en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 544 subscribers, ranking 8 333 in the Technologies & Applications category and 2 158 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 544 subscribers.

According to the latest data from 27 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by -16 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.06%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.33% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 895 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 7.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 544
Subscribers
-1624 hours
-97 days
+1030 days
Posts Archive
photo content

photo content
+7

photo content
+9

የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ተማሪዎችን አስመረቀ ...///... የጊቤ-3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ያሰለጠናቸውን 27 ወንድ እና 2 ሴት ሠራተኞች በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በማመንጫ ጣቢያው ግቢ ውስጥ አስመርቋል። በዛሬው ዕለት የተመረቁት የጣቢያው ሠራተኞች በዩኒቨርስቲው የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በተከታታይ የትምህርት መርሀ-ግብር ፕሮግራም በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ( ፓወር ስትሪም) ለ5 ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለዋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስላለፉት የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሃብታሙ አበበ ዩኒቨርስቲው ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ የማህበረሰቡን ችግሮች የሚፈቱ፣ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ንቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን እያፈራ ይገኛል። ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የትምህርት መስኮችን በመቅረፅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ የጠቀሱት ፕሬዚዳንቱ በጊቤ 1፣ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እየተማሩና እየተመረቁ የሚገኙ ሠራተኞች ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል። እንደ ዶ/ር ሃብታሙ ገለፃ ዩኒቨርስቲው በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ እያከናወናቸው በሚገኙ የመማር ማስተማር ሒደቶች ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያልተቋረጠ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎችን ሲያደርግ በመቆየቱ ምስጋና ይገባዋል። በዛሬው ዕለት ለምረቃ የበቁት ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ሙሉ በሙሉ ማለፍ መቻላቸውንም ነው የገለፁት። በዩኒቨርቲው የፖወር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ እንዲከፈት መሠረት የጣሉትና በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ትምህርቱ እንዲሰጥ የዩኒቨርስቲውን ሴኔት ያሳመኑትን የቀድሞው የዩኒቨርስቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕረዚዳንት ዶ/ር አሻሞ ኤራንቆን አመስግነዋል። የወላይታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ እንደተናገሩት ትምህርት ስብዕናው የተገነባ ስራ ፈጣሪ ዜጋ በመቅረፅ ረገድ የሚጫወተው ሚና ጉልህ ስፍራ ይሰጠዋል። መንግሥት ለፍትሃዊ የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት መጎልበት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ዩኒቨርስቲዎች በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ የበኩላቸውን እየወተጡ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶክመንቴሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው ተቋሙ በሰው ኃይል ግንባታ እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት ላይ መሆኑን የዛሬ ተመራቂዎች ማሳያ ናቸው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትምህርትና ሥልጠና፣ በምርምር ዘርፍ እንዲሁም በአካባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረታቸውን ባደረጉ መስኮች ላይ በጋራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ለዓመታት የጊቤ-1፣ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞችን በፖወር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ እያስተማረ በማስመረቅ ላይ በመሆኑ በተቋሙ ስም ምስጋና እንደሚገባው ተናግረዋል። ከትምህርት ክፍሉና ከዩኒቨርሲቲው 3 ነጥብ 98 በማምጣት የላቀ ውጤት ያስመዘገበው የተቋሙ ሠራተኛ ታሪኩ ጠንክር የወርቅ ሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ ተሸልሟል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጊቤ-3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሃብታሙ ሰሙን ጨምሮ የጣቢያው ሠራተኞች፣ የዋቻሞ ዩኒቨርስቲ የሴኔት አባላትና የትምህርት ዘርፉ መምህራን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 06 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+9

