en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 553 subscribers, ranking 8 399 in the Technologies & Applications category and 2 163 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 553 subscribers.

According to the latest data from 20 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 12 over the last 30 days and by 7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.73%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 14.92% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 157 views. Within the first day, a publication typically gains 2 320 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 21 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 553
Subscribers
+724 hours
+77 days
+1230 days
Posts Archive
የውጤት ማስታወቂያ ........///............ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 08 እና ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ
+1
የውጤት ማስታወቂያ ........///............ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 08 እና ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱ አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው 1. በቧንቧ ጥገና ሠራተኛ ተ.ቁ. 1 በተሰጠው የጽሁፍና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጡ ስለሆነ 2. በኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ተ.ቁ. 1-2 በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከመጋቢት 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናዉን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለአካባቢው የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወላይታ ሶዶ ኮ
+6
ተቋሙ ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለአካባቢው የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ዙሪያ ለሚገኙ ነዋሪዎች የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ መስጠቱን በተቋሙ የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት ተቋሙ በሶዶ ከተማ የሚገኙ 12 ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የሰራው ሥራ የአካባቢው ነዋሪዎችን እርካታ አሳድጓል፡፡ ቀበሌዎቹን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከተመደበው ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ውስጥ 60 በመቶውን ወይም 150 ሚሊዮን ብሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሲሸፍን የተቀረውን 40 በመቶ ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሸፈኑን ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ከ150-ሚሊዮን-ብር-በላይ-ወጪ-በማድረግ-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው …….///……. የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል
+8
የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው …….///……. የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል ለማዘጋጀት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ከዴንማርክ የኢነርጂ ኤጀንሲ እና ኢነርጂኔት የኤሌክትሪክ ኃይልና የጋዝ አቅርቦት ኩባንያ ጋር በመተባበር በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ መዘግየቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል አውደ ጥናት አካሂዷል፡፡ አውደ ጥናቱ በዴንማርክ - ኢትዮጵያ የኢነርጂ ትብብር (Danish-Ethiopian Energy Partnership) ማዕቀፍ ስር የተዘጋጀ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎች እና ባለሙያዎች ከፕሮጀክት ትግበራ ሞዴል ጋር ተያይዞ ዓለም አቀፍ ልምዶችንና ተሞክሮዎችን እንዲቀስሙ ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የፕሮጀክቶችን-አፈፃፀም-ለማሻሻል-የሚያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅም በመጠገን ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ‎…....///....... ‎በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅ
+4
የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅም በመጠገን ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ‎…....///....... ‎በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅም በመጠገን ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። ‎ ‎የቢሮው ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ብሩክ እንዳለ እንደገለጹት ቢሮው በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት በተቋሙ ጋራዥ ለ1 ሺህ 227 ተሽከርካሪዎች የቀላል፣ መካከለኛ እና ከባድ የጥገና ሥራዎች አከናውኗል፡፡ ‎ ‎በተቋሙ ጋራዥ በራስ አቅም ጥገናዎችን ማከናወኑ ተሽከርካሪዎች በጥገና የሚቆዩበትን ጊዜ በማሳጠር፣ የተሽከርካሪዎችን የጥገና ታሪክ በቀላሉ በመመዝገብ እና በመከታተል የተሽከርካሪዎችን ዝግጁነት ማሳደጉን የገለጹት አቶ ብሩክ በተከናወነው ጥገናም 31 ነጥብ 58 ሚሊዮን ብር ማዳን መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-ተሽከርካሪዎች-በራስ-አቅም-በመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የጊቤ ግድቦች ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የመጀመሯ ማሳያ ናቸው - ዛዲግ አብርሃ ‎....///.... ‎በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የተገነቡት የግልገል ጊቤ 1 እና 2 እንዲሁም የጊቤ 3 የ
+3
የጊቤ ግድቦች ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የመጀመሯ ማሳያ ናቸው - ዛዲግ አብርሃ ‎....///.... ‎በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የተገነቡት የግልገል ጊቤ 1 እና 2 እንዲሁም የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የመጀመሯ ማሳያ መሆናቸውን የአፍሪካ አመራረረ ሥራ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። ‎ ‎እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ ይህ የግቤ ሰንሰለት የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይልና የኢኮኖሚ ከፍታ ማሳያ ከመሆኑም በተጨማሪ የቀጠናው የኃይል ማማ እንድትሆን አስችሏታል። ‎ ‎ እ.ኤ.አ በ2004 ሥራ የጀመረው የግልገል ግቤ 1፣ 184 ሜጋ ዋት በማመንጨት በወቅቱ የነበረውን የኃይል እጥረት በመቅረፍ ለሀገሪቱ የኢንዱስትሪ መነሳሳት መሠረት እንደነበር አስታውሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጊቤ-ግድቦች-ኢትዮጵያ-የውሃ-ሀብቷን-በአ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ጣቢያዉ ከ200 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለደንበኞች እያቀረበ ነው …….///…. የሐዋሳ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ለሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች፣ ለቴክኖሎጂ ድርጅቶች
+5
ጣቢያዉ ከ200 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለደንበኞች እያቀረበ ነው …….///…. የሐዋሳ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ለሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች፣ ለቴክኖሎጂ ድርጅቶች እና ለማህበረሰቡ ከ200 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ዳንኤል አንጄሎ እንደገለፁት በ2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 125 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እና ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 28 ሜጋ ዋት ለከተማው ነዋሪዎች፣ 40 ሜጋ ዋት ለኢንዱስትሪዎች እንዲሁም 135 ሜጋ ዋት ለቴክኖሎጂ ተቋማት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጣቢያዉ-ከ200-ሜጋ-ዋት-በላይ-ኃይል-ለደንበኞች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

