en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 553 subscribers, ranking 8 395 in the Technologies & Applications category and 2 164 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 553 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 5 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.99%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 043 views. Within the first day, a publication typically gains 2 393 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 553
Subscribers
+124 hours
+47 days
+530 days
Posts Archive
photo content
+2

የተቋሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ አመራሩ ሚናውን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል .........///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠውን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ ሚናውን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በየደረጃው ለሚገኙ የተቋሙ የሥራ መሪዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ የተሳትፎ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስልጠናውን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለፁት መንግስትና ህዝብ ከተቋሙ  የሚጠብቀውን ነገር በአግባቡ ለመፈፀም ብቃት ያለው አመራር  ያስፈልጋል። በዚህም የአመራሩን አቅም ማሳደግ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እየተካሄዱ ይገኛሉ ብለዋል። የተቋሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኘው አመራር ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር  አመራሩ የተቋሙን ግብ፣ ርዕይ፣ ተልዕኮና እሴቶች  ተገንዝቦ ወደ ውጤት መቀየር እንደሚጠበቅበትም ተናግረዋል። አመራሩ ከስልጠናው የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ሠራተኛው በማውረድ  በተቋሙ ስትራቴጅና የለውጥ ሥራዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር እንደሚኖርበት ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስገንዝበዋል። የተቋሙን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ተተኪ አመራርና ሠራተኛ ማፍራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት መሠራት ይኖርበታል ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው። የተቋሙን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም በየደረጃው የሚገኝ አመራር በትብብር መስራት  እንደሚጠበቅበትም አሳሰበዋል። የአመራሩን አቅም ለማሳደግ በቀጣይ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኢንጂነር አሸብር አረጋግጠዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ የያዘውን ዕቅድ በአግባቡ ለማሳካት የአመራሩን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ስልጠናው የአመራሩን ተሳትፎ በማጎልበት የተቋሙን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ብቃት ያለው፣ ሥነ ምግባር  የተላበሰ  እንዲሁም ለለውጥ አርአያ  የሆነና ግንባር ቀደም አመራር ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ አስረድተዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ በተቋሙ ስትራቴጅክ ዕቅድ፣ በሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ፣ በሰው ሀብት አስተዳደርና ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲሁም በለውጥ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል። ለቀሪ የሥራ መሪዎች መሰል ስልጠና በቀጣይ ሳምንት እንደሚሰጥም አቶ  ሙላት ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ ……//…..… ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ሲገነባ የቆየው የ2 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተለለፊያ መስመር ዝርጋታ የፍተሻና ሙከራ ሥራ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለፁት 8 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ያሉት የማስተላለፊያ መስመሩ ከቆቃ-ገላን ከተዘረጋው ጥምር መስመር ጋር በማገናኘት ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል፡፡ በተያያዘ ዜና የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሚኖሩት አራት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች መካከል 50 ሜጋ ዋት ኃይል የማቅረብ አቅም ያለው አንዱ ትራንስፎርመር የፍተሻ እና ሙከራ ሥራውን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ እንደ ሳይት ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የፍተሻና ሙከራ ሥራው የተጠናቀቀውን ትራንስፎርመር አገልግሎት እንዲጀምር ለማድረግ የኢንጂነሪንግ ዘርፍን ማረጋገጫ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ለአፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያነት እየተገነቡ ያሉ አምስት ቤቶች ላይ የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል፡፡ የስዊችያርድ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታ እና ቀሪ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ገጠማ ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑን ጨምረው አብራርተዋል፡፡ የኃይል ማከፋፈያው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ባለስልጣን ለሚፈልገው አገልግሎት ኃይል የሚያቀርቡ 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ እየተገነባ የሚገኝ ጣቢያ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ እና የማማከር ሥራ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን ለግንባታ ሥራው የሚያስፈልገው ወጪም በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን እየተሸፈነ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቼንጅ ማኔጅመንት ኦፊሰር 3ኛ (ዲ-4) የስራ መደብ ለመቅጠር ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም የቃል ፈተና መስጠቱ ይታወቃል
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቼንጅ ማኔጅመንት ኦፊሰር 3ኛ (ዲ-4) የስራ መደብ ለመቅጠር ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም የቃል ፈተና መስጠቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም በቼንጅ ማኔጅመንት ኦፊሰር 3ኛ (ዲ-4) የስራ መደብ የቃለ መጠይቅ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተራ ቁጥር 1 እና 2 ላይ  ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ከነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡   በቼንጅ ማኔጅመንት ኦፊሰር 2ኛ (ዲ-3) የስራ መደብ የወጣው ማስታወቂያ የተሰረዘ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

‎የህዳሴ ግድብ የብሔራዊ ጥቅሞች ንጉስ ነው ‎ዛዲግ አብርሃ ‎.....///...... ‎የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ብሔራዊ ጥቅማችንን በማስጠበቅ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የመልማት ሀገራዊ ፍላጎታችን ዐቢይ ማሳያ መሆኑ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። ‎ ‎ሀገራት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዎቻቸው የሚቀዱት ከብሔራዊ ጥቅማቸው በመሆኑ ለዚህ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ‎ ‎ለታዳጊ ሀገራት የኃይል አቅርቦት የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ኢትዮጵያ በአባይ ውሃ ላይ ፍትሐዊ አጠቃቀምን ማረጋገጥ እና ወደብ ማግኘት ቀዳሚ ብሔራዊ ጥቅሟቿ መካከል ዋነኞቹ ናቸው ብለዋል። ‎ ‎የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ ቅቡልነት ያገኘ ፕሮጀክት በመሆኑ ለስኬት መብቃቱን ተናግረዋል። ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ግድቡ ተገንብቶ መጠናቀቅ የተፈጥሮ ሀብታችንን እንዳንጠቀም ተደቅኖ የቆየውን ፈተና በማስወገድ ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ስትራቴጅካዊ ድል የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ ሌሎች ፍላጎቶቻችንን ለማሳካት የሚያስችል የብሔራዊ ጥቅሞች ንጉስ መሆኑን በመረዳት ወደ ኦፕሬሽን ከገባ በኋላም ተንከባክቦ መጠቀምና ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ብለዋል። ‎ ‎ተቋሙ የሀገርን የኢነርጂ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እየሰራቸው ያሉ የኃይል መሠረተ ልማቶችን ከብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመቃኘት ብዙ ህዳሴዎችን አቅዶ መተግበር እንዳለበት አብራርተዋል። ‎ ‎ብሔራዊ ጥቅም ላይ ተመስርቶ ሥራዎችን የማያከናውኑ ተቋማዊ መጨረሻቸው ውድቀት ነው ያሉት አቶ ዛዲግ ተቋሙ በዚህ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት እና የመፈጸም አቅሙን በማሳደግ በኃይል ልማት ዘርፉ ለሀገር ማንሰራራት መሰረት የሆኑ ሥራዎችን እንደሚገባው ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

‎በተቋሙ የሚከናወኑ ሥራዎች አርበኝነትን የሚጠይቁ ናቸው ‎.....///..... ‎በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ መሠረታዊ ለውጥ በማምጣት ሁሉን አቀፍ ዕድገት ለማረጋገጥ በአርበኝነት ስሜት መስራት እንደሚገባ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። ‎ ‎ሦስተኛ ቀኑን በያዘው ሥልጠና ላይ ፕሬዚዳንቱ በአርበኝነት ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች ገለፃ አድርገዋል። ‎ ‎አርበኝነት በሀገር ፍቅር ስሜትና በአሻጋሪ ሀሳቦች ዙሪያ በመሰለፍ ዜጎች ችግርና መከራን ተጋፍጠው ለሀገር ልማት እና ዕድገት እንዲሁም ነጻነት የሚከፍሉት መስዋዕተነት ነው ብለዋል። ‎ ‎እንደ ሀገር በፍጥነት ለማደግና ሁለንተናዊ ለውጥ ለማምጣት የኃይል ልማት ዘርፉ ማደግ ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ለዚህም በዘርፉ መስዋዕትነት ለመክፈልና ሀገርን ለማገልገል ቁርጠኛ የሆኑ አርበኛ ሠራተኞችን ማፍራት እንደሚገባ አብራርተዋል። ‎ ‎ተቋሙ ህዳሴ እና ኮይሻን ጨምሮ የሚያከናውናቸው ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በአርበኝነት ስሜት የተቃኙ ዓላማዎች እንዲኖሩት አመራሩ ሚናውን መወጣት እንዳለበት ገልፀዋል። ‎ ‎አርበኝነት ተስፋንና ታሪክን የሚያገናኝ ዘርፈ ብዙ መልክ ያለው መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ በባህሪው ገንቢም አጥፊም ሊሆን እንደሚችል አብራርተዋል። ‎ ‎አርበኝነት አጥፊ ሲሆን ሙስና በማስፋፋት፣ የጋራ ርዕይን በማጥፋት፣ ትብብርና አንድነትን በመሸርሸር ዕድገትና ተስፋ እንዳይኖር እንደሚያደርግ አብራርተዋል። ‎ ‎የተቋሙ አመራር የአርበኝነትን መልካም ጎን ለይቶ ተቋማዊ ባህል በማድረግ በኃይል ልማት ዘርፉ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣትና መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆን እንደሰለበት አሳስበዋል። ‎ ‎አመራሩ ሠራተኛውን በማስተባበር ማህበረሰብንና ሀገርን በመሠረታዊነት ለመለወጥ መትጋት፣ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ተግባራትን አቅዶ መስራት፣ ችግሮችን ከመገፋፋት ወጥቶ በትብብርና በጊዜ የለኝም ስሜት ማከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