ከተቋሙ ዕሴቶች ጋር የተስማማ የስራ ዘዬ መከተል ይገባል ተባለ .......///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ራሳቸውንና ተቋሙን ስኬታማ ለማድረግ  ከተቋም ዕሴቶች ጋር የተስማማ የስራ ዘዬ እንዲከተሉ የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ አሳሰበ። ቢሮው ለተቋሙ መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር የምክር ቤት አባላት በተቋም እና ሠራተኛ ግንኙነት ላይ ያተኮረ ስልጠና በአዳማ ከተማ ሲሰጥ ሥራ አስኪያጁ አቶ አንዷለም ኪዳኔ እንደተናገሩት የአገልጋይነት ስሜት የተላበሰ የስራ ባህል በመፍጠር የተቋሙን ራዕይ እና ተልዕኮ ማሳካት ይገባል። በየትኛውም የሥራ መስክ ስኬታማ ለመሆን የሙያ ክህሎትን እና ዕውቀትን ማበልፀግ፣ ፕሮፌሽናል አስተሳሰብ መገንባት እና የሥራ ፍቅርን ማጎልበት ይገባል ብለዋል። ለደመወዝ እና ኃላፊ ለመሆን ሳይሆን ለተቋሙ ሁለንተናዊ ዕድገት እና ለህሊና መስራት እንደሚገባም ነው አቶ አንዷለም ያነሱት። የተቋሙ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው የምክር ቤቱ አባላት የሠራተኛውን ጥቅም ከማስጠበቅ ባሻገር ዘመኑን የዋጀ ዕውቀት፣ ክህሎትና አስተሳሰብ በማዳበር ለኃይል ልማት ዘርፉ እመርታ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። ስኬታማ የቡድን ሥራ እውን ለማድረግም በዕውቀት የሚመራ ምክንያታዊ አሰራር  ማጎልበት እና መልካም የእርስ በእርስ ግንኙነት መፍጠር እንደሚገባ በስልጠናው ወቅት ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 05 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+5

photo content
+3

ክልሉ ከ17 ቀናት በኃላ ኤሌክትሪክ አግኝቷል ...///... ላለፉት 17 ቀናት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳግም መገናኘቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት በክልሎቹ ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲመለስ ለማድረግ እልህ አስጨራሽ ጥረቶች ሲደረጉ ቆይተዋል። ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚገቡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ተደጋጋሚ ስርቆት ስለሚፈፀም የተቋረጠውን ኃይል መልሶ የማገናኘት ሥራውን ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል ብለዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ለቀናት መስመሩን ለማገናኘት የተደረገው ጥረት ተሳክቶ ዛሬ ከቀኑ 9:05 ሰዓት ጀምሮ አካባቢዎቹ ኤሌክትሪክ አግኝተዋል። በጥገና ሥራው ላይ ድጋፍ ላደረጉት የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ለሁለቱ ክልሎች መስተዳድሮች እና ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኤሌክትሪክ አገልግሎት ምስጋና አቅርበዋል። በአንድ አካባቢ የሚፈፀም የኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ተፅዕኖው ሰፊ እንደሆነ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኃይል መቋረጥ በግልፅ የታየ በመሆኑ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት ለመሰረተ ልማቱ ጥበቃ እንዲያደርጉ ሥራ አስፈፃሚው ጠይቀዋል።

የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንባታ 62 በመቶ ደርሷል ……//…… የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክት ግንባታን በሚቀጥለው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን እና አቅም ማሻሻል ፕሮጀክት አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ወ/ጊዮርጊስ እንደገለጹት የመቆጣጠሪያ ማዕከሉ ህንጻ ግንባታ የስትራክቸር ስራ 98 በመቶ፣ የብሎኬት ሥራው 75 በመቶ እንዲሁም የልስን ስራው 47 በመቶ ደርሷል። በማዕክሉ ውስጥ የሚተከሉት የግሪድ መቆጣጠሪያ ሲስተሞች ፍተሻ በኮንትራክተሩ ፋብሪካ ውስጥ መከናወን መጀመሩን አቶ በኃይሉ ተናግረዋል። በማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚተከሉ የመረጃ ማሰባሰቢያ መሳሪያዎች፣ የኮሙዩኒኬሽን ዕቃዎቸ እንዲሁም ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል የሚያገለግሉ ፋየርዎሎች የፍብሪካ ፍተሻ መከናወኑንም ገልጸዋል፡፡ ቀይ ባህር ላይ ባጋጠመ የባህር ትራንስፖርት ስጋት ምክንያት የግንባታው አንዳንድ ሥራዎች የመዘግየት ችግር እንደገጠማቸው ኃላፊው ተናግረዋል። እንደ አቶ በኃይሉ ገለጻ የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ፕሮጀክቱን ግንባታ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ከኮንትራክተሩና አማካሪ መሀንዲሱ ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በዚህም አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 62 በመቶ መድረሱንና አጠቃላይ የግንባታ ሥራውን እስከ ሐምሌ 2017 ዓ.ም ድረስ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አቶ በኃይሉ ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በዋነኛነት ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ የSCADA/EMS ሶፍትዌሮችን መጠቀም ከማከፋፈያ እና ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር ወቅታዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ የኦፕሬሽን ሥራዎችን አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለማከናወን የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉ ከሳይበር ጥቃት ሊከላከል የሚያስችል የሴኩሪቲ ሲስተም እንደሚኖረው የጠቆሙት ኃላፊው ለኦፕሬተሮች የሚሆን የመኖሪያ ቤት ግንባታም በመከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ፕሮጀክቱ በሥራ ላይ ካሉት የኃይል ማመንጫዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተጨማሪ ወደፊት የሚገነቡትን የኃይል መሰረተልማቶች ታሳቢ በማድረግ እየተገነባ ይገኛል። የማዕከሉ መገንባት የሲስተም መዋዠቅን በመቀነስ የኃይል አቅርቦት ጥራትን ለማሻሻል ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል፡፡  የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክት ከፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ (AFD) በተገኘ ብድር እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተመደበ 197 ሚሊየን ብር እና 62 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ በጀት በመገንባት ላይ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 05 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+3