መምሪያው የሴቶችን የአመራርነት እና ውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ….…///……. የሴቶችን የአመራርነትና እና ውሳኔ ሰጪነት ሚና በማሳደግ ሴቶች በዘርፉ ላይ የላቀ ተሳትፎ እንዲ
+8
መምሪያው የሴቶችን የአመራርነት እና ውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ….…///……. የሴቶችን የአመራርነትና እና ውሳኔ ሰጪነት ሚና በማሳደግ ሴቶች በዘርፉ ላይ የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለማስቻል በትኩረት እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መመሪያ አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ከ60 በላይ ለሚሆኑ የተቋሙ ሴት አመራሮች በሁለት ዙር ሲሰጥ የቆየው የአመራርነት ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለጹት የተቋሙ ሴት አመራሮች ሥራዎችን በብቃት ቢያከናውኑም ራሳቸውን ወደ ፊት በማምጣት እና ሥራዎቻቸውን በማሳየት ረገድ ግን ውስንነቶች አሉባቸው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=መምሪያው-የሴቶችን-የአመራርነት-እና-ውሳ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ ለሚቀርቡለት የኃይል ጥያቄዎች በአግባቡ ምላሽ እየሰጠ ነው ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 2 ሪጅን ከደንበኞች ለሚቀርቡለት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄዎች በአግባቡ ምላሽ እ
+7
ሪጅኑ ለሚቀርቡለት የኃይል ጥያቄዎች በአግባቡ ምላሽ እየሰጠ ነው ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 2 ሪጅን ከደንበኞች ለሚቀርቡለት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄዎች በአግባቡ ምላሽ እየሰጠ መሆኑን የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ ተናገሩ። አቶ ምትኩ እንደተናገሩት አሁን ላይ በሪጅኑ የሚቀርቡ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ የሚያስችል በቂ ኃይል በመኖሩ ከደንበኞች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ እየተሰጠ ይገኛል። ይሁንና ከኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ከከተሞች ፈጣን ዕድገት ጋር ተያይዞ እየጨመረ የሚመጣው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ በአግባቡ ለማስተናገድ ከወዲሁ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-ለሚቀርቡለት-የኃይል-ጥያቄዎች-በአ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የከተማዋን የኢንቨስትመንት ፍሰት እንደሚያሳድገው ተገለጸ ……..///……… በአርባ ምንጭ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኘው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣ
+5
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የከተማዋን የኢንቨስትመንት ፍሰት እንደሚያሳድገው ተገለጸ ……..///……… በአርባ ምንጭ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኘው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የከተማዋን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እና ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያነቃቃው የከተማ አስተዳደሩ ገለፀ። የከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደብል ደሳለኝ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በሆቴል፣ በኢንዱስትሪ እና በግብርና ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ትልቅ ተስፋ የፈጠረ በመሆኑ ለዘርፉ ዕድገትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። ከተማዋ በአሁኑ ወቅት በተለይም በሆቴልና በኢንዱስትሪ ዘርፎች በርካታ ባለሀብቶችን እየሳበች ትገኛለች ያሉት ኃላፊው ለዚህም የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ ግንባታ ትልቁን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማከፋፈያ-ጣቢያው-የከተማዋን-የኢ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

