en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 540 subscribers, ranking 8 340 in the Technologies & Applications category and 2 161 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 540 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 1 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.98%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.34% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 882 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 540
Subscribers
-424 hours
-147 days
+130 days
Posts Archive
photo content

በክልሉ በሁለት ዓመት ተኩል ብቻ ከ76 ሚሊዮን ብር በላይ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆት ተፈጽሟል ........///......... በኦሮሚያ ክልል በሁለት ዓመት ተኩል ብቻ 76 ነጥብ 07 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ተቋሙ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት፤ በጸጥታ ሥጋቶች፣ በካሳ ክፍያ፣ በወሰን ማስከበርና ተያያዥ ጉዳዮች ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ምክክር አድርጓል፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የምክክሩን ዓላማ አስመልክተው እንደገለፁት በኃይል አቅርቦት ዘርፍ ተቋሙ እያከናወነ ያለውን ሰፊ የመሰረተ-ልማት ግንባታ እና የኦፕሬሽን ሥራዎች ለባለድርሻ አካላት በማስገንዘብ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ነው፡፡ የኤሌክትሪክ መሰረተልማት በሚገነባባቸውና በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የደህንነት ጥበቃ ከማድረግ ጀምሮ የካሳ ጥያቄዎች እና የወሰን ማስከበር ጉዳዮችን ለመፍታት ክልሎችና በየደረጃው የሚገኙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛህኝ በበኩላቸው በክልሉ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል ግንባታ ፕሮጀክቶች እና በተቋሙ ላይ እያጋጠሙ ስላሉ ችግሮች በዝርዝር ለክልሉ የሥራ ኃላፊዎች አብራርተዋል፡፡ ኃላፊው እንደገለጹት በክልሉ በ10 ቢሊዮን ብር ሁለት የኃይል ማመንጫ ፕሮጄክቶች እና ከ16 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በሚደርስ ወጪ ሰባት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ግንባታ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ በነባርና አዲስ በሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶች ላይ የሚፈጸሙ የስርቆት ወንጀሎች ተቋሙን ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረጉትና ፕሮጀክቶችንም እያጓተቱ ስለመሆኑን ገልጸዋል። ከ2016 በጀት ዓመት በፊት በነበሩ ሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ በስርቆት ብቻ 76 ነጥብ 07 ሚሊዮን ብር በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የጠቀሱት አቶ ሙላት የደረሠው ጉዳት ኃይል ባለመሸጡ የደረሠውን ኪሳራ አያካትትም ብለዋል። በተጨማሪም የወሰን ማስከበር ችግሮች እና ያልተገባ የካሳ ክፍያ መጠየቅ እንዲሁም በሠራተኞች ላይ የሚደርሱ የፀጥታ ስጋቶች በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ እንቅፋት እየፈጠሩ መሆኑን አስረድተዋል። ከክልሉ የተለያዩ ዘርፎች የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ተቋሙ ባነሳቸው ጉዳዮች ላይ ምላሽ ተሰጥተዋል። በምላሻቸውም በክልሉ ልማትን የሚያውኩ አሠራሮችን እንደማይታገሱና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ጥበቃ ከተቋሙ ጋር በቅንጅት እንደሚሠሩ ኃላፊዎች አረጋግጠዋል። የኦሮሚያ ክልል መሬት አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊና የህግና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ቢያ ራያ እንደገለፁት የሀገር ሀብት በሆኑ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን ለማስቀረት እና የሚታዩ የህግና አፈጻጸም ክፍተቶችን ለማረም ክልሉ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል። በክልሉ የልማት ተነሽዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ተስፋ በበኩላቸው ካሳ የተከፈለባቸውን የተቋሙ ይዞታዎች ለማስከበር እና ተገቢ ያልሆነ ካሳ በመጠየቅ ፕሮጀክቶችን የሚያጓትቱ አካሄዶችንም ለማረም ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ተቋሙ በክልሉ የሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ጥያቄዎች የሚመልሱ በመሆናቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በምክክሩ ማጠቃለያ እንደ ገለፁት ተቋሙ የሚያከናውናቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታዎች ኢኮኖሚያዊ፣ፓለቲካዊና ማህበራዊ ፋይዳቸው የላቀ በመሆኑ መንግስትና ህብረተሰቡ ጥበቃ ሊያደርጉላቸው ይገባል። እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለፃ ተቋሙ ከከልሉ መንግስት ጋር ተቀራርቦ በመስራት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማሳደግ ወደ ፊትም ትኩረት ሠጥቶ ይሠራል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋሙ የማማከር ሥራ ይሁንታ ከዓለም ባንክ አገኘ ………….