ማህበሩ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ ...........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአዳማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የተጠናቀቀውን የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባኤው ያቀረቡት የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበጀት ዓመቱ በጡረታ እና በሞት ለተለዩ የማህበሩ አባላት ከ3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈፀሙን ተናግረዋል። ዲፕሎማ የትምህርት ደረጃ ያላቸው የተቋሙ ሠራተኞች የሥራ ልምዳቸውን ታሳቢ በማድረግ የዲግሪ ትምህርት ዝግጅት በሚጠይቁ የሥራ መደቦች ላይ እንዲመደቡ መደረጉን ተናግረዋል። የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማሳደግም በቅጥር ወቅት 30 በመቶ ዕድል ለሴቶች መሰጠቱን ገልፀዋል። እንደ አቶ መኮንን ገለፃ በህብረት ስምምነቱ መሠረት በደረጃ ዕድገት እና በትምህርት ዕድል ሴቶችን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው። የማህበሩን የገቢ አቅም ከማሳደግ አንፃር የተለያዩ ስልቶችን ተግባራዊ በማድረግ በ2012 በጀት ዓመት አራት ሚሊዮን ብር የነበረውን የማህበሩ ሀብት በ2016 በጀት ዓመት መገባደጃ ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ ማድረስ ተችሏል። የማህበሩ ዋና ፀሐፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በበኩላቸው በተለያዩ  ምክንያቶች በተጓደሉ የምክር ቤት አባላት የተተኩ  አዲስ አባላትን ለምክር ቤቱ ይፍ አድርገዋል። ማህበሩ ዛሬ እና ነገ በሚያከናውነው መርሐ ግብር የ2016 በጀት ዓመት የፊስካል እና የበጀት አፈፃፀም እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ገምግሞ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 04 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+7

የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ………///……… በአዲሱ በጀት ዓመት የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ምጣኔ ለማሳደግ በሚያስችሉ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት እንደሚደርጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቁ፡፡ የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በህዝብ ውክልና ሥራ ለተሰበሰቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 15 የሚሆኑ አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ይጀመራል፡፡ የሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደ ህዳሴና ኮይሻ ያሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ የውጪ ምንዛሬ ዕጥረት፣ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ከወሰንና ካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ችግሮች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ዝርፊያ የኃይል ተደራሽነትን ከመጉዳቱ በላይ ዘርፉን ወደ ኋላ እየጎተተ ይገኛል። በመሆኑም ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መሠረት ልማቶችን በመጠበቅ የሀገርን ሀብት ከብክነት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ በበኩላቸው ተቋማቸው ከኃይል ፍላጎትና ጥራት እንዲሁም አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል። በበጀት ዓመቱ ከ 100 በላይ ከተሞችን የኃይል ተጠቃሚ የሚያደርጉና የኃይል መቆራረጥን የሚቀርፉ የማሻሻያ ፕሮጀክቶች ይተገበራሉ ብሏል። በገጠራማ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 17 የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች በያዘነው በጀት ዓመት ግንባታቸው እንደሚጠናቀቅ ተመልክቷል። ከክፍያ ጋር የተያያዙ እንግልቶችን ለማስቀረት የዲጂታል የክፍያ ዘዴ መመቻቸቱና ዲጂታል ቆጣሪዎችን በመጠቀም የቅድመ ክፍያ አገልግሎት በመሰጠት ላይ እንደሚገኝ ተቋሙ ገልጿል። ከኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎትና የኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ ህብረሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት እንደሚሰሩ ሁለቱ ተቋማት አረጋግጠዋል። በቀጣይ ሶስት አመታት የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ የአዳዲስ የኃይል ምንጮችና ማሰራጫዎች ግንባታ እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል። የመረጃ ምንጫችን የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content