‎የተቋሙ አመራር ዘመን ተሻጋሪና ለቀጣዩ ትውልድ አሻራ የሚሆኑ ሥራዎችን ማከናወን አለበት ‎.....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች በዓላማ ጥራት ዘመን ተሻጋሪና ለቀጣዩ ትውልድ አሻራ የሚሆኑ ሥራዎችን መስራት እንዳለባቸው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ተናገሩ። ‎ ‎ፕሬዝዳንቱ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደተናገሩት አመራሮቹ ለጊዜያዊ ስኬት ሳይሆን መሠረታዊ የተቋሙን እሴቶች ጠብቀው ለትውልድ የሚሻገሩና ዘመኑን የሚዋጁ ሥራዎችን ትኩረት ሰጥተው ማከናወን አለባቸው። ‎ ‎ደካማ የሥራ አፈጻጸም ባህልን በማስወገድ በዘርፉ የመጪውን ዘመን ስጋቶች በመቀነስ እና መልካም ዕድሎችን በመጠቀም ለሀገር የሚጠቅም አሻራ ለማኖር የአመራሩ ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። ‎ ‎ከዓላማና ከአሻራ የተፋታ የሥራ አፈጻጸምን ብቻ መሰረት ያደረገ የሥራ ባህል መሰላቸትን፣ የሥነ ምግባርና የተቋማዊ እሴት መሸርሸር እንዲሁም የፈጠራ ችግርን እንዲኖር ያደርጋል ያሉት አቶ ዛዲግ ይህም በሥራ አመራሩ መካከል ፉክክርን በማስፈን ትብብርን እንደሚያጠፋ ገልጸዋል። ‎ ‎እንደኤንሮንና ቮልስ ዋገን ያሉ ኩባንያዎች እንዲሁም ሌማን ብራዘር የተሰኘ አሜሪካዊ ባንክ ጊዜያዊ ስኬት ላይ በማተኮር እና አፈጻጸማቸው ከዓላማ እና ከአሻራ የተፋታ በመሆኑ ለውድቀት መዳረጋቸውን ለአብነት አንስተዋል። ‎ ‎እንደአመራር ዘላቂ ስኬትና መሠረታዊ ለውጥ ለማስመዝገብ በተቋሙ ያለውን የማትጊያ ሥርዓት፣ የሠው ኃይል ምደባ፣ የሥራ ግምገማና በጀት ከዓላማ፣ ከተቋማዊ እሴትና ከርዕይ አንጻር መቃኘትና የመማማር ሥርዓትን ማጎልበት እንደሚገባ አብራርተዋል። ‎ ‎የተቋሙ መጠንከር የሀገር ብቻ ሳይሆን ለቀጣናው መነሳትና ማንሰራራት በመሆኑ አመራሮች ለጊዜያዊ ስኬት ሳይሆን ዘላቂ አሻራን ለማኖር ትልልቅ ሥራዎችን በተነሳሽነት ስሜት ማከናወን አለባቸው ብለዋል። ‎ ‎ተቋሙ አባይን በመሳሰሉ ወንዞቻችን ተጠቅመን የሕብረተሰባችንን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እንዳንችል አድርጎ የቆየውን የኢትዮጵያን የዘመናት ሰንኮፍና ፍርደ ገምድል ውሳኔ በማስወገድ የበራች ኢትዮጵያን የመፍጠር ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት የመወጣት ዓላማ ላይ አተኩሮ መስራት እንዳለበት ገልጸዋል።  ‎ ‎በኃይል ዘርፉ የሚመዘገበው ለውጥ የአጠቃላይ ብልጽግና መሠረት ነው ያሉት አቶ ዛዲግ ለትውልድ በረጅም ጊዜ በዓላማ አቅዶ በመስራት ውጤት የማምጣት ተምሳሌት በሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የተገኘውን ውጤት በማባዛት የበራች ኢትዮጵያን መፍጠር እንደሚገባ አብራርተዋል። ‎ ‎አመራሩ የአሻራ ግምገማ በማድረግ፣ መጭውን ጊዜ አልሞ በትብብር ለተቋማዊ እሴት እና ለረጅም ጊዜ ውጤት ያለመታከት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

በሀገሪቱ የአረንጓዴ ኢነርጂ ፖሊሲን ለመተግበር የተቋሙ አመራር ቁርጠኛ መሆን አለበት .....///….. በኢትዮጵያ  የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በማስፋት የአረንጓዴ ኢነርጂ ፖሊሲ የበላይነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ የተቋሙ አመራር ቁርጠኛ መሆን እንደሚኖርበት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት ገለጹ፡፡ ፕሬዚደንቱ አቶ ዛዲግ አብርሃ የኃይል ማመንጨት ዕድገት ትናንት፣ ዛሬ እና የወደ ፊት መጻኢ ተስፋን አስመልክተው ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ሰፊ ገለጻ አድርገዋል፡፡ በገለጻቸውም ዓለም ከቅድመ ኢንዱስትሪ ማህበረሰብ ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ የተመዘገቡ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ጂኦ ፖለቲካዊ ዕድገቶች በኢነርጂ ሽግግር ላይ የተመሰረቱ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ እንደ ቻይና፣ ጀርመንና አሜሪካ ያሉ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ሀገራት የነበራቸውን የነዳጅ፣ የኒውክለርና ሌሎች የኃይል ምንጮችን  ወደ ታዳሽ የኃይል ምንጮች በማሸጋገር   ከካርቦን ልቀት የጸዳ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የፓሊሲ ለውጥ እያደረጉ መሆኑን አስታውሰዋል። ጀርመን በ2050 ስልሳ በመቶ የኃይል ምንጯን ከታዳሽ ኃይል ለማግኘት የፖሊሲ ለውጥ ማድረጓን ለአብነት የጠቀሱት አቶ ዛዲግ  ኢትዮጵያም የኢነርጂ ፖሊሲዋን በመፈተሽ ታዳሽ ኃይል ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባት ገልጸዋል። እንደ አቶ ዛዲግ ገለጻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢነርጂ ሴክተሩን በበላይነት የሚመራ ተቋም በመሆኑ በግሎባል ኢነርጂ ሽግግር ላይ አመራሩ ግንባር ቀደም ሚና መጫወት ይኖርበታል። ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አማራጯን በማስፋት በቀጠናው ብሎም በዓለም የአረንጓዴ ኢንቨስትመንት ፉክክር ላይ ተወዳዳሪ ሆና እንድትቀጥል በዕውቀት ላይ የተመሠረተ አመራር እንደሚያስፈልግ ነው  የተናገሩት። በተቋሙ ጠንካራ የኢነርጂ ፖሊሲን በመቅረጽ ፍትሐዊ የኢነርጂ ክፍፍልን ማስፈን፣ የኃይል ብክነትን መቀነስ እና የማጠራቀም አቅምን ማሳደግ እንዲሁም ወጪ ቆጣቢ የኃይል አጠቃቀም ሥርዓትን ማሻሻል የአመራሩ ቁልፍ ተግባር መሆን አለበት ብለዋል። ስለሆነም በተቋሙ የኢነርጂ ፖሊሲ ውስጥ ብሔራዊ የተቀናጀ የኃይል ዕቅድን እና የኃይል ሽግግር ምክር ቤትን  እንዲሁም  የታሪፍ እና የድጎማ ሪፎርሞችን  በማካተት ዘላቂና የማይበገር የአረንጓዴ ኢነርጂ የበላይነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች የአመራርነት ሥልጠና ሲሰጡ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦ 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለዘመናዊነት ቆርጠን መነሳታችን ማሳያ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምሰሶና የብሔራዊ አንድነት መገለጫ ነው። 💡 ግድቡ ኢትዮጵያውያን ማህበራዊ ስብራቶቻችንን በመጠገን በትናንት ብቻ የምንኮራና በዛሬ የምናፍር እንዳንሆን የሚያደርግ ታሪካዊ ድል ነው። 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአንድ ወገን የበላይነትን እና ለብቻ ተቆጣጥሮ የመጠቀም ፍላጎት እንዲያከትም በማድረግ በቀጠናው ፍትሐዊ የውሃ አጠቃቀም ሥርዓት እንዲዘረጋ ፈር የቀደደ ነው።                                                           💡ግድቡ ኢንዱስትሪንና እና ዘመናዊ ግብርናን በማስፋፋት  የማህበረ ኢኮኖሚ ዕድገት እንዲኖር ወሳኝ ሚና ይጫወታል። 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሀገራዊ ውክልና/ National symbol/ እንዲሁም በማመንጨት አቅሙ የሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የማዕዘን ድንጋይ ነው። 💡ግድቡ የሚያመነጨውን ያህል ኢነርጂ ለማመንጨት ይወጣ የነበረን ወደ 2 ሚሊዮን ቶን ካርቦንዳይኦክሳይድ በማስቀረት ለዓለም ከባቢ አየር አወንታዊ አስዋጽኦ ያበረክታል። 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በዘመናት መካከል ግጥም እየገጠሙ ዘፈን እየዘፈኑ ቁጭታቸውንና አለመቻላቸውን በሚገልጹበት አባይ ላይ መገንባቱ የተለየ ትርጉም አለው። 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የማንሰራራት ትርክት፣የአንድነት፣የዘመናዊነት እና የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ኩራት መገለጫ ነው። ግድቡ ኢትዮጵያውያን የኢነርጂ ሉዓላዊነታቸውን ለማረጋገጥ ቁርጠኛ መሆናቸውን ማሳያ ጭምር ነው። 💡ኢትዮጵያ አፈሯን እየወሰደ እያየችው ምንም ማድረግ ላልቻለችውና ተቀምጣበት የእሷ መሆን ባልቻለው ሽፍታው አባይ ላይ ግድብ መገንባቷ፤ ኢትዮጵያውያን ተፈጥሮን በተለይም ውሃን መቆጣጠር አይችሉም፣ውሃ እያላቸው ውሃ የሚጠሙና የሚራቡ ህዝቦች ናቸው የሚለውን የጸና ትርክት አሽቀንጥሮ በመጣል የትውልድ የመቻል ማሳያ ነው። 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በላይኛውና በታችኛው ተፋሰስ ጸንቶ የቆየውን ታችኞቹ ይጠቀማሉ ላይኞቹ ውሃውን ይልካሉ የሚለውን ትርክት የበጣጠሰ ነው። በተለይም ውሃ እያላቸው መጠቀም ላልቻሉ የዓለም ህዝቦች የማንቂያ ደወል ነው። 💡የግድቡ መገንባት የናይል ተፋሰስ ሀገራት ጩኸት የቁራ ጩኸት ሆኖ ሰሚ እንዳያገኝ ሲደደረግ የነበረውን የዘመናት ሴራ በአፍ ጢሙ የደፋ ነው። 💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንጂነሪንግ አቅም እንዲሁም የሀገሪቱ የፖሊሲ፣የኮሙዩኒኬሽን እና የዲፕሎማሲ ጥረት ትልቅ ማሳያ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+5