///………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ላይ የኢንጂነሪንግ የማማከር ሥራዎችን በራሱ አቅም እንዲያከናውን ከባንኩ ይሁንታ ማግኘቱን በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮች ሲስተም ዲዛይን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ፍቃዱ እንደገለፁት ከዓለም ባንክ ጋር በተደረጉ ተደጋጋሚ ውይይቶች ተቋሙ የማማከር ሥራውን በራሱ አቅም እንዲያከናውን ከስምምነት ተደርሷል ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰርቬይንግ ፣ በቅድመ ዲዛይን፣ በቴክኒካል ስፔሲፊኬሽን ዝግጅት፣ በፍላጎት መግለጫ፣ በኮንትራት አስተዳደር እና የኮንስትራክሽን ቁጥጥር ሥራዎችን በራስ አቅም እንዲያከናወን ፈቃድ መገኘቱንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የኢንጂነሪንግ ዘርፉ የአቅም ማሳደጊያ ፕሮግራምን በመቅረፅ የተለያዩ ስልጠናዎችን ለባለሙያዎች እንዲሰጥ በማድረግና ፣የቴክኒካል ስፔሲፊኬሽን ዝግጅት ላይ የነበሩ ክፍተቶችን በማስቀረት እና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ለውጥ መታየቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የሳይት የግንባታ ቁጥጥር ሥራና የኮንትራክት አስተዳደር ሥራዎችን በተሻለ ቅልጥፍናና ወጥነት ባለው መልኩ ማከናወን መጀመሩን አስረድተው የኢንጂነሪንግ ክፍሉ በአዲስ መልኩ መደራጀት ለዚህ ስኬት እንዳበቃውም ገልፀዋል፡፡ በዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚሰሩ ፕሮጀክቶች እንደ ወራቤ ቡታጅራ የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፐሮጀክት፣ ፕሮቴክሽን ሪፍሬሽመንት ፕሮጀክት እና በራስ ፋይናንስ እየተሰሩ ባሉ ፕሮጀክቶች አፈፃፀማቸው ተገምግሞ በራስ የማማከር ዕድሉ እንደተገኘ አብራርተዋል፡፡ ተቋሙ ሙሉ የማማከር ሥራ ማግኘቱ የነደፈውን የሶስት ዓመት የስትራቴጂ ዕቅድ ለማሳካት እና የውጭ ምንዛሬን ለማዳን አስተዋጽዖ እንደሚኖረው አቶ ያሬድ አስረድተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥሯል ………..///………. የአሸጎዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅና ተቀጣሪዎች ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አብርሃም አባተ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በጥበቃና በተለያዩ የግንባታ ሥራዎች ለ70 ወጣቶች ጊዚያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። በመቐለ ከተማ ዙሪያ ነዋሪ የሆኑት አቶ ደስታ ገብሬ እንደተናገሩት ለብዙ ዓመታት በአናፂነት ሙያ ቢሰሩም የሚያገኙት ገቢ ከራሳቸው ልብስና ጉርስ አልፎ ቤተሰብን ለማገዝ ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር። የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ በአካባቢያቸው መጀመሩ የሥራ ዕድል ስለፈጠረላቸው የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደረዳቸው ተናግረዋል። በፕሮጀክቱ በመስራት ላይ የሚገኘው አቶ መሐሪ ግርማይ በበኩሉ እርሱና ቤተሰቡ ኑሯቸውን የሚገፉት በትንሽ የእርሻ ሥራ በሚያገኙት ገቢ እንደነበር ጠቅሶ ፕሮጀክቱ በአካባቢው ከተጀመረ ወዲህ ግን የሥራ ዕድል እና ተጨማሪ ገቢ ማግኘቱን ተናግሯል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚያከናውናቸው የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታዎች ለበርካታ ወጣቶች ቋሚና ጊዚያዊ የሥራ ዕድል እየፈጠረ ይገኛል። የአሸጎዳ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በህዳር ወር 2016 ዓ.ም የግንባታ ሥራው የተጀመረ ሲሆን በ8 ወራት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ትግበራ ፕሮጀክት አፈፃፀም ከ62 በመቶ በላይ ደርሷል ……....///…….... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጡ አገልግሎቶችንና አሰራሮችን ለማዘመን እየተከናወነ የሚገኘው የሳፕ ሲስተም ሁለተኛ ምዕራፍ ትግበራ አፈፃፀም 62 ነጥብ 2 በመቶ መድረሱ ተገለፀ። የተቋሙ ሥራ አመራር ከኢትዮጵያ አየር መንገድና ሲስተሙን ከሚያለማው የህንዱ ኦሬን ኩባንያ ጋር በሳፕ የትግበራ አፈፃፀም ዙሪያ ግምገማ አካሂደዋል። ግምገማው የመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ላይ የነበሩ ክፍተቶች የታረሙበትን ሁኔታ ለመረዳትና በሁለተኛው ምዕራፍ ላይ የአሰራር ሥርዓቱ የደረሰበትን የትግበራ ደረጃ ለማወቅ ያለመ ነው። በሁለተኛው የሳፕ ሲስተም የትግበራ ምዕራፍ የሚተገበሩ ሞጁሎችን አስመልክተው ማብራሪያ የሰጡት በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሳፕ ትግበራ አማካሪና የኦሬን ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ማኑቺ ጉፕታ እንደተናገሩት በቀጣይ 3 ወራት ፕሮጀክቱን አጠናቆ ወደ ትግበራ ለማስገባት እየተሰራ ነው። በሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ላይ በሚካተቱት የፋይናንስ፣ ሰው ኃይል አስተዳደርና ግዥ እንዲሁም ዕቃ ግምጃ ቤት ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያም ለሥራ አመራሩ ሰጥተዋል። በሲስተሙ ውስጥ አሪባ፣ ሰክሰስ ፋክተር፣ ፕላንት ሜንቴናንስ፣ ስፒር፣ ጂ.አር.ሲ የተሰኙ ሞጂሎች ተግባራዊ እንደሚደረጉ የገለፁት ሚስተር ማኑቺ ሞጁሎቹ ሙሉ በሙሉ መተግበር ሲጀምሩ የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን ጠቀሜታቸው የጎላ ነው ብለዋል። የፕሮሰስ ሞደርናይዜሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈለቀ አፈወርቅ በበኩላቸው በሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ አንዳንድ የሥራ ክፍሎች መረጃ በወቅቱ ባለመስጠታቸው በአሰራር ሥርዓቱ ትግበራ ላይ አሉታዊ ጫና መፍጠሩን ጠቅሰው ፕሮጀክቱን በተያዘለት ዕቅድ ለማጠናቀቅ የሥራ ክፍሎች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በግምገማው ወቅት የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ተቋሙን ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሥርዓት ለማሸጋገር እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎችን አድንቀዋል። የአሰራር ሥርዓቱን ወደ ትግበራ ለማስገባት የቀረው ጊዜ አነስተኛ ቢሆንም ለፕሮጀክቱ መሳካት ቅድሚያ በመስጠት መስራት ይገባል ብለዋል። ፕሮጀክቱን በተያዘለት መርሃ ግብር ለመተግበር እያንዳንዱ የሥራ ክፍል ቅድሚያ ሰጥቶ ሥራውን በተነሳሽነትና በቁርጠኝነት እንዲሰራም ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የሴቶችን አሳታፊነት እና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ……..///………. ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተለያዩ ሪጅኖች መከበሩን የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደተናገሩት የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ከዋና መ/ቤቱ በተጨማሪ በገናሌ ዳዋ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ፣ በደቡብ ምዕራብ ሪጅን፣ በመካከለኛ 1 እና 2 ሪጅኖች እና በደቡብ 1 ሪጅን በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ የተቋሙ ሴት ሠራተኞች ተፈጥሮአዊ እና ሌሎች ሰው ሰራሽ ልዩነቶች ሳያግዳቸው በአስቸጋሪ የሥራ ቦታዎች ጭምር ውጤታማ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ ሴት ሠራተኞች ያሉባቸው ችግሮች በዘላቂነት ተቀርፈው በሁሉም መስክ ተጣቃሚነታቸውን እና ተሳታፊነታቸውን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ በግንባር ቀደምትነት ተሰልፈው የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ በዓሉ በተለያዩ ትምህርታዊ ጉብኝቶችና ውይይቶች እንዲከበር ትብብር ላደረጉ የሥራ ኃላፊዎችም ዳይሬክተሯ ምስጋና አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው የማስፋፊያ ግንባታ 34 መቶ ተጠናቋል ……...///…….... የአሸጎዳ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ አፈፃፀም 34 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ አብርሃም አባተ እንዳስታወቁት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው እየተከናወነ የሚገኘው የማስፋፊያ ግንባታ የሲቪል ሥራ 30 ነጥብ 1 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራ 4 በመቶ ተጠናቋል። የኃይል ማስፋፊያ ሥራውን በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ነው የገለፁት። የሁለት ባዝባር ማስፋፊያ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች፣ የአጥር ሥራ፣ የፍሳሽ ውሃ ማስወገጃ ግንባታዎች በፕሮጀክቱ ከሚከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች መካከል እንደሚጠቀሱ ተናግረዋል። 40 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮችን የማስቀመጥ ሥራ መከናወኑን የገለፁት አቶ አብርሃም ትራንፎርመሮቹ 64 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም እንዳላቸውም ገልፀዋል። እንደ አቶ አብርሃም ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታው ሰባት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ ሲጠናቀቅ 70 ካሬ ለሚባለው የመቐለ ከተማ አዲስ መንደር፣ ለኢታካ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ፣ ለአዲጉዶም፣ ለሔዋኔ ከተማና አካባቢው እንዲሁም ወደፊት ለሚገነቡ የኢንዱስትሪ መንደሮች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የማስፋፊያ ፕሮጀክቱን በ8 ወራት ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ከ219 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መያዙንም ነው የጠቀሱት። የአሸጎዳ የማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ እያከናወነው ሲሆን ፓወር ቻይና የተሰኘ ኩባንያ በዕቃ አቅርቦት እየተሳተፈ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመ
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል አቶ አብርሃም አምባዬ በርሄ በተሰጠው የጽሁፍ እና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጡ በመሆኑ ከመጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ ዋናውን በመያዝ ቀርበው የቅጥር ሂደት እንዲፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

ተቋማቱ በጋራ ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ .......///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮ- ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። ውይይቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስተባባሪነት ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት መስራትና ልምዶችን መለዋወጥ እንዲችሉ ለማድረግ ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የውስጥ አቅምን በማጠናከርና ያሏትን ሃብቶች አሟጦ መጠቀም ይገባል። በአሁኑ ወቅት ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በአዲስ ራዕይና አመራር የተቋቋመ ተቋም በመሆኑ የመደገፍና ውጤታማ የሚሆንበትን ሁኔታ በማመቻቸት በጋራ ለመስራት ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የሁለቱ ተቋማት በትብብር መስራት የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለማስወገድ፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠርና ከውጭ ጥገኝነት ለመላቀቅ እንዲሁም የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ሚናው የጎላ መሆኑንም ነው ኢንጂነር አሸብር የገለፁት። በቀጣይም ተቋሙ ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የጥራት ደረጃቸውን ያሟሉ የኤሌክትሪክ ግብዓቶችን በጥናትና በዕቅድ ለይቶ ለመግዛት እንዲያስችለው የቴክኒክ ቡድን በማዋቀር  ወደ ሥራ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል። የኢትዮ- ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ በበኩላቸው ተቋማቸው ትልቅ ራዕይ ይዞ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ቢሆንም ከሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት ጋር በትብብር ካልሰራ ውጤታማ ሊሆን አይችልም። ሁለቱ ተቋማት የሚያጋጥማቸውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ችግር ለመቅረፍ በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አምባሳደር ሱሌማን ተናግረዋል። ተቋሙ ወደፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች ባሻገር ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት ማቀዱንም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለፁት። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገረመው ቀኖ እንደተናገሩት የሁለቱ ተቋማት ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል አመራሩ ቁርጠኛ ሊሆን ይገባል። አስተዳደሩ በተቋማት መካከል የሚፈጠሩ ቅንጅታዊ አሰራሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያከናውንም ነው አቶ ገረመው ያመለከቱት። በውይይቱ ላይ ሁለቱ ተቋማት የቀድሞ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ብረታ-ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ወይም ሜቴክ ከተቋሙ ጋር ለነበረው ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ ባስገባቸው ብረታ-ብረቶች፣ ማሽነሪዎች እና ተሽከርካሪዎች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይም መክረዋል። በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውስጥ በሚገኙ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ የሌላቸው ተሽከርካሪዎች ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር እገዛ እንዲያደርግ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