የኃይል ዘርፍ ሪፎርም፣ኢንቨስትመንት እና ሞደርናይዜሽን ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሄደ .........///......... በዓለም ባንክ ብድር የሚተገበረው የኃይል ዘርፍ ሪፎርም፣ ኢንቨንስትመንት እና ሞደርናይዜሽን ፕሮግራም በእንግሊዝኛ ምዕፃሩ (PRIME ) የተሰኘው ፕሮግራም ይፋ ተደረገ። ፕረግራሙ ዘርፈ ብዙ የኢነርጂ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ያለመ ነው። በፕሮግራሙ ማስጀመሪያ ላይ የፋይናንስ ሚኒስትር ዲኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው እንደገለፁት ለኢነርጂ ዘርፍ የሪፎርም ትግበራ በዓለም ባንክ በኩል 1.5 ቢሊዮን ዶላር ተመድቧል። የኢነርጂ ዘርፍ ልማት በመንግሥት ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ የተመደበውን መዋዕለ ንዋይ ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኤታዋ አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ አበበ ዘሪሁን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በኢነርጂ ዘርፍ ወሳኝ መሠረተ ልማቶችን እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። አቶ አበበ እንደገለፁት በባንኩ ብድር የሚተገበረው የኃይል ዘርፍ ሪፎርም፣ ኢንቨንስትመንት እና ሞደርናይዜሽን ፕሮግራም በእንግሊዝኛ ምዕፃሩ (PRIME )ዘርፈ ብዙ የኢነርጂ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ያለመ ነው። የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር አማካሪ አቶ ጎሳዬ አለማየሁ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን አቅምን እና የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማሳደግ ያግዛል። የሀገሪቱ ግማሽ ያህል ዜጎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንደማያገኙ የገለፁት አቶ ጎሳዬ ፕሮጀክቱ ዜጎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል። የኢነርጂ እና ነዳጅ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክትር ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ  በበኩላቸው እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ  ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አቅርቦት እውን ለማድረግ ይረዳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተጀመረው የፕራይም (PRIME) ፕሮጀክት የኢነርጂ ዘርፉን ለማሳደግ የሚያግዝ በመሆኑ የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ሥራ በተቀናጀ መልኩ እንደሚመሩ አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ የኢነርጂ ስፔሻሊስት አቶ አብዱልሃኪም ሙሐመድ በበኩላቸው በዓለም ባንክ ፋይናንስ የሚደረገው የኢነርጂ ሪፎርም በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ለማከናወን የታቀደ ነው። በስካይ ላይት ሆቴል በተከናወነው የማስጀመሪያ መርሃግብር የፋይናንስ ሚኒስቴር፣የኢነርጂ እና ነዳጅ ባለስልጣን፣ የዓለም ባንክ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፋተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ታድመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+2

photo content
+9

ከሁለት ሳምንታት በላይ ተቋርጦ የቆየው ኃይል መልሶ ተገናኝቷል .........///......... ላለፉት 18 ቀናት በሁመራ እና አካባቢው ተቋርጦ የቆየውን ኃይል መልሶ የማገናኘት ሥራ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንዳስታወቁት በአካባቢው ኃይል ተቋርጦ የቆየው ከሽሬ- ሁመራ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በመውደቁ ነው። ከሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል የተቋረጠባቸው ሁመራ ከተማን ጨምሮ ዳንሻ፣ ባዕከር፣ አዲረመጥ፣ ሶረቃ፣ ማይካድራ፣ አብደራፊ፣ አብርሃጅራ፣ አዲጎሹ እና አደባይ የኤሌክትሪክ ኃይል ዳግም አግኝተዋል። ህብረተሰቡ የደረሰው ጉዳት እስኪጠገን ድረስ በትዕግስት በመቆየቱ እና በጥገና ሥራው ላይ ድጋፍ በማድረጉ አቶ ውበት አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ አካውንት | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content