en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 537 subscribers, ranking 8 329 in the Technologies & Applications category and 2 179 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 537 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 31 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.36%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 097 views. Within the first day, a publication typically gains 2 520 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 537
Subscribers
-124 hours
-167 days
+3130 days
Posts Archive
ባለፉት 8 ወራት ከ8 መቶ በላይ ለሚሆኑ ተሸከርካሪዎች የጥገና አገልግሎት ተሰጥቷል ……..///………. ባለፉት 8 ወራት ለ8 መቶ 73 ተሸከርካሪዎች የተለያዩ የጥገና አገልግሎቶችን መስጠቱን የተቋሙ የተሸከርካሪዎች ጥገናና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የተሸከርካሪ ጥገና አስተዳደር ከፍተኛ ኦፊሰር አቶ ብሩክ እንዳለ እንዳስታወቁት ባለፉት 8 ወራት በተቋሙ ጋራዥ ለ696 ተሸከርካሪዎች ቀላል፣መካክለኛ፣ ከባድ እና የመስክ የጥገና አገልግሎቶችን ለመስጠት ታቅዶ 873 ጥገናዎችን ማከናወን ተችሏል፡፡ ከዚህ ውስጥ 537 ቀላል፣ 244 መካከለኛ፣ 12 ከባድ እንዲሁም 80 የመስክ የጥገና አገልግሎቶች መሰጠቱን ገልፀዋል፡፡ ይህም ከዕቅዱ ጋር ሲመነፃፀር በ177 እንዲሁም ከባለፈው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነፃጸር ደግሞ በ136 ተሽከርካሪዎች ብልጫ ማሳየቱን ነው የጠቆሙት፡፡ በዚህም የተቋሙ ጋራዥ ተሽከርካሪዎችን በራስ አቅም በመጠገኑ ተቋሙ ባለፉት 8 ወራት ከ12 ነጥብ 36 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ችሏል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ብሩክ ገለፃ ጋራዡ ከሚያከናውናቸው የጥገና ሥራዎች በተጨማሪ ከተቋሙ ውጪ በሆኑ ጋራዦች ጥገና ለተደረገላቸው የተቋሙ 50 ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች በአግባቡ መጠገናቸውን የክትትል እና ቁጥጥር ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ለ936 ተሸከርካሪዎች ቀላልና መካከለኛ ጥገና፣ ለ9 ከባድ፣ ለ100 መስክ ስራ ላይ ላሉ ተሸከርካሪዎች የጥገና ስራ ለማከናወን እንዲሁም በውጭ ድርጅቶች የጥገና ስራ ይከናወንላቸዋል ተብሎ ለታሰቡ 96 ተሸከርካሪዎች የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችን ለማከናወን በዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን አቶ ብሩክ ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ ጋራዥ በ2011 ዓ.ም የተቋቋመ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በ36 ሠራተኞች የተለያዩ ጥገናዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከተሸከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5

ተቋሙን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወናቸው ተገለፀ …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ውስጥ ተቋሙን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ለማዘመን
ተቋሙን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወናቸው ተገለፀ …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ውስጥ ተቋሙን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን ማከናወኑ አስታወቀ፡፡ የተቋሙ የአይሲቲ መሠረተ ልማት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደገለፁት በ6 ወራት ውስጥ ተቋሙ የሚጠቀምባቸውን የአይሲቲ አውታረ መረብ መሰረተ ልማትና የዳታ ማዕከል መቋረጥን በመቀነስ ተደራሽነቱን የማሻሻል ሥራ ተሰርቷል፡፡ የሥራ ክፍሉ ለብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የመስመር ላይ የኃይል መቋረጥ (online Power interruption) መከታተያ እና መጠየቂያ ሲስተም በኦንላይን ማስተናገድ የሚያስችሉ ሦስት ሶፍትዌሮችን እንዳበለፀገ ወ/ሮ ጽዮን ገልፀዋል፡፡ በተቋሙ ያሉ የሥራ ክፍሎችን እና የሪጅን ቢሮዎችን ከዳታ ማዕከል ጋር የማገናኘት፣ የአውታረ መረብና ዋይ ፋይ መሰረተ ልማት የመዘርጋት እና ለተቋሙ የIT ተጠቃሚ ደንበኞች ጥራት ያለው ድጋፍና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎት ለመስጠት የድጋድ ማዕከል (Help Desk) የማቋቋም ሥራ መከናወኑን አስታውቀዋል፡፡ በቀጣይም የኃይል ማመንጫዎችንና የሪጅን ቢሮዎችን ከዳታ ማዕከሉ ጋር የማገናኘት፣ ሁሉንም የድርጅቱ ቢሮዎች የአውታረ መረብ መሰረተ ልማት ተደራሽ የማድረግ እና የSAP ሲስተምን መጠቀም እንዲችሉ የማድረግ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ሥራ አስኪያጇ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 20 ቀን 2014 ዓ/ም

