚህ ልደት ይገባል። ጌትነትና ገናንነት ኀያልነት አዚዝነት፡፡ እልልታ ግርግታ ለዚህ ልደት ይገባል። ፰ ይህ ጥበብ ፍልስፍና ዕጹብ ድንቅ ነው። ለዚህ አንክሮ ይገባል። ይህም የሥጋዌ ምሥጢር ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ ለዚህ አንክሮ ይገባል። ይህም ሰው መሆን ሥጋ መልበስ እጅግ ዕፁብ ድንቅ ነው፡፡ ፱ የሔዋን ደኅንነቷ እመቤታችን ሆይ የድንግልናሽ ኃይል እጅግ የሚያስደንቅ ዕጹብ ነው። ፲ የአዳምን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያጠፋሽለት እመቤታችን ሆይ የማይመረመር ረቂቅ ምሥጢር ባንቺ ተደረገ፡፡ ፲፩ እሳትና ውሀም ባንድነት ተስማምተው መኖራቸው እጅግ ድንቅ ነው፡፡ የሚያስፈራውንም ያንበሳ ደቦል ፀዓዳ በግዕት በክንዷ እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ፲፪ ከድንግልም ብላቴና ጡቶች ወተት መፍሰስ እጅግ ድንቅ ነው። በበረትም ለድኆች ልጅ የሰማይ ሠራዊት መስገድ እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ፲፫ ዓለምን ሁሉ የመላ አምላክም ከበረት ተጥሎ በጨርቅ ተጠቅሎ መገኘቱ እጅግ ድንቅ ነው። በረት ከጽርሐ አርያም ቁመት ረዘመ ከሰማይም ዳርቻ ሰፋ፡፡ ፲፬. ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ፡፡ ይኽውም አደፍ ጉድፍ ሳይኖርበት ንጽሕት የወለደችው ንጹሕ በግ ነው። በረት ለንጹሑ መሥዋዕት ሽታ መሰብሰቢያ ሆነ፡፡ ፲፭ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው ወሰነውም በረት የተመሰገነ ነው፡፡ የኃያላን ጌታ በውስጡ ተገኝቷልና።" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ   (አርጋኖን ዘሰኑይ)

✝ " ድንግል ማርያም ዘለዓለማዊውን አምላክ መውለዷን ፣ ማጥባቷን ፣ እንደ ሕፃን በእቅፏ ማቀፏን ስናስበው ይህን ድንቅ ምሥጢር ለመረዳትና ለማሰላሰል እንኳ ከአእምሯችን በላይ ይሆንብናል። ፍጡር የሆነች እርሷ ወደ መለኮታዊ ባሕርይና ክብር ይህን ያህል የቀረበችና የከበረች የመሆኗን ነገር ማሰብስ የሚያስከትለው ምን ዓይነት አግራሞትንና ፍርሃትን ይሆን?" ከሊቃውንት አንዱ " ስለ እርሷ ድንቅ ሆኖ የሚነገረውን ይህን ምሥጢር ማወቅ የሚቻለው ምን ልብ ነው?! መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው?! መስማት የሚቻለውስ ምን ጆሮ ነው?!" ቅዱስኤፍሬም (ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ) @bahiretibebat21

ብሒለ አበው! 1 ‹ራስህን በሐሰት አትውቀስ ራስን መክሰስ ትህትና አይደለም ታላቁ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው።›› /ቅዱስ ስራፕዮን/ 2 ‹‹የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ።›› /መጽሐፈ ምክር/ 3 ‹‹አንደበቱን ከቧልት ከሐሜት ያየውንም ሚስጥር ከመናገር የሚከለከል ሰው ልቦናውን ከኀልዮ ኃጥያት ያርቀዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/ 4 ‹‹ ጸጋ ቢሰጥህ በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እንዳታጣ።›› /ማር ይስሐቅ/ 5 ‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/ 6 ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።›› /አባ እንጦንስ/ 7 ‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል።›› /ቅዱስ አትናቴዎስ/ 8 ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።›› /ቅዱስ ሚናስ/ 9 ‹‹በማንም ላይ ክፈትን አትስሩ አትፍርዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።›› /ታላቁ አባ መቃርስ/ 10 ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።›› /ቅዱስ አርሳንዮስ/ 11 ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።›› /ቅዱስ እንድርያስ/ 12 ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ነጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/ 13 ‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ 14 ‹‹የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ 15 ‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ፀሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትፀልይ እደር።›› /ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ/ 16 ‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።›› /ቅዱስ እንጦንስ/ በረከተ ቅዱሳን አበው አይለየን!