የኢነርጂ ተደራሽነት ከሀገራዊ ብልጽግና ጋር ይያያዛል .......///...... የኢነርጂ ተደራሽነት ከሀገራዊ ብልጽግና እና ተሰሚነት ጋር እንደሚያያዝ የአፍሪካ የአመራር ልቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ተናገሩ። ፕሬዝዳንቱ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ እንደተናገሩት በኢነርጂ ዘርፍ የሚደረገው ሽግግር ወደ ሥልጣኔ የሚደረግ ሽግግር ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ወሳኝ ለውጦች በኢነርጂ ታግዘው የመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። የኃይል ቀውስ መከሰት የፖለቲካ አለመረጋጋት እንዲፈጠር እና መንግስታት እንዳይፀኑ ስለሚያደርግ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። እንደ አቶ ዛዲግ ገለፃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግር የተቋሙ ችግር ብቻ ተደርጎ የሚወሰድ ባለመሆኑ ለውጥ በሚያመጣ መልኩ መስራት ያስፈልጋል። የቀጣዩ ዘመን የኃይል ምንጭ ውሃ፣ ንፋስ፣ ነዳጅ ወይም ኢነርጂ ሳይሆን ርዕይ ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

“የህዳሴው ግድብ ከአንገት መድፋት ወደ ደረት መንፋት አሸጋግሮናል” ዛዲግ አብርሃ .......///...... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከአንገት መድፋት ወደ ደረት መንፋት አሸጋግሮናል ሲሉ የአፍሪካ አመራት ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። ፕሬዝደንቱ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች በተቋሙ ዋና መ/ቤት የአመራርን ስልጠና ሲሰጡ እንደተናገሩት የህዳሴ ግድብ ከኃይል ማመንጫነት ባሻገር ለኢትዮጵያውያን ያለው ትርጉም የላቀ ነው። “የህዳሴ ግድብ የሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የማዕዘን ድንጋይ ነው።” ያሉት አቶ ዛዲግ ግድቡ ለሀገር ከሚያስገኘው የኢኮኖሚ ጥቅም በላይ ለዓለም የከባቢ አየር ጥበቃ ድርሻው ጉልህ መሆኑን ተናግረዋል። የውሃ ኃይል ግድቦች በሩቅ ምስራቋ ቻይና በዓለም የመጀመሪያው ሀገረ መንግስት ግንባታ እንዲጀመር መሰረት መሆናቸውን ጠቅሰው የሚመነጨው ኃይል ከኢኮኖሚ ጥቅም በላይ መሆኑን አሳይቷል ብለዋል። አቶ ዛዲግ እንዳሉት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የብሄራዊ ኩራት ምንጭ በመሆኑ ግድቡ ከታሪካዊ ማንነታችን ጋር በጥብቅ በተሳሰረው የአባይ ወንዝ ላይ መገንባታችን ኩራቱን ከፍ እንደሚያደርገው ገልፀዋል። ግድቡ በሚያመነጨው ኃይል፣ በሚያስገኘው የውጭ ምንዛሪ እና በሚፈጥረው ትስስር ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት የወሳኝነት ሚና እንዲጎለብት የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል። የአባይን ውሃ እንዳንጠቀም ብዙ ሴራ ቢሸረብብንም ያንን ሁሉ አልፈን የወሰንነው ውሳኔ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እርምጃ ነው ሲሉ የግድቡን የሉዐላዊነት መገለጫነት አስረድተዋል። ግድቡ ኢትዮጵያ ልማቷን ለማረጋገጥ የምትሄደውን ረዥም ርቀት ያሳየም ነው ብለዋል። ስለትውልዳዊ ቅብብሎሽ ሲያነሱም “ጀምሮ ያለመጨረስ ታሪካችን የሁል ጊዜም አለመሆኑን በህዳሴው ግድብ አረጋግጠናል” ሲሉ ተደምጠዋል። ይህ ትውልድ ከአፄ ዳዊት ጀምሮ የነበረውን አባይን የመገደብ ህልም ከግብ ማድረስ የቻለ አኩሪ ትውልድ መሆኑን የተናገሩት አቶ ዛዲግ “የቀደመውን ትውልድ ህልም ተቀብሎ እውን የማድረግ ተግባር አስቀጥለን ለትውልድ ማስተላለፍ ከቻልን ኢትዮጵያን ለሁልጊዜም የታላላቅ ጅምሮች እና የታላላቅ ፍጻሜዎች ሀገር እናደርጋታለን” ሲሉ እምነታቸውን ገልጸዋል። በኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ አቅም አውጥቶ መጠቀም እንደሚገባ የገለጹት ፕሬዝደንቱ ይህንን ለማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትልቁን ኃላፊነት እንደሚወስድ አስረድተዋል። በመሆኑም የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ እያንዳንዱ ቤት የሚገባ በመሆኑ አፈጻጸሙ በሀገረ መንግስት ግንባታው ላይ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል። “የኤሌክትሪክ ኃይልን ተጠቃሚነት ማሳደግ ኢትዮጵያ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ለምታደርገው ሽግግር ወሳኝ በመሆኑ ለኢኮኖሚያችን መዋቅራዊ ሽግግር መክፈቻ ቁልፉ መብራት ኃይል ጋር ነው ያለው ማለት ይቻላል” ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም ተቋሙ ወደ ውጪ ሀገራት በሚልከው ኢነርጂ ምክንያት የዲፕሎማሲ ሥራ እየሰራ ነው ሊባል እንደሚችል ጠቅሰዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2