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ማደጉን አረጋገጠ .......////....... ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ጌዲዮ ዲላን በመርታታት ወደ ቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን አረጋገጠ። ወደ ፕሪ
ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ማደጉን አረጋገጠ .......////....... ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ጌዲዮ ዲላን በመርታታት ወደ ቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን አረጋገጠ። ወደ ፕሪሚየር ሊግ ለመግባት በሶስት ምድብ ተከፍሎ በከፍተኛ ሊግ ውድድር ሲካሄድ ነበር፡፡ ዛሬ ረፋድ ላይ ባህር ዳር ላይ በተደረገ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ጌዲዮ ዲላን 2-0 መርታቱን ተከትሎ አንድ ጨዋታ እየቀረው ወደ ፕሪምየር ሊጉ መመለሱን አረጋግጧል። ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ወደ ፕሪሚየር ሊግ የሚያድግ ከሆነ ለበቡድኑ 10 ሚሊየን ብር ለመሸለም ቃል መግባቱን መዘገባችን ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የአመራር ቡድን በተገኘው ድል የተሰማውን ደስታ እየገለፀ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2014 ዓ/ም

የወልዲያ ባለ 230/33/15 ኪ.ቮ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ ተጀመረ …….///…….. በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአሸባሪነት የተፈረጀው የህወኃት ቡድን ሙሉ በሙሉ ተነቅሎ የተወሰደውን የወልድያ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በአዲስ ማከፋፈያ ጣቢያ ለመተካት የሚያስችል ፕሮጀክት የግንባታ ስራ ተጀምሯል። የፕሮጀክቱ የሲቪል ስራዎች ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ከዚህ በፊት ከነበረው ተንቀሳቃሽ ጣቢያ በተለየ መልኩ በቋሚ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚከናወን ይሆናል። የወልድያ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ወልድያ ከተማና አካባቢውን ጨምሮ በአብዛኛው በሰሜን ወሎ ዞን ስር ለሚገኙ አስር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ይሰጥ ነበር። ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያው ከዚህ በፊት አገልግሎት ይሰጣቸው ለነበሩ አካባቢዎች በፍጥነት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንዲቻል በወልዲያ ከተማ እየተገነባ ከሚገኘው ባለ 400 ኪሎ ቮልት አዲስ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ላይ አንድ ቤይ በማንሳት በዚህ ፕሮጀክት ለመግጠም መታቀዱን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ የስቲል ስትራክቸር ዕቃዎች የሚቀመጡባቸውና የሚተከሉባቸው የመሰረት ስራዎች ተጠናቀዋል ብለዋል፡፡ ስቲል ስትራክቸር የመትከል ሥራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን በአሁን ሰዓት የፕሮጀክቱ የሲቪል ግንባታ አማካይ አፈፃፀም 35 በመቶ ደርሷል፡፡ እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለጻ በአሁኑ ሠዓት የመቆጣጠሪያ ቤቱ የዲዛይን ሥራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን ዲዛይኑ እንደተጠናቀቀ የመቆጣጠሪያ ቤቱን የመገጣጠም ሥራዎች በቀጣዮቹ ወራት ፕሮጀክቱን ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው፡፡ የአካባቢው ወጣቶች አሸባሪው የህወኃት ቡድን በአካባቢው ባደረሰው ጉዳት እልህና ቁጭት በፕሮጀክቱ ላይ መስራት ካለባቸው ሰዓት በላይ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ሳይጠይቁ እየሰሩ መሆናቸውንና ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሃ ግብር መሠረት እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ያላቸውን አቅም አሟጠው እየሰሩ መሆናቸውን አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ - ሜካኒካል ሥራዎች የሳይት አስተባባሪ አቶ አሊ ከሚል በበኩላቸው ጣቢያው አንድ ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር እንደሚገጠምለትና ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 5 ባለ 33 ኪ.ቮ እና 6 ባለ 15 ኪ.ቮ ወጭ መስመሮች እንደሚኖሩት ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት ያገኙ ለነበሩ እንደ ጭፍራ፣ ጎብየ፣ ቆቦ፣ ሮቢት እና ለሌሎች የሰሜን ወሎ ዞን አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጥ ይሆናል። በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና ቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለጹት በአሸባሪው የህወኃት ቡድን ዘረፋ የተፈጸመበትን የወልድያ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በአዲስ ለመገንባት እየተከናወነ ላለው ስራ የሚያስፈልጉ ዕቃዎች በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ስራ ጽ/ቤት አማካኝነት እየቀረቡ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ ስራ በተቋሙ ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስራክሽን የራስ ኃይል ቢሮ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን ለሥራው የግብዓት አቅርቦቱን ሳይጨምር ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ዕቅድ መያዙን ለማወቅ ተችሏል። ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዟል፡፡ ሙሉ በሙሉ በአሸባሪ ቡድኑ የተወሰደውን የወልዲያ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያን ወደነበረበት ለመመለስ እና በአዳዲስ ዕቃዎች ለመተካት በትንሹ እስከ 200 መቶ ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ከዚህ በፊት መገለጹ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 17 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+4