headline

Omit yetederege neger ale

ከይርጋለም ቁጥር 2- ሐዋሳ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር
+2
ከይርጋለም ቁጥር 2- ሐዋሳ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየተሰራ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ። በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የቱላ ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ማቴዎስ ወንድሙ እንደገለፁት በሀገር ሀብት ላይ ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን የተለያዩ ፖሊሳዊ የምርመራና ክትትል ስልቶችን ተጠቅሞ በቁጥጥር ሥር ለማዋል ሥራዎች ተጀምረዋል። ከህብረተሰቡ በሚገኘው መረጃ መሠረት ክትትል በማድረግ የተሰረቁ ንብረቶችን በህግ አግባብ ለማስመለስ እንደሚሰራ አዛዡ አረጋግጠዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተጠርጣሪዎችን-የተለያዩ-ፖሊሳዊ-የምርመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ ተጨማሪ ትራንስፎርመሮችን በመትከል አቅም የማሳደግ ሥራ ላይ ዕቅድ ይዟል …….///…….. በደቡብ 1 ሪጅን በየጊዜው እያደገ ለሚሄደው የኃይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በይርጋለም ቁጥር 2፣ በሐ
+3
ሪጅኑ ተጨማሪ ትራንስፎርመሮችን በመትከል አቅም የማሳደግ ሥራ ላይ ዕቅድ ይዟል …….///…….. በደቡብ 1 ሪጅን በየጊዜው እያደገ ለሚሄደው የኃይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በይርጋለም ቁጥር 2፣ በሐዋሳ ቁጥር 2 እና በዲላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የትራንስፎርመሮችን አቅም ለማሳደግ ዕቅድ መያዙን በሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ያለው አማረ እንደተናገሩት የሐዋሳ ቁጥር 1 እና የዲላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተሞቹ አሁን ለደረሱበት ዕድገት ሚናቸው የጎላ ነው። ይሁንና በአሁኑ ወቅት የሐዋሳ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያን ጨምሮ በሪጅኑ የሚገኙ አብዛኛዎቹ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጭነታቸው ከ90 በመቶ በላይ በመድረሱ የሚቀርቡ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎቶችን በአግባቡ ማስተናገድ የማይችሉበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-ተጨማሪ-ትራንስፎርመሮችን-በመትከ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ትናንት ማምሻውን በተፈፀመ ስርቆት አንድ ታወር ሲወድቅ በሀዋሳ ከተማ በከፊል ኃይል ተቋርጧል …….///……. ከይርጋለም ቁጥር 2 - ሐዋሳ ቁጥር 2 በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመበት ስርቆት ምክንያት አንድ ታወር መውደቁን የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ። በሪጂኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞሲሳ ገልቻ እንደገለፁት ስርቆቱ የማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍበት በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ቱላ ክፍለ ከተማ ጨፌ በሚባል ቀበሌ በሚገኝ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የተፈፀመው ነው። የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶው በተፈፀመበት ስርቆት ምክንያት በትላንትናው ዕለት ከምሽቱ 12:00 አካባቢ መውደቁን አቶ ሞሲሳ ተናግረዋል። የተፈፀመው ስርቆት ያደረሰው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ብረቶቹን መልሶ ለመጠቀም እንኳ አስቸጋሪ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስጂያጁ ገለፃ በስርቆቱ ምክንያት የሐዋሳ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ከይርጋለም ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ የሚያገኘው ኃይል የተቋረጠ ሲሆን የጣቢያው ኃይል የመስጠት አቅም በከፊል ቀንሷል፡፡ የወደቀውን ምሰሶውን ወደነበረበት ለመመለስ ሥራዎች መጀመራቸውንም የገለፁት አቶ ሞሲሳ የማስተላለፊያ መስመሩ ዳግም ኃይል ማስተላለፍ እስኪጀምር ድረስ በከፊል ኃይል የተቋረጠባቸው ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

ከፕሮጀክቱ የእውቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር ተገኝቷል ……….///……. የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል ከሆነው የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 -አርባ ምንጭ ቁጥር 2- አርባ ምንጭ ቁጥር 1 የኃይል ማስ
+8
ከፕሮጀክቱ የእውቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር ተገኝቷል ……….///……. የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል ከሆነው የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 -አርባ ምንጭ ቁጥር 2- አርባ ምንጭ ቁጥር 1 የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ የእውቀትና የቴክኖሎጅ ሽግግር ማግኘታቸውን በፕሮጀክቱ ሥራ ላይ የተሳተፉ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተናገሩ። በደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ ተቋራጭ የምዕራፍ አንድ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ከበደ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከሚኖረው ሀገራዊና አካባቢያዊ ፍይዳ ባሻገር በግንባታ ሂደት ላይ እያለ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም የእውቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር እንድኖር በማድረግ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከፕሮጀክቱ-የእውቀትና-ቴክኖሎጅ-ሽግግር&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የሐዋሳ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የከተማዋን 90 በመቶ የኃይል አቅርቦት እየሸፈነ ነው ……..///…….. የሐዋሳ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 90 በመቶ የሚሆነ
+5
የሐዋሳ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የከተማዋን 90 በመቶ የኃይል አቅርቦት እየሸፈነ ነው ……..///…….. የሐዋሳ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 90 በመቶ የሚሆነውን የከተማዋን የኃይል አቅርቦት እየሸፈነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ታከለ ተፈሪ ተናገሩ። አቶ ታከለ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ከ1980 ዓ.ም ጀምሮ የሐዋሳ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት እስከጀመረበት 2011 ዓ.ም ድረስ ለሐዋሳ ከተማና በዙሪያው ለሚገኙ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ሲያቀርብ ቆይቷል። ይሁንና የቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ ደንበኞችን በማዛወር ኢንዱስትሪዎችን ጨምሮ የተወሰኑ የከተማዋ ደንበኞች ከቁጥር ሁለት ኃይል እንዲያገኙ የተደረገ በመሆኑ በጣቢያው ላይ የነበረውን ጫና በማቃለል በኩል ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የሐዋሳ-ቁጥር-1-ማከፋፈያ-ጣቢያ-የከተማዋን-90&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም

“ሴቶች የኢነርጂ ሽግግር ተቀባዮች ብቻ ሳይሆኑ ወደፊት የሚመሩ መሐንዲሶች እና ውሳኔ ሰጪዎች ናቸው” - ኢንጂነር የምስራች ወርቁ ….….///……... ሴቶች የኢነርጂ ሽግግር ተቀባዮች ብቻ ሳይሆኑ መ
+7
“ሴቶች የኢነርጂ ሽግግር ተቀባዮች ብቻ ሳይሆኑ ወደፊት የሚመሩ መሐንዲሶች እና ውሳኔ ሰጪዎች ናቸው” - ኢንጂነር የምስራች ወርቁ ….….///……... ሴቶች የኢነርጂ ሽግግር ተቀባዮች ብቻ ሳይሆኑ መሪዎች፣ መሐንዲሶች፣ ፈጣሪዎች እና ውሳኔ ሰጪዎች መሆናቸውን በኢትዮጵያ የሴቶች ኢነርጂ ማህበር አምባሳደር (Ethiopian Women in Energy - EWiEn) ኢንጂነር የምስራች ወርቁ ገለጹ፡፡ ኢንጂነሯ ዓለም አቀፍ የሴቶችን ቀን (ማርች 8) ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ሴቶች የኢትዮጵያን ኢነርጂ የወደፊት ዕጣ ፈንታ በመቅረጽ ረገድ የሚጫወቱት ሚና የላቀ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ የሀገራችን የለውጥ ማዕከልና የማዕዘን ድንጋይ በመሆኑ በዚህ የለውጥ ሂደት ውስጥ ሴቶችን ማሳተፍ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ ያግዛል ብለዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሴቶች-የኢነርጂ-ሽግግር-ተቀባዮች-ብቻ-ሳ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም

"የሥርዓተ ጾታ እኩልነት መከበር የሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ አቅም ይፈጥራል" - አቶ ሙላት ገዛኽኝ …….///…... የሥርዓተ ጾታ እኩልነት መከበር ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገትና ብ
+9
"የሥርዓተ ጾታ እኩልነት መከበር የሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ አቅም ይፈጥራል" - አቶ ሙላት ገዛኽኝ …….///…... የሥርዓተ ጾታ እኩልነት መከበር ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገትና ብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (ማርች 8) "50 ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ!” በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ተከብሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኽኝ በዓሉን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሲከበር በኢትዮጵያ ብሎም በዓለም ዙሪያ ያሉ ሴቶች ለመብቶቻቸው በፅናት ታግለው ያስመዘገቧቸው ስኬቶች አብረው ይታሰባሉ፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የሥርዓተ-ጾታ-እኩልነት-መከበር-የሀገራች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ሴቶች ወደ ኃላፊነት እንዲመጡ ለማስቻል የማብቃትና የመደገፍ ሥራ ሊሰራ ይገባል …..…///……. ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (ማርች 8) "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ"
+9
ሴቶች ወደ ኃላፊነት እንዲመጡ ለማስቻል የማብቃትና የመደገፍ ሥራ ሊሰራ ይገባል …..…///……. ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (ማርች 8) "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተከብሯል። በዓሉ የሴቶችን መብት ለማስከበር፣ የእኩልነት ድምፅን ለማጎልበት እና ሴቶች ለሀገር ብልጽግና የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ እውቅና ለመስጠት ያለመ ነው። በበዓሉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 3 ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ጥሩ ወርቅ ሽፈራው ሴቶች ወደ ኃላፊነት እንዲመጡ ለማድረግ ማብቃትና መደገፍ ያስፈልጋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሴቶች-ወደ-ኃላፊነት-እንዲመጡ-ለማስቻል-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም