en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 546 subscribers, ranking 8 351 in the Technologies & Applications category and 2 178 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 546 subscribers.

According to the latest data from 02 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 27 over the last 30 days and by 8 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.76%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.84% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 005 views. Within the first day, a publication typically gains 2 463 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 546
Subscribers
+824 hours
-227 days
+2730 days
Posts Archive
photo content

በተጀመረው የመልሶ ጥገና ሥራ ሪጅኖች ያላቸውን የትብብር መንፈስ አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ተባለ ………//////………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ ዘርፍ በምስራቅ ሪጅን ድሬዳዋ ከተማ ሲያካሂድ የቆየውን የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አጠናቋል። ግምገማው የሩብ ዓመቱን የሪጅኖች አፈፃፀም የተመለከተ ሲሆን አብዛኛዎቹ ሪጂኖች ወቅቱን የጠበቀ ዕቅድና ሪፖርት አዘጋጅቶ ከመላክ፣ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በትክክል ተጠቅመው ሥራቸውን ከመከወን እንዲሁም የሥራ ሰዓትን ከማክበር ጋር ተያይዞ የታዩ ድክመቶች ስለተስተዋሉባቸው በቀጣይ እንዲታረሙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡ በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት ሁሉም ሪጅኖች ያላቸውን የትብብር መንፈስ በማጠናከር ሥራዎችን በጋራ በማከናወን የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በጦርነቱ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለማገናኘት በሚደረገው ርብርብ የታየው ቅንጅታዊ አሰራር የሚደነቅ እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስፈጻሚው አሁን በተጀመረው የመልሶ ጥገና ሥራ ትብብሩ ሊደገም ይገባል ብለዋል። የማህበረሰቡን ዕሴት በመጠቀም እና መስመሮች በሚያልፉባቸው አካባቢዎች የሚኖረውን ህብረተሰብ ኃላፊነት በመስጠት በኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚደርሱ ስርቆቶችን ለመከላከል በምዕራብ እና ደቡብ ሪጅኖች የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎችን በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት እንደሚገባ አቶ ሀብታሙ አሳስበዋል። በማከፋፋያ ጣቢያዎች ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር በምስራቅ ሪጅን የተሰሩት መንገዶች፣ ችግኞችን በመትከል የተከናወነው የማስዋብ ሥራ እና በድሬዳዋ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ የተገነባው የመኪና እጥበት አገልግሎት መስጫ (ላቪያጆ) ለሌሎች ሪጅኖች ትልቅ ማስተማሪያ እንደሆኑ ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል። የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው የሥራ ዘርፉ ያደረገው ግምገማ ትልቅ መማማር እና የልምድ ልውውጥ የታየበት እንደነበር አንስተዋል። ማህበሩ ሠራተኛው የሚያነሳቸውን የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎች በህብረት ስምምነቱ መሠረት ምላሽ እንዲያገኙ በማድረግ እና በተቋሙ እና በሠራተኛው መካከል ያለው መልካም ግንኙነት ተጠናክሮ ውጤት እንዲመጣ እንደሚሰራ ገልፀዋል። ለሦስት ቀናት በቆየው ግምገማ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሥራዎች እና ተቋማዊ የጎንዮሽ ጉዳዮችን በመገምገም ከሰው ሀብት፣ ከንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት፣ ከፋይናንስ እና ከፕላኒንግ ዘርፍ ጋር የሚያያዙ ጥያቄዎችን በማንሳት ከዘርፉ ሥራ አስፈፃሚዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 13 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+7

በድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የተከማቹ ተቀጣጣይ ቁሶች ወደሌላ ቦታ እንዲዛወሩ ጥያቄ ቀረበ ………../////……….. በድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀጣጣይ ነገሮችን በአንድ ቦታ ማከማቸት ተገቢ ባለመሆኑ ከጣቢያው እንዲወጡና ወደሌላ ቦታ እንዲከማቹ ማድረግ ይገባል ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጀዋር አሳሰቡ፡፡ ከንቲባ ከድር ጀዋር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ ጋር ለህብረተሰቡ እና ለኢንደስትሪዎች ያልተቆራረጠ ኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ በሚቻልበትና ከከተማ አስተዳደሩ በሚፈለጉ ድጋፎች ዙሪያ መክረዋል፡፡ አቶ ሀብታሙ ለከንቲባው እንደገለፁት ድሬዳዋ የኢንዱስትሪ ማዕከል ስለሆነች በከተማዋ ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ ጉዳዮችን ለመለየትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መፍትሔ ለመስጠት ድረገጽን መሰረት ያደረገ መተግበሪያ በተቋሙ እንዲበለፅግ ተደርጓል፡፡ በከተማዋ ያሉት የማከፋፈያ ጣቢያዎች ያሉበትን ሁኔታ በማብራራት እንዲመለከቷቸውም ጋብዘዋቸዋል፡፡ አብዛኛውን የከተማዋን ኃይል እያቀረበ በሚገኘው የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተጠራቀሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገለገሉ የእንጨት ምሰሶዎች እና በአስር ሺህ ሊትሮች የሚገመት ናፍጣ ለጣቢያው ስጋት በመሆኑ ችግር ከማስከተሉ በፊት ወደሌላ አካባቢ እንዲዛወር ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው እንዲሁም ከተማውን የሚመጥን የሪጅን ቢሮ ህንፃ በድሬዳዋ ቁጠ ር 3 ግቢ ውስጥ ለመገንባት ፍቃድ ጠይቀዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር በሥራ አስፈፃሚው የቀረበውን ጥያቄ ካደመጡ በኋላ ለውሳኔ እንዲረዳቸው ችግሩን ማየት እፈልጋለሁ በማለታቸው የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ባሉበት ማከፋፈያ ጣቢያዎቹን ጎብኝተዋል፡፡ በድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀጣጣይ ነገሮችን በአንድ ቦታ ተከማችተው መቀመጣጣቸው ለጣቢያው ደህንነት አስጊ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዎቹ ተቀጣጣይ ቁሶቹ ከጣቢያው መውጣት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡ ተቋሙ በከተማዋ የሪጅን ቢሮ ግንባታ እንዲጀምርም አስተዳደሩ ፍቃደኛ መሆኑንና አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎችን ለማነጋገር ቀጠሮ እንይዛለን ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት (ቢ ኤስ ሲ) የሠራተኛውን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚተገበር መሆኑን መረዳት ይገባል …….///……. የውጤት ተኮር ሥርዓት (ቢ ኤስ ሲ) ትግበራ ሠራተኛውን በሥራው ልክ መዝኖ ውጤት ለመስጠት፣ ለማበረታታትና ለማሻሻል እንዲሁም ያሉበትን ውስንነቶች ለማስተካከል እንጂ ሠራተኞችን ለመጉዳት እንዳልሆነ ሁሉም ሊያውቀው ይገባል ተባለ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ የውጤት ተኮር ሥርዓት ያለበትን ደረጃ ከሪጅን ዳይሬክተሮች ጋር ገምግመዋል፡፡ አቶ ሀብታሙ በግምገማው ላይ እንደገለፁት በዘርፉ ያለው ሠራተኛ ውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓትን ለመተግበር ጥሩ ጅምሮች ቢያሳይም አብዛኛው ሠራተኛ ግን ጥቅሙን ባለመረዳት ሠራተኛን ለመጉዳት የተቀመጠ አሰራር አድርጎ የማየት አዝማሚያ እየተስተዋለ ነው፡፡ በመሆኑም እየታየ ያለው የተሳሳተ አመለካከት መስተካከል አለበት ያሉት ሥራ አስፈጻሚው የምዘና ሥርዓቱ በተቃራኒው ሠራተኛውን ለማሻሻል ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የሁሉም ሪጅን ዳይሬክተሮች ለሠራተኛው ስለ ውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት ግልጽነት በመፍጠር እና ሥራዎችን ወጥ በሆነ መንገድ አቅዶ በመስጠት ተጠያቂነት ሊያሰፍኑ ይገባል። የውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት ፅንሰ ሀሳብን በአግባቡ ተረድቶ ተግባራዊ ለማድረግ የአቅም ውስንነት መኖር፣ ውጤቱን ለመለካት የሥራው ባህርይ አስቸጋሪ መሆን እና የስልጠና፣ ክትትልና ድጋፍ ማነስ በአብዛኞቹ ሪጅኖች ሥርዓቱን በትክክል ለመተግበር አለመቻል እንቅፋት መሆናቸውን የየሪጅኖቹ ዳይሬክተሮች በግምገማው ላይ አንስተዋል። በተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በግምገማው ላይ ተገኝተው ሪጅኖች እንደ ክፍተት ላነሷቸው ሀሳቦች ማብራሪያ ሰጥተዋል። አቶ አታላይ በማብራሪያቸው ከውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት ሥርዓቱን በሚገባ ተግባራዊ ለማድረግ ለዘርፉ ሠራተኛ በየደረጃው ሥልጠና መስጠትና ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል ። ሠራተኛው የሚሰጠውን የአቅም ግንባታ ሥልጠና በንቃት ተከታትሎ በተግባር ላይ ማዋል ይጠበቅበታል ሲሉም ተናግረዋል። ከዚህ በኋላ የሚደረጉ የዕድገት፣ ጭማሪና የማትጊያ ጥቅማጥቅሞች ሠራተኛው በውጤት ተኮር የምዘና ሥርዓት ተመዝኖ በሚያገኘው ውጤት እንደሚመሰረቱ አቶ አታላይ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ህብረተሰቡ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ንክኪ እንዲርቅ ተጠየቀ ………////…….. የኢትዮ ኬንያ ባለ 5 መቶ ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በቅርብ ጊዜ ኃይል ማስተላለፍ ስለሚጀምር ህብረተሰቡ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ንክኪ እንዲርቅ ተጠየቀ፡፡ በመስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ሊጀመር መሆኑን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የተመራ ቡድን በደቡብ ክልል ከጋሞ ዞን አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ በጋሞ ዞን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀመው ስርቆት እየቀነሰ ቢመጣም አሁንም ክትትል የሚያስፈልገው ስለመሆኑ ለአመራሮቹ ተገልጾላቸዋል፡፡ በቀጣይም በዞኑ መሰረተ ልማቱ በሚያልፍባቸው አካካቢዎች ምንም ዓይነት ስርቆት እንዳይከሰት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንዲሰራ፣ የፀጥታ አካላትም ተንቀሳቅሰው እንዲጠብቁና ህብረተሰቡ በይዞታው ላይ የተተከሉትን ምሰሶዎች እንዲጠብቅ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንዲሰራ ጥያቄ ቀርቦ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የወሰን ማስከበር ሥራን በተመለከተም በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ 18 ቤቶች ካሳ ተከፍሏቸው አለመነሳታቸው በውይይቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ መስመሩ በሚያልፍባቸው የአርባምንጭ ከተማ የማስፋፊያ አካባቢዎች በዲዛይንም ሆነ በግንባታ ወቅት ያልነበሩ ቤቶች በህገወጥ መንገድ በመገንባታቸው ኃይል ማስተላለፍ ከመጀመሩ በፊት በፍጥነት እንዲነሱ አቶ ክብሮም ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ የየዞኖቹ አመራሮች በሰጡት ምላሽ ካሳ ተከፍሎባቸው ያልተነሱትን ቤቶች ምትክ ቦታ በማዘጋጀት በአስቸኳይ እንዲነሱ ለማድረግ የዞኑ ልዩ አማካሪ ጉዳዩን ተከታሎ እንዲያስጨርስ መመሪያ ተሰጥቷል፡፡ በአርባምንጭ ከተማ ዙሪያ የተገነቡት ህገወጥ ቤቶችን በተመለከተ ነዋሪዎቹን በማሳወቅ ከመስመሩ ሥር በአስቸኳይ እንዲነሱ እናደርጋለን ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡም መስመሩ ኃይል ያልተለቀቀበት መስሎት በመዘናጋት ጉዳት እንዳይደርስበት በህዝብ መድረክ፣ በማህበራዊ ሚዲያ እና ለነዋሪዎች ተደራሽ በሆኑ ዋና ዋና ሚዲያዎች ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ከወላይታ ዞን አመራሮች ጋርም ተመሳሳይ ውይይት መደረጉን አስቀድመን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

የኢትዮ ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ሊጀምር ነው፤ ህብረተሰቡም ራሱን እንዲጠብቅና እንዳይዘናጋ ማድረግ ይገባል ተብሏል ………////…….. የኢትዮ ኬንያ ባለ 5 መቶ ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት ውስጥ ኃይል ማስተላለፍ ሊጀምር ነው፡፡ በመስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ሊጀመር መሆኑን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የተመራ ቡድን በደቡብ ክልል ከወላይታ ዞን አስተዳዳሪና የመምሪያ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ በመሰረተ ልማት ስርቆት፤ ወሰን ማስከበርና የግንዛቤ በማስጨበጫ ሥራዎች ላይ ባተኮረው ውይይት መስመሩ ለሁለቱ ሀገራት የኃይል ትስስር እና ለሀገራችን ኢኮኖሚ ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑን አቶ ክብሮም ለአመራሮቹ ገልፀውላቸዋል፡፡ በዞኑ የኃይል ተሸካሚ ማማ ብረቶች በተደጋጋሚ መሰረቃቸውና ለመስመሮች ደህንነትና ለኮሙዩኒኬሽን የተዘረጋው ኦፕቲካል ግራውንድ ፋይበር እና ፋይበር ኦፕቲክስ መገናኛ ሳጥኖች በዘራፊዎች መወሰዳቸውን አስረድተዋል፡፡ ስርቆቱ በሚደጋገምባቸው አካባቢዎች እስከ 6 ሜትር ከፍታ ብረቶቹን የመበየድ ሥራ ቢሰራም ስርቆቱ አሁንም አለመቆሙን ገልፀዋል፡፡ እጅ ከፍንጅ በሚያዙ ወንጀለኞች ላይ የሚወሰደው የህግ እርምጃም ከሚደርሰው ሀገራዊ ጉዳት አንፃር ተመጣጣኝ አለመሆኑ በውይይቱ ላይ ተነስቶ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የወሰን ማስከበር ሥራን በተመለከተም በዞኑ 5 ቤቶች ካሳ ተከፍሏቸው ያልተነሱ መኖራቸው የተነሳ ሲሆን የዞኑ አመራሮች ካሳ ለተከፈላቸው ቤቶች ምትክ ቦታ በማዘጋጀት በአስቸኳይ እንዲነሱ እንደሚደረግ ቃል በመግባት ቤቶቹ የሚገኙበት ወረዳ አስተዳዳሪ ውሳኔውን እንዲያስፈጽሙ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ህብረተሰቡም መስመሩ ኃይል ያልተለቀቀበት መስሎት በመዘናጋት ጉዳት እንዳይደርስበት በህዝብ መድረክ፣ በማህበራዊ ሚዲያ እና ለነዋሪዎች ተደራሽ በሆኑ ዋና ዋና ሚዲያዎች ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በተያያዘ ዜና በፕሮጀክቱ ሥራ መጀመር ዙሪያ ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተመሳሳይ ውይይት መደረጉን አቶ ክብሮም ገልፀዋል፡፡ ምንም እንኳ ፕሮጀክቱ በሚያልፍበት የቦረና ዞን ከስርቆትም ሆነ ከካሳ ማስከበር ጋር የተያያዘ ችግር ባይኖርም እረኞች ኢንሱሌተሮችን ለጨዋታ በሚል እየሰበሩ በመሆናቸው ድርጊቱን ለማስተው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር እንዲሰራ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በተመሳሳይ ጉዳይ ከደቡብ ክልል አመራሮች ጋር ለመነጋገር ለዛሬ ቀጠሮ መያዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+7

የኢትዮ-ጂቡቲ ሁለተኛ ሰርኪዩት የኃይል ትስስር መስመር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ተጀመረ ……..////……… የኢትዮ-ጂቡቲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ሁለተኛ ሰርኪዩት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ፡፡ ግንባታው በይፋ መጀመሩን ለማብሰር በተዘጋጀው መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ ማስገኛ ሲሆን ለጅቡቲ ደግሞ በተመጣጣኝ ዋጋ ኤሌክትሪክ በማግኘት የሀገሪቱን ኢንዱስትሪ ለማነቃቃት እና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ቀጣናዊው የኃይል ትስስሩን የሚያሳልጥ እና ሁለቱን ጎረቤት ሀገራት በኤሌክትሪክ እና በትራንስፖርት የጀመሩትን ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን የጅቡቲ አሌክትሪክ ተቋም ያሳየው ተነሳሽነት እና ድጋፍ የሚመሰገን ነው ብለዋል፡፡ የጅቡቲ ኤሌክትሪክ ተቋም ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አቡበከር ሀሰን በበኩላቸው የመጀመሪያው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከፍተኛ የኃይል ጫና እየደረሰበት በመሆኑ ሁለተኛው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ፕሮጀክት ለጅቡቲ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በተመጣጠነ ዋጋ ለህብረሰተባቸው ያልተቆረረጠ ኃይል ተደራሽ በማድረግ እና በሀገራቸው ያለውን የኃይል አቅርቦት እጥረት በመቅረፍ በኩል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብነት አህመድ እንደተናገሩት ከድሬዳዋ ተነስቶ ወደጅቡቲ የተዘረጋው መስመር ከአስር ዓመታት በላይ በማገልገሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጫና እየደረሰበት በሚፈለገው መጠን ኃይል ለማቅረብ አስቸጋሪ እየሆነ በመምጣቱ ሁለተኛውን ሰርኪዩት መገንባት አስፈልጓል፡፡ ነባሩ መስመር 54 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለጂቡቲ በማቅረብ መጀመሩን ያስታወሱት አቶ አብነት በ2014 ዓ.ም. ኃይል የማቅረብ አቅሙ ወደ 611 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማደጉን አስረድተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በኮምቦልቻ 2 እና በሠመራ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ግንባታ የሚኖረው ሲሆን በሚሌ ከተማ ደግሞ አንድ ባለ 230 ኪቮ አዲስ ማከፋፈያ ግንባታ ሥራ ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም ከኮምቦልቻ 2 እስከ ሠመራ ድረስ ያለውን ነባሩን 170 ኪ.ሜ የባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር የማጠናከር፣ ከሠመራ እስከ ጂቡቲ ድንበር ደግሞ የ290 ኪሜ ርዝመት ያለው አዲስ የባለ 230 ኪሎ ቮልት የመስመር ዝርጋታ ሥራዎች እንደሚሰሩ አቶ አብነት ገልፀዋል፡፡ 240 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፍ አቅም የሚኖረውን ፕሮጀክት የሁለቱ ሀገራት መንግስታት በድንበሮቻቸው ውስጥ እንደሚገነቡት ሥራ አስኪያጁ አብራተዋል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል የሚከናወነውን ግንባታ ለማጠናቀቅ የሚያስፈልገው 71 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሙሉ በሙሉ ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ ብደር የሚሸፈን ነው፡፡ የኢትዮ-ጂቡቲ ሁለተኛ ሰርኪዩት የኃይል ትስስር መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፣ ከዓለም ባንክ እና ከጂቡቲ የተወጣጡ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

የኃይል ተሸካሚ አካላት ስርቆትን ለመከላከል የህብረተሰቡን ዕሴቶች መጠቀም ይገባል …….////…….. በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የኃይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ዝርፊያ እየጨመረና አገልግሎት አሰጣጡን እያስተጓጎለ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሪጅን ኃላፊዎች ገለፁ፡፡ ዘርፉ የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈፃፀሙን በድሬዳዋ ሲገመግም ኃላፊዎቹ እንደገፁት በተለያዩ አካባቢዎች በዘራፊዎች የተፈታቱትንና ሳይወድቁ ጥገና የተደረገላቸውን የኃይል ተሸካሚ ማማዎች ሳይጨምር ስድስት ማማዎች ሙሉ በሙሉ በዘራፊዎች ተፈታተው ወድቀዋል፡፡ ይህም ለኃይል መቋረጥና ብክነት እንዲሁም ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ እንደዳረገው በመድረኩ ላይ ተጠቅሷል፡፡ የግምገማው ተሳታፊዎች እንዳነሱት የኃይል ተሸካሚ ማማዎች ስርቆት ሳይፈፀምባቸው ለመከላከል እንዲቻል ከተለያዩ የማህበረሰብ አደረጃጀቶችና ከመስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ ቢሆንም የወንጀል ድርጊቱ ግን ሊቆም አልቻለም፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚፈፀመው ስርቆት ኃይል እንዲቋረጥ ከማድረግ ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በሚያበረክቱ ግዙፍ ፋብሪካዎች እንቅስቃሴና ምርት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየፈጠረ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና ከህብረተሰቡ፣ ከመስተዳድር እና ከፀጥታ አካላት ጋር በቅርበት ለመስራት የተጀመረው እንቅስቃሴ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተሳታፊዎቹ ገልፀዋል፡፡ በደቡብ ምዕራብ ሪጅን ጅማ ዞን ሰኮሩ ወረዳ የተፈፀመ የኃይል ተሸካሚ ማማ ስርቆትን ማህበረሰቡን በማሳተፍ ወንጀል ፈፃሚዎችን ለህግ ማቅረብ መቻሉ፤ በምስራቅ ሪጅን ሶማሌ ክልል በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት ጋር ተነጋግሮ ግንዛቤ በመፍጠር ስርቆቱን ማስቆም መቻሉ፣ በደቡብ ሪጅን ሻሸመኔ አካባቢ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅርበት መስራት በመጀመሩ ለውጥ እየመጣ መሆኑ፣ በሰሜን ምዕራብ ሪጅን ከክልል መስተዳድር ጀምሮ እስከ ወረዳ ድረስ በጋራ መስራት መጀመሩ በመልካም ጎን ተነስተዋል፡፡ በአንፃሩ በአዲስ አበባ ሪጅን ቦሌ ለሚ አካባቢ ተደጋጋሚ ስርቆት ቢኖርም ከክፍለ ከተማ አመራሮች እና የፀጥታ አካላት ተገቢው ድጋፍ እየተገኘ ስላለመሆኑ፣ በማዕከላዊ ሪጅን ሆለታ፣ ወለንኮሚና ሞጆ አካባቢ ስርቆቱ አሳሳቢ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በሰጡት ምላሽ የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው ሪጅኖች ልምድ በመውሰድ የኃይል ተሸካሚ አካላት ስርቆትን ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል፡፡ የተቋሙ መሰረተ ልማት በአብዛኛው በበረሃ፣በተራራማ አካባቢና ከመኖሪያ አካባቢ ርቆ የሚገኝ በመሆኑ በሁሉም አካባቢ ጥበቃ ማስቀመጥ የሚቻል ባለመሆኑ ወደፊት በቴክኖሎጂ በመታገዝ የጥበቃ ሥራውን ለመስራት መታሰቡን ጠቁመዋል፡፡ ይሁንና ቴክኖሎጂው እስኪተገበር ድረስ በደቡብ ምዕራብ ሪጅን ጅማ ዞን ሰኮሩ ወረዳ እንደተጀመረው የህብረተሰቡን ዕሴቶች በመጠቀም ስርቆትን መከላከልና ወንጀል ፈፃሚዎችን ለህግ የማቅረብ ሥራው በሁሉም አካባቢ እንዲተገበር አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ማቅረብ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ውይይት ተካሄደ ......../////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሐረርና የጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ብዙ ሥራዎችን ሰርቶ መፍትሔ እየሰጠ ቢሆንም ተጨማሪ የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን እንዲሰራ የሐረሪ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠየቀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ የተመራ ቡድን ከሐረሪና ሶማሌ ክልሎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ከጭሮ ዲስትሪክት የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ማቅረብ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል። የሐረሪ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፈሪድ አብዱልሰላም እንደገለፁት ከሁርሶ - ድሬደዋ - ሐረር በተዘረጋው መስመር ላይ ችግር ሲያጋጥም እስከ ጅግጅጋ ችግሩ ስለሚዘልቅ ዘላቂ መፍትሔ እንዲበጅለት ጠይቀዋል። በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ 12 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም የነበረውን ትራንስፎርመር ወደ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር የማሳደግ ሥራ ቢሰራም ብሬከሮችና ተጨማሪ ወጪ መስመሮች ስላልተዘጋጁ ችግሩ ሙሉ በሙሉ አልተቀረፈም ብለዋል። በሐረር ከተማ ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት መኖሩን የጠቀሱት የሪጅኑ ሥራ አስፈፃሚ የሐረር ሪፈራል ሆስፒታል እስከ አራት ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል ስለሚፈልግ እና የሐረር መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ራሱን የቻለ መስመር ቢዘረጋለት ብዙ ችግር ስለሚቀርፍ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቴክኒክ እገዛ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። የሶማሌ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ካሊድ ጠሃ በበኩላቸው በጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የተሰራው የማስፋፊያ ሥራ ብዙ ችግሮችን መቅረፉን ጠቅሰው በሁለቱ ተቋማት መካከል በቅርበት መስራቱም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በኦሮሚያ ክልል የኤሌክትሪክ አገልግሎት የጭሮ ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ ድሪባ ተሾመ ዲስትሪክቱ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በማንሳት ድጋፍ እንፈልጋለን ያሏቸውን ጉዳዮች ዘርዝረዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በሰጡት ምላሽ ለአዲሱ ትራንስፎርመር አራት አዳዲስ ብሬከሮች እንደሚተከሉ ገልፀዋል። ሲስተሙን አስተማማኝ ለማድረግና መቆራረጡን የሚቀንስ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ተጨማሪ ጥናቶች መደረግ ይኖርባቸዋል ያሉት ሥራ አስፈፃሚው በሁለቱ ተቋማት በጋራ እና በተናጠል የሚሰሩ ሥራዎች ተለይተው ሥራዎች በኃላፊነት ሊከናወኑ ይገባል ብለዋል። በከተሞች አካባቢ የሚስተዋለው የኃይል አቅርቦት ችግር ከፍተኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ብቻ የሚቀረፍ ባለመሆኑና እንደተቋምም ሆነ እንደሀገር ወጪው ከፍተኛ ስለሆነ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንቨስት ያደርጋል ብሎ መጠበቅ እንደማይገባ አስታውቀዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ባለ 45 እና 66 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በመገንባት የሚቀረፉ ችግሮችን በመለየት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተሰጠው ኃላፊነት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ትኩረት መስጠት ይኖርበታል። በሪጅኖቹ በአብዛኛው ከሾርት ሰርኪዩት ጋር የተያያዘ የኃይል መቆራረጥ እንደሚደጋገም የጠቀሱት ሥራ አስፈፃሚው ተደጋጋሚ ችግር ያለባቸው መስመሮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ በበኩላቸው የሐረርና የጅግጅጋ ከተሞችን የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ትልልቅ የማስፋፊያ ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በከተሞቹ በሚገኙት የማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራሸሲሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሶማሌ ሪጅን ከፍተኛ ድጋፍ በማድረጉ ሪጅኑና ክልሉን አመስግነዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከድሬዳዋን ሪጅን ጋርም ተመሳሳይ ውይይት ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 09 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ የ2015 ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ጀመረ ......../////.......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ የ2015 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አፈጻጸሙን በምሥራቅ ሪጂን ድሬዳዋ ከተማ መገምገም ጀምሯል። ከጥቅምት 9 እስከ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ግምገማ ላይ የሁሉም ሪጅኖች የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ የተገኙ መልካም አጋጣሚዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች በዝርዝር ቀርበው ውይይት እንደሚካሄድባቸው ይጠበቃል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ ገየግምገማ ሂደቱን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት በሦስቱ ቀናት ለትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ አጋዥ የሆኑ የሥራ ክፍሎች ቅንጅታዊ አሰራር ምን እንደሚመስል ከየዘርፉ ተወካዮችና ሥራ አስፈፃሚዎች ጋር ውይይት ይደረጋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድሬዳዋን ጨምሮ ከአራት የአገልግሎቱ ሪጅኖች ጋር በአካባቢው አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ማቅረብ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ለማድረግ መታቀዱም ተጠቁሟል። በምስራቅ ሪጅን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት የሚፈፀሙ ስርቆቶችን በጋራ ለመከላከል ከከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር ምክክር ለማድረግ ቀጠሮ ስለመያዙም ተገልጿል። በግምገማው ማጠናቀቂያ ላይ ምቹ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር አኳያ ልምድ ይሆናሉ የተባሉ የተመረጡ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በመገባደድ ላይ በሚገኘው በአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጉብኝት እንደሚካሄድ ይጠበቃል። በሩብ ዓመቱ ግምገማ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ ሲሆኑ በግምገማው ላይ የየሪጅኖቹ ዳይሬክተሮችና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 09 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

photo content