# News Update በባሌ ዞን በሚገኙ አካባቢዎች የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል የመጠገን ሥራ ከቀኑ 11:36 ላይ ተጠናቋል፣ ከመልካዋከና ሮቤ ያለው መስመር ዳግም እንዲገናኝ በመደረጉ አካባቢዎቹም ኃይል አግኝተዋል።

በባሌ ዞን በሚገኙ አካባቢዎች የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ነው ..........////..... በባሌ ዞን በሚገኙት የሮቤ፣ ጎባ፣ ጋሠራ፣ አጋርፋ፣ ሲናና፣ ዲንሾ እና አካባቢያቸው ከትናንት በስቲያ አንስቶ የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ነው። በዞኑ የኤሌክትሪክ መቋረጥ ያጋጠመው ከመልካ ዋከና የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ሮቤ የሚሄደው መስመር በዲንሾ አካባቢ ተቆርጦ በመውደቁና የማከፋፈያ ጣቢያውን የከረንት ትራንስፎርመር በማቃጠሉ ነው። በኃይል ማከፋፈያው ላይ ያጋጠመውን ብልሽት በመጠገን አገልግሎቱን እስከምሽት ድረስ ለማስቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 16 ቀን 2014 ዓ/ም

የታርጫ ባለ 132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጀመረ …….////……… በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞን ታርጫ ዙሪያ ወረዳ የባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጀምሯል፡፡ በወረዳው አባ ዳሂ ቀበሌ በ1998 ዓ.ም. ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአባ ባለ 132/33 ኪ.ቮ. ማከፋፈያ ጣቢያ በደረሰበት የመሬት መንሸራተት ጉዳት የተነሳ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በማቋረጡ በወረዳው ጎሪቃ ቤርሳ ቀበሌ አዲስ ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ የግንባታው የሲቪል ሥራዎች ኃላፊ አቶ በላይ ሀብተገብርኤል እንደገለጹት ግንባታው በይፋ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ የማከፋፈያ ጣቢያው የመሰረት ሥራ 80 በመቶ፣ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ የመሰረት ግንባታ 90 በመቶ ተከናውኗል፡፡ የሠራተኞች የመኖሪያ ቤት የቅየሳ ሥራ መከናወኑንና አጠቃላይ የሲቪል ሥራው 23 በመቶ መድረሱን አቶ በላይ ገልፀዋል፡፡ በአካባቢው እንደ ድንጋይ፣ አሸዋና ጠጠር ያሉ የግንባታ ግብዐቶች እጥረት ቢኖርም ግንባታውን ከዓመት ባነሰ ጊዜ ለማጠናቀቅ ይሰራል ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች አስተባባሪ አቶ ደምረው ታደሰ በበኩላቸው የሲቪል ሥራዎችን ተከትሎ የኤሌክትሮ መካኒል ሥራዎችን ለመሥራት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ የመሬት መንሸራተት ከገጠመው ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሮ መካኒካል ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመፍታት አጓጉዞ በአዲሱ ማከፋፈያ ጣቢያ ለመትከል ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ ይህም ፕሮጀክቱ በፍጥነት ለማጠናቀቅ ዕድል ይሰጣል ያሉት አቶ ደምረው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች አፈፃፀም 10 ነጥብ 15 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል ደመላሽ ዳምጠውና ማርታ ከበደ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ወጣቱ ተወልዶ ባደገበት መንደር የሥራ ዕድል መፈጠሩ ሥራ ለማግኘት ወደሌላ አካባቢ መጓዝን ያስቀራል ብለዋል፡፡ በሚነሳው እና አዲስ በሚገነባው ማከፋፈያ ጣቢያ ዙሪያ ከአካባቢው ነዋሪዎችና ከታርጫ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ጋር ውይይቶች ተደርገው ለፕሮጀክቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ጥበቃ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል፡፡ በአባ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ጉዳት ከደረሰ በኋላ ቀደም ሲል ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በጊዜያዊነት በማቋቋም አገልግሎቱን ሲያገኙ ቆይተዋል፡፡ አዲሱን ማከፋፈያ ጣቢያ የሚገነባው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ቢሮ ሲሆን ለሥራው ከ65 ሚሊየን ብር በላይ በጀት ተመድቦለታል፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው 5 ወጪ መስመሮች ያሉትና አንድ ባለ 20/25 MVA ትራንስፎርመር ይኖሩታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 16 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+9

በተቋሙ ዘመናዊ የሆነ ተንቀሳቃሽ ወይም ሞጁላር (Modular) ዳታ ማዕከል ተገነባ ……///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰራሩን ለማዘመንና ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ ዘመናዊ የሆነ ተንቀሳቃሽ ወይም ሞጁላር (Modular) ዳታ ማዕከል መገንባቱን ገለፀ፡፡ የተቋሙ የአይሲቲ መሠረተ ልማት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደገለፁት የዳታ ማዕከሉ መገንባት ለድርጅቱ ወሳኝ የሆኑትን የመረጃ ሥርዓቶች ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ለማስቀመጥ፣ በቀላሉ ለመጠቀም፣ ለማስተዳደር እና ለመቆጣጠር ያስችላል፡፡ እንደ ወ/ሮ ጽዮን ገለጻ ዳታ ማዕከሉ የሰርቨር፣ የኤሌክትሪክ ገቢ ዋና የስርጭት ቦርድ እና የማዕከሉን የመቆጣጠሪያ ክፍሎችን ያየዘ ሲሆን የማዕከሉን ደህንነት ለመጠበቅ የበር መቆጣጠሪያ (Door Access Control System) ተገጥሞለታል፡፡ ለማዕከሉ ደህንነት አጋዥ የሆኑ 16 ካሜራዎች እንደተገጠሙለትና የዳታ ማዕከሉን ዕቃዎች ለመቆጣጠር የሚያስችል Data center Infrastrucutre Manager የሚባል ሲስተም መተግበሩን ሥራ አስኪያጇ አብራርተዋል፡፡ ሰርቨሮች የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እንዳይገጥማቸው ጀነሬተር እና ዩ ፒ ኤስ እንደተገጠመላቸውና የዳታ ማዕከሉን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የማቀዝቀዣ (cooling system)፣ የሙቀት፣ የጭስ እና የውሃ ፍሳሽ መቆጣጠሪያ ሴንሰሮች የተገጠመለት ዘመናዊ ማዕከል መሆኑ ተገልጿል፡፡ የማዕከሉን ግንባታ ISYX TECHNOLOGIES L.L.C በሚባል የውጭ ሃገር ኩባንያ ነው፡፡ ማዕከሉን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 173 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር የወጣ ሲሆን የተሽፈነውም በተቋሙ በጀት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 12 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content

photo content
+3

ጉዳት የደረሰበትን የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ነው ........./////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከደብረብርሃን ኮምቦልቻ በሚሄደው የባለ230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የሚገኘውን የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር (OPGW) ጥገና እያከናወነ ነው። በአሸባሪው የህወኃት ቡድን ጉዳት የደረሰበትን የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር የመጠገን ሥራ በአብዛኛው የተጠገነ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ አንድ ተጨማሪ ቀን ብቻ የሚያስፈልግ ይሆናል። ጥገና የሚደረግበትን ቀን አስቀድመን የምናሳውቅ ይሆናል። ዛሬ በሸዋሮቢት፣ በከሚሴ፣ በአቀስታ፣በዓለም ከተማ፣ በኮምቦልቻ፣ በደሴ፣ በወልዲያ እና አካባቢያቸው በከፊል እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት ኤሌክትሪክ ተቋርጦ እንደሚቆይ ማስታወቃችን ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 11 ቀን 2014 ዓ/ም

ነገ በሸዋሮቢት፣ በከሚሴ፣ በአቀስታ፣በዓለም ከተማ፣ በኮምቦልቻ፣ በደሴ፣ በወልዲያ እና አካባቢያቸው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል ........./////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከደብረብርሃን ኮምቦልቻ በሚሄደው የባለ230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የሚገኘውን የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር የመጠገን ሥራ ያከናውናል። በዚህ የተነሳ ነገ እሁድ መጋቢት 11 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 12:00 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ድረስ በሸዋሮቢት፣ በከሚሴ፣ በአቀስታ፣ በዓለም ከተማ በኮምቦልቻ፣ በደሴ፣ በወልዲያ እና አካባቢያቸው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል። በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚሰራው የጥገና ሥራ የነዋሪውን መደበኛ እንቅስቃሴ ሳያውክ በሳምንት አንድ ቀን እሁድ ላለፉት አራት ሳምንታት ለተወሰኑ ሰዓታት ብቻ በከፊል ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ጥገናው ሲከናወን ቆይቷል። በዚህም ተቋማችን እያከናወነ ያለውን ሥራ በመገንዘብ ላሳያችሁት ትዕግስት እያደነቅን የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በትዕግስት እንድትቆዩን በአክብሮት እናሳስባለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 10 ቀን 2014 ዓ/ም

የጽሑፍ ፈተና ጥሪ
+2
የጽሑፍ ፈተና ጥሪ

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ፕሪሚዬር ሊጉን ሊቀላቀል ከጫፍ ደርሷል .......////.......... በከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ተደልድሎ እየተጫወተ የሚገኘው ኢትዮ ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የኢትዮጵ
+1
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ፕሪሚዬር ሊጉን ሊቀላቀል ከጫፍ ደርሷል .......////.......... በከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ተደልድሎ እየተጫወተ የሚገኘው ኢትዮ ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግን ለመቀላቀል ተቃርቧል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በትናንትናው ዕለት የሻሸመኔ አቻውን 1ለ0 በመርታት መርሀ ግብሩ ሊጠናቀቅ ሶስት ጨዋታ እየቀረው በ32 ነጥብ ተከታዮቹን አርሲ ነገሌንና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በ4 ነጥብ ልዩነት እየመራ ይገኛል። ክለቡ ካሉት ቀሪ ሶስት ጨዋታዎች ሁለቱን ካሸነፈ የማንንም ውጤት ሳይጠብቅ በቀጥታ ፕሪሚየር ሊጉን የሚቀላቀል ይሆናል። የክለቡ የቦርድ አባል አቶ መንግስቱ ዓባይነህ በባህርዳር ኢንተርናሽናል ስቴዲየም እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ ግብር በአካል በመገኘት ተጫዋቾችን አበረታተዋል። የክለቡን አደረጃጀት ለማዘመንና አሠራሩን ቀልጣፍ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ለቡድኑ ውጤታማነት ጉልህ ድርሻ ማበርከታቸውን አቶ መንግስቱ ገልፀዋል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በዚህ ዓመት ፕሪሚዬር ሊጉን ከተቀላቀለ የ10 ሚሊዮን ብር ጉርሻ እንደሚያገኝ በክለቡ ቦርድ ቃል እንደተገባለት መዘገባችን ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 08 ቀን 2014 ዓ/ም

የጥገና ሥራዉ የሠራተኛው አቅም የታየበት ነው- በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችና አመራሮች …….////……… አሸባሪው የህወኃት ቡድን ውድመት ያደረሰበትን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመጠገን በተደረገው ርብርብ የሠራተኛው የመስራት አቅም የታየበትና ከዚህም በላይ መስራት እንደሚችል የተረጋገጠበት መሆኑን በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የማስተላለፊያ መስመሮች የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊና የጥገና ስራው አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የደረሰውን ውድመት መልሶ ለመጠገን እና ህብረተሰቡ በአፋጣኝ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከስምንቱ ሪጅኖች እና ከራስ ኃይል ቢሮ የተውጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ ወደ ጥገና ሥራው ሲገባ ከፍተኛ ውድመት አጋጥሞ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተስፋዬ ሥራው በቅንጅት በመሰራቱ እና ለጥገና ሥራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎችና የሰው ኃይል በማሟላት ዝግጅት በመደረጉ ህብረተሰቡ በአጭር ጊዜ ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ ህብረተሰቡ ከነበረበት የስነ ልቦና ችግር ተላቆ ወደ ቀየው እንዲመለስ እና አካባቢውን እንዲያረጋጋ ለማድረግ ከተከናወነው ሥራ በተጓዳኝ ሠራተኛውን በማደራጀት ጥገናው በተነሳሽነት ስሜት እንዲከናወን ተቋሙ ከፍተኛ ርብርብ ማድረጉንም አስረድተዋል፡፡ እየተከናወነ ባለው የጥገና ሥራ የሠራተኛው አንድነት፣ ተነሻሽነትና አቅም የታየበት እንዲሁም ከዚህ የባሰ ችግር ቢመጣም ችግርን ተቋቁሞ ለውጤት የሚሰራ ጠንካራ ሠራተኛ እንዳለን ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ ሥራው ወደፊት ተቋሙ የሚያከናውናቸውን ትልልቅ ሥራዎች በራስ አቅም ለመስራት ልምድ የተገኘበት ነው፡፡ በሰሜን ምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ኃላፊ አቶ ፀሐይነህ አበበ በበኩላቸው ሠራተኛው የተለያዩ መሰናክሎችን በመቋቋም ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ በቁርጠኝነት ሲሰራ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ የጥገና ሥራው የሠራተኛውን አቅም ለመለየትና በራስ አቅም መስራት እንደሚቻል ያረጋገጠ ነው ያሉት አቶ ፀሐይነህ፡፡ በጥገና ስራው ላይ እየተሳተፉ ከሚገኙት ባለሙያዎች መካከል የሰሜን ምስራቅ ሪጅን የጥገና ባለሙያ የሆኑት አቶ ያረጋል ታዬ እና በትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስትራክስን የራስ ኃይል ቢሮ ሠራተኛ የሆኑት አቶ ፀሐዬ ማቼ በበኩላቸው ከአካባቢው መልከዓ ምድር አቀማመጥ የተነሳ ሥራው አሰልቺና አድካሚ ቢሆንም ሠራተኛው ችግሩን በመቋቋም በእልህና በቁጭት ሰርቶ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ ህብረተሰቡ በጦርነት ከደረሰበት ጉዳት በተጨማሪ በኤሌክትሪክ ኃይል ችግር ምክንያት ለሌላ ቀውስ እንዳይዳረግ ተቋሙ አጥጋቢ ሥራ እየሰራ እንደሆነና በቀጣይ ይህን ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የስራ መሪዎቹና ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የጥገና ስራ ተቋሙ የህዝብ አገልጋይ መሆኑን እንዳሳዩ ሁሉ በቀጣይ በሚከናወኑ ስራዎች ላይ ህዝቡን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 08 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+8