✝ ክርስቶስን ባንድ ነገር እንዋሐደው " ሰማዕታት ደሙን አፍሶ ሲዋሐዳቸው አይተው ደማቸውን አፍሰው ተዋሐዱት። መነኮሳትም ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቶ  ሲዋሐዳቸው  አይተው መንነው ገዳም ገብተው ተዋሐዱት። ሰብአ አለምም በቃና ዘገሊላ አንድ አድርጎ ሲዋሐዳቸው አይተው ባንድ ተወስነው ተዋሐዱት።መምህራንም ሲያስተምር አይተው እያስተማሩ  ተዋሐዱት። ዘካርያንም  አምስት እንጀራ አበርክቶ ሲያጠግብ አይተው  ያላቸውን እየሰጡ እየመጸወቱ ተዋሐዱት። ትሁታን ትህትናን ሲሰራ አይተው ትሁታን ሁነው  በትህትና ተዋሃዱት።ስዱዳን ሲሰደድ አይተው በስደት ተዋሐዱት። ኮነነ በኩረ ወጥንተ.... ለበጎው ነገር  ሁሉ አርአያ ሆነን እንዲል። ጻዕ ውስተ ሐሠሣሁ ለዘመጽአ ለሐሲሶትከ ሊፈልግህ የመጣውን ለመፈለግ ውጣ።        እንዲል? ማር ይስ። "ከእኔም ተማሩ፤" እንዲል። ማቴ 11:29 ክርስቶስን እንዴት እንዋሐደው? እስከ አሁን እንዴትስ ተዋሐድነው? ከርዕሱ በርዕሱ ለርዕሱ ለመሆን እንዴት እንብቃ? አለመዋሐድ ዕሩቅ ብእሲነት ነውና። ዕውቀት የሰጠው ሕይወት የነሳው እንዳንሆን።         ዕውቀት የሌለው አዋቂ        ልብ የሌለው ልበኛ        ሕይወት የሌለው ሕይወተኛ ማን ነው? የለምና። ግን ለመሆኑ እኛን እየተዋሐደን ያለው ማን ነው?ምኞት እና ፍላጎት ሲዋሐደን መንፈሳዊነት እና የቤተክርስቲያን የሆነውን ከመዋሐድ ግን ነጻ እየሆን ከመጣን ዕሩቅ ብእሲነት ነው። ከሁሉም የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታዎች መራቆት  ሕያው ሁኖ ግዑዝ ዕቃ መሆን ነው። ስለዚህ የታችኛውን  የዓለምን ተንኮል እና ሴራ  አጋልጠን አራግፈን የላይኛውን ዓለም መናፈቅ ይጠይቀናል። ከአእምሮ ጠባያዊ ብቻ  ከማሰብ እና ከመኖር ወጥተን በአእምሮ መንፈሳዊ መሳብ አለብን። የበለጠ ከፍ ስንል የበለጠ ከፍታ አለና። የበለጠ ክርስቲያን ስንሆን የበለጠ ፍቅረ ክርስትና ይሰጠናል። ስርር በአክናፊከ እምነ ምድር ወዕርግ ኀበ ሀገሪትከ.. "ከምድር ተነስተህ በክንፍ በረህ  ወደሀገርህ ግባ"።             ማር.ይስ.እንዲል። በዚያም በረሩ በዚያም በረሩ መገናኛው ኮሩ  እንዲሉ በዚያም በዚያም ብለን ለመንግሥቱ ያብቃን።       የንታ ገብረመድኅን እንየው

✝ ክርስቶስን ባንድ ነገር እንዋሐደው " ሰማዕታት ደሙን አፍሶ ሲዋሐዳቸው አይተው ደማቸውን አፍሰው ተዋሐዱት። መነኮሳትም ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቶ  ሲዋሐዳቸው  አይተው መንነው ገዳም ገብተው ተዋሐዱት። ሰብአ አለምም በቃና ዘገሊላ አንድ አድርጎ ሲዋሐዳቸው አይተው ባንድ ተወስነው ተዋሐዱት።መምህራንም ሲያስተምር አይተው እያስተማሩ  ተዋሐዱት። ዘካርያንም  አምስት እንጀራ አበርክቶ ሲያጠግብ አይተው  ያላቸውን እየሰጡ እየመጸወቱ ተዋሐዱት። ትሁታን ትህትናን ሲሰራ አይተው ትሁታን ሁነው  በትህትና ተዋሀዱት።ስዱዳን ሲሰደድ አይተው በስደት ተዋሐዱት። ኮነነ በኩረ ወጥንተ.... ለበጎው ነገር  ሁሉ አርአያ ሆነንእንዲል። ጻዕ ውስተ ሐሠሣሁ ለዘመጽአ ለሐሲሶትከ ሊፈልግህ የመጣውን ለመፈለጥግ ውጣ።        