ተቋሙ የነደፈውን ዕቅድ ለማሳካት የሴቶችን እምቅ አቅም ሊጠቀም ይገባል …………///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ113ኛ፣ በአገር አቀፍ ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን "ሴቶችን እናብቃ፤ ሰላምና ልማትን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ቃል በተቋም ደረጃ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብረዋል፡፡ በመርሀግብሩ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ባስተላለፉት መልዕክት በተቋሙ ሁሉም የሥራ ክፍሎች ያሉ ሴቶችን ተሳትፎ የሚገድቡ ማናቸውንም እንቅፋቶች በማስወገድ የሥራ ቦታዎች ከጾታ መድሎ የጸዱ፣ አካታችና አሳታፊ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ሴቶች ችሎታቸውን እንዲያጎለብቱ ዕድል መስጠቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ያሉት ኢንጂነር አሸብር አንድ ተቋም የሚጠበቅብንን ስኬት ለማስመዝገብ የሴቶችን እምቅ አቅም መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በተቋም ደረጃ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሲከበር የተቋሙ ሴት ሠራተኞች በሁሉም ዘርፍ ራሳቸውን እንዲያሳድጉና አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት በማስቀጠል ሊሆን እንደሚገባል ገልፀዋል፡፡ በዓሉን የተመለከተ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት በተቋሙ የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መመሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው ሴቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች ለመቅረፍ የሁሉም ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል። በጽሁፉ ሴቶች ሥለራሳቸው ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ እምቅ አቅማቸውን የሚጠቀሙበትን አውድ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን በጽሁፋቸው አመልክተዋል፡፡ በተቋሙ የሴቶችን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ የተሰሩ ሥራዎችን በተመለከተ የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን የሴቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆናቸው ተገልጿል፡፡ ለሴቶች በቅጥር፣ በልዩ ልዩ ሥልጠናዎች፣ በነጻ የትምህርት እድል እና በደረጃ ዕድገት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው በሕብረት ስምምነቱ መካተቱን በውይይቱ ላይ ተነስቷል፡፡ ተቋሙ እየተገበረ ባለው የስትራቴጅክ ዕቅድ ላይ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች ታቅደው እየተከናወኑ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የዝግጅቱ ተሳታፊዎችም በተቋሙ የህፃናት ማቆያ መቆቋሙ የሴቶችን ጫና በማቃለል በኩል ያለውን መልካም ጅማሮ አድንቀው በቀጣይ በተቋም የሴቶችን ተጠቃሚነትና የአመራር ሰጭነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የተቋሙ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ ተቋማት የስኬት ሽልማት ተሸላሚ ሆነ …….….///……….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ ተቋማት የስኬት ሽልማት ተሸላሚ ሆነ፡፡ በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደ የስኬት ሽልማት ሥነ ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ጨምሮ ለአምስት ተቋማት ሽልማት አበርክተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሽልማቱን ባበረከቱበት ወቅት እንደተናገሩት ተቋማቱ በሀገር ብቻ ሳይሆን በአህጉር ደረጃ ባላቸው የመወዳደር አቅምና ባስገኙት ውጤት ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በአፍሪካ አንደኛ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ከፍተኛ ፈተና የገጠመው እንደሆነ ጠቁመው ፕሮጀክቱ ፈተናውን ተቋቁሞ የኢትዮጵያዊያንን ቁጭትና የመልማት ፍላጎት እያሳካ ይገኛል ብለዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ብዙ ያልተነገሩ ታሪኮችና ምስጢሮችን በውስጡ ስለያዘና በአፍሪካ የመጀመሪያው ስለሆነ ተሸላሚ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፃ ፕሮጀክቱ ቀደም ሲል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ቢያልፍም ባለፉት ዓመታት ችግሮችን ለመፍታት በተሰጠው አመራር ውጤታማ ሆኗል፡፡ ሽልማቱን የተቀበሉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው የላቁ ተቋማትን መሸለም ለተሻለ ሥራ ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ከማድረጉም ባለፈ በቀጣይ ለሌሎች መነሳሳትን የሚፈጥር ነው፡፡ ዕውቅናው በፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራ ላይ በተሰማሩት ስም የተበረከተ ቢሆንም ፕሮጀክቱን ለስኬት ላበቁት ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን የተሰጠ ነው ብለዋል፡፡ ሽልማቱ ፕሮጀክቱን በትጋት በማጠናቀቅ የኢትዮጵያዊያን ተስፋ የሆነውን ግድብ ዕውን ለማድረግና በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለማከናወን እንደሚያነሳሳም ጠቁመዋል፡፡ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በተጨማሪ የግብርና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የኢትዮጵያ ተቋማት የስኬት ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2