ጉዳት የደረሰበትን የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ነው …….///…….. በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአሸባሪው የተፈረጀው የህወሃት ቡድን በወረራ ይዟቸው በቆየባቸው በምስራቅ አማራ እና በአፋር የተወሰኑ አካባቢቢዎች ላይ የተጎዱ የፋይበር ኦፒቲክስ (OPGW) መስመሮችን የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይበር ኦፕቲክስ የኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ስራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ገብረ መድህን እንደተናገሩት ከኮምቦልቻ- ሰመራ፣ ከሸዋሮቢት - ኮምቦልቻ፣ ከኮምቦልቻ- አላማጣ እንዲሁም ከኮምቦልቻ- አቀስታ ከኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ምሶሶዎች አናት ላይ ተዘርግተው በሚገኙ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮቹ ለኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መከላከያ (protection) ከመስጠት ባለፈ ለቴሌኮሙዩኒኬሽን ሥራዎች እና ከኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መረጃዎችን ወደ ብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለማድረስ እንደሚያግዙ አቶ ኤርሚያስ አስረድተዋል፡፡ ይሁን እንጂ መስመሮቹ በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከሉ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች ያሉ መረጃዎችን መሰብሰብና መመልከት አለመቻሉን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም ጉዳት በደረሰባቸው መስመሮች ላይ የፋይበር ኦፕቲክስ ተከራይቶ ይጠቀም እንደነበር ያስታወሱት አቶ ኤርሚያስ በደረሰው ጉዳት ምክንያትም አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ጉዳት የደረሰባቸውን መስመሮች በመጠገን ወደ አገልግሎት ለማስገባት እየተሰራ እንደሆነም ሥራ አስኪያጁ አንስተዋል፡፡ የፋይበር ኦፕቲክስ የጥገና ስራ ጥንቃቄን የሚጠይቅና አድካሚ እንደሆነ ያነሱት አቶ ኤርሚያስ አገልግሎቱን ለህብረተሰቡ በወቅቱ ለማድረስ ሁሉም ሠራተኛ በከፍተኛ ተነሳሽነት፤ በመተሳሰብና በመደጋገፍ የጥገና ስራውን እያከናወነ ይገኛል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ጉዳት የደረሰባቸውን የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች ለመለየት የሚከናወነው ስራ ከጥገና ስራዉ የማይተናነስ አድካሚና አስቸጋሪ በመሆኑ ‘‘OTDR (Optical Time Domain Reflector’’ በተሰኘ ማሽን በመታገዝ ጉዳቱን በመለየት የጥገና ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በአካባቢው ያለው ህብረተሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ያገኘው ከረጅም ጊዜ በኋላ በመሆኑና ለጥገና ሥራ በሚል ኤሌክትሪክ በተከታታይ እንዳይቋረጥበት በማሰብ በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ጥገናው እየተከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ ከኮምቦልቻ- ሰመራ በተዘረጋው የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ላይ ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ በሚሆነው ላይ ጉዳት የደረሰበት ቢሆንም ሁሉንም በአዲስ በመቀየር ደሴ ከተማ ከሚገኘው የኢትዮ ቴሌኮም ሰርቨር ጋር ማገናኘት ተችሏል ብለዋል፡፡ ከሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ በተዘረጋው የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ላይ ደግሞ 33 ኪሎ ሜትር በሚሆነው ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 18 ኪሎ ሜትር የሚሆነውን በአዲስ መቀየር መቻሉን ነው የጠቆሙት፡፡ የ15 ኪሎ ሜትሩን ቀሪ ሥራዎች በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት በሚገኙት እሁድ ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አመልክተዋል፡፡ ከኮምቦልቻ- አቀስታ ባለው የፋይበር ኦፐቲክስ መስመር ላይ 1 ኪሎ ሜትር በሚሆነው ላይ ጉዳት እንደደረሰበትም ታውቋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ15 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች እንደሚገኙ ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ አሸባሪው የህወሃት ቡድን የአማራና አፋር ክልሎችን በወረራ ይዞ በቆየባቸው አካባቢዎች ከሚገኙ የማስተላለፊያ መስመሮች መካከል በ53 ነጥብ 3 በመቶው ላይ ጉዳት ማድረሱን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 06 ቀን 2014 ዓ/ም