እንዲል? ማር ይስ። "ከእኔም ተማሩ፤" እንዲል። ማቴ 11:29 ክርስቶስን እንዴት እንወሐደው? እስከ አሁን እንዴትስ ተዋሐድነው? ከርዕሱ በርዕሱ ለርዕሱ ለመሆን እንዴት እንብቃ? አለመዋሐድ ዕሩቅ ብእሲነት ነውና። ዕውቀት የሰጠው ሕይወት የነሳው እንዳንሆን።         ዕቀት የሌለው አዋቂ        ልብ የለው ልበኛ        ሕይወት የሌለው ሕይወተኛ ማን ነው? የለምና። ግን ለመሆኑ እኛን እየተዋሐደን ያለው ማን ነው?ምኞትእና ፍላጎት ሲዋሐደን።  መንፈሳዊነት እና የቤተክርስቲያን የሆነውን ከመዋሐድ ግን ነጻ እየሆን ከመጣን ዕሩቅ ብእሲነት ነው። ከሁሉም የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታዎች መራቆት  ሕያው ሁኖ ግዑዝ ዕቃ መሆን ነው። ስለዚህ የታችኛውን  የዓለምን ተንኮል እና ሴራ  አጋልጠን አራግፈን የላይኛውን ዓለም መናፈቅ ይጠይቀናል። ከአእምሮ ጠባያዊ ብቻ  ከማሰብ እና ከመኖር ወጥተን በአእምሮ መንፈሳዊ መሳብ አለብን። የበለጠ ከፍ ስንል የበለጠ ከፍታ አለና። የበለጠ ክርስቲያን ስንሆን የበለጠ ፍቅረ ክርስትና ይሰጠናል። ስርር በአክናፊከ እምነ ምድር ወዕርግ ኀበ ሀገሪትከ.. "ከምድር ተነስህ በክንፍ በረህ  ወደሀገርህ ግባ"።             ማር.ይስ.እንዲል። በዚያም በረሩ በዚያም በረሩ መገናኛው ኮሩ  እንዲሉ በዚያም በዚያም ብለን ለመንግሥቱ ያብቃን።   የንታ ገብረመድኅን እንየው

✝️ክርስቶስን ባንድ ነገር እንዋሐደው ሰማዕታት ደሙን አፍሶ ሲዋሐዳቸው አይተው ደማቸውን አፍሰው ተዋሐዱት። መነኮሳትም ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቶ  ሲዋሐዳቸው  አይተው መንነው ገዳም ገብተው ተዋሐዱት። ሰብአ አለምም በቃና ዘገሊላ አንድ አድርጎ ሲዋሐዳቸው አይተው ባንድ ተወስነው ተዋሐዱት።   መምህራንም ሲያስተምር አይተው እያስተማሩ  ተዋሐዱት።   ዘካርያንም  አምስት እንጀራ አበርክቶ ሲያጠግብ አይተው  ያላቸውን እየሰጡ እየመጸወቱ ተዋሐዱት። ትሁታን ትህትናን ሲሰራ አይተው ትሁታን ሁነው  በትህትና ተዋሀዱት። ስዱዳን ሲሰደድ አይተው በስደት ተዋሐዱት።   ኮነነ በኩረ ወጥንተ.... ለበጎው ነገር  ሁሉ አርአያ ሆነንእንዲል። ጻዕ ውስተ ሐሠሣሁ ለዘመጽአ ለሐሲሶትከ   ሊፈልግህ የመጣውን ለመፈለጥግ ውጣ።          እንዲል? ማር ይስ። "ከእኔም ተማሩ፤" እንዲል። ማቴ 11:29 ክርስቶስን እንዴት እንወሐደው?   እስከ አሁን እንዴትስ ተዋሐድነው? ከርዕሱ በርዕሱ ለርዕሱ ለመሆን እንዴት እንብቃ? አለመዋሐድ ዕሩቅ ብእሲነት ነውና። ዕውቀት የሰጠው ሕይወት የነሳው እንዳንሆን።         ዕቀት የሌለው አዋቂ        ልብ የለው ልበኛ        ሕይወት የሌለው ሕይወተኛ ማን ነው? የለምና። # ግን ለመሆኑ እኛን እየተዋሐደን ያለው ማን ነው? ምኞትእና ፍላጎት ሲዋሐደን።  መንፈሳዊነት እና የቤተክርስቲያን የሆነውን ከመዋሐድ ግን ነጻ እየሆን ከመጣን ዕሩቅ ብእሲነት ነው። ከሁሉም የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታዎች መራቆት  ሕያው ሁኖ ግዑዝ ዕቃ መሆን ነው።   ስለዚህ የታችኛውን  የዓለምን ተንኮል እና ሴራ  አጋልጠን አራግፈን ፦የላይኛውን ዓለም መናፈቅ ይጠይቀናል። ከአእምሮ ጠባያዊ ብቻ  ከማሰብ እና ከመኖር ወጥተን በአእምሮ መንፈሳዊ መሳብ አለብን። የበለጠ ከፍ ስንል የበለጠ ከፍታ አለና። የበለጠ ክርስቲያን ስንሆን የበለጠ ፍቅረ ክርስትና ይሰጠናል። ስርር በአክናፊከ እምነ ምድር ወዕርግ ኀበ ሀገሪትከ.. "ከምድር ተነስህ በክንፍ በረህ  ወደሀገርህ ግባ"።             ማር.ይስ.እንዲል። በዚያም በረሩ በዚያም በረሩ መገናኛው ኮሩ  እንዲሉ በዚያም በዚያም ብለን ለመንግሥቱ ያብቃን።   የንታ ገብረመድኅን እንየው

ክርስቶስን ባንድ ነገር እንዋሐደው ሰማዕታት ደሙን አፍሶ ሲዋሐዳቸው አይተው ደማቸውን አፍሰው ተዋሐዱት። መነኮሳትም ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቶ  ሲዋሐዳቸው  አይተው መንነው ገዳም ገብተው ተዋሐዱት። ሰብአ አለምም በቃና ዘገሊላ አንድ አድርጎ ሲዋሐዳቸው አይተው ባንድ ተወስነው ተዋሐዱት።   መምህራንም ሲያስተምር አይተው እያስተማሩ  ተዋሐዱት።   ዘካርያንም  አምስት እንጀራ አበርክቶ ሲያጠግብ አይተው  ያላቸውን እየሰጡ እየመጸወቱ ተዋሐዱት። ትሁታን ትህትናን ሲሰራ አይተው ትሁታን ሁነው  በትህትና ተዋሀዱት። ስዱዳን ሲሰደድ አይተው በስደት ተዋሐዱት።   ኮነነ በኩረ ወጥንተ.... ለበጎው ነገር  ሁሉ አርአያ ሆነንእንዲል። ጻዕ ውስተ ሐሠሣሁ ለዘመጽአ ለሐሲሶትከ   ሊፈልግህ የመጣውን ለመፈለጥግ ውጣ።          እንዲል? ማር ይስ። "ከእኔም ተማሩ፤" እንዲል። ማቴ 11:29 ክርስቶስን እንዴት እንወሐደው?   እስከ አሁን እንዴትስ ተዋሐድነው? ከርዕሱ በርዕሱ ለርዕሱ ለመሆን እንዴት እንብቃ? አለመዋሐድ ዕሩቅ ብእሲነት ነውና። ዕውቀት የሰጠው ሕይወት የነሳው እንዳንሆን።         ዕቀት የሌለው አዋቂ        ልብ የለው ልበኛ        ሕይወት የሌለው ሕይወተኛ ማን ነው? የለምና። # ግን ለመሆኑ እኛን እየተዋሐደን ያለው ማን ነው? ምኞትእና ፍላጎት ሲዋሐደን።  መንፈሳዊነት እና የቤተክርስቲያን የሆነውን ከመዋሐድ ግን ነጻ እየሆን ከመጣን ዕሩቅ ብእሲነት ነው። ከሁሉም የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታዎች መራቆት  ሕያው ሁኖ ግዑዝ ዕቃ መሆን ነው።   ስለዚህ የታችኛውን  የዓለምን ተንኮል እና ሴራ  አጋልጠን አራግፈን ፦የላይኛውን ዓለም መናፈቅ ይጠይቀናል። ከአእምሮ ጠባያዊ ብቻ  ከማሰብ እና ከመኖር ወጥተን በአእምሮ መንፈሳዊ መሳብ አለብን። የበለጠ ከፍ ስንል የበለጠ ከፍታ አለና። የበለጠ ክርስቲያን ስንሆን የበለጠ ፍቅረ ክርስትና ይሰጠናል። ስርር በአክናፊከ እምነ ምድር ወዕርግ ኀበ ሀገሪትከ.. "ከምድር ተነስህ በክንፍ በረህ  ወደሀገርህ ግባ"።             ማር.ይስ.እንዲል። በዚያም በረሩ በዚያም በረሩ መገናኛው ኮሩ  እንዲሉ በዚያም በዚያም ብለን ለመንግሥቱ ያብቃን።   የንታ ገብረመድኅን እንየው