en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 537 subscribers, ranking 8 368 in the Technologies & Applications category and 2 174 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 537 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.86%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.87% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 862 views. Within the first day, a publication typically gains 2 620 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 537
Subscribers
-624 hours
-207 days
+1030 days
Posts Archive
የሥራ አመራር ቡድኑ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ጎበኘ .........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የበላይነህ ክንዴ ሜታል ኢንጂነሪንግ ፋብሪካን ጎበኘ። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዷለም ሲዓ  የተመራው ቡድን በገላን ከተማ የሚገኘውን በፋብሪካው የመኪና መገጣጠሚያ ወርክሾፕ የተገጣጠሙ  የኤሌክትሪክ፣ የከባድ ደረቅ ጭነት እና የፈሳሽ ጭነት ተሽከርካሪዎችን የገጠማ ሂደት ተመልክተዋል። የበላይነህ ክንዴ ብረታብረት ኢንጂነሪንግ ስራ አስኪያጅ በሱፍቃድ ሸዋዬ እንደገለፁት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎቹ በአንድ ጊዜ ቻርጅ ብቻ ከ270 እስከ 350  ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ። ፋብሪካው ላመረታቸው ተሽከርካሪዎች ባትሪ የስምንት ዓመት እንዲሁም  ለሞተር  የአምስት ዓመት ዋስትና ይሰጣል። የመለዋወጫ አቅርቦት ዝግጁ መደረጉን እና ከሽያጭ በኃላ ሰርቪስ ማድረጊያ ቦታ ቄራ አካባቢ መዘጋጀቱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ፋብሪካው አስራ አምስት ቻርጂንግ ማድረጊያዎችን አስመጥቶ ለሙከራ ቢገጥምም ባለሦስት ፌዝ የኤሌክትሪክ መስመር የሚፈልግ  በመሆኑ ቻርጅ ማድረጊያዎችን በተለያዩ አካቢዎች በጋራ መትከል የሚቻልበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቀዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዷለም ሲዓ በበኩላቸው ፋብሪካው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መግጠም የጀመረበት ሰዓት  ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጨማሪ ዩኒቶች ወደሥራ በሚገቡበትና እንደሀገር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት በተሰጠበት ወቅት ነው። በመሆኑም የሁለቱ ተቋማት አጋርነት በተሽከርካሪ ብቻ ሳይገደብ በሚያድግበት ሁኔታ ላይ ለመስራት ተቋሙ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በሰጡት አስተያየት ፋብሪካው  የውጭ ምንዛሪ የሚያድን እና የስራ ዕድል የሚፈጥር  መሆኑን  በጉብኝቱ መመልከታቸውን ተናግረዋል። የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ እና የቦርድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰጠኝ እንግዳው እንደተናገሩት ፋብሪካው ከብክለት የፀዳ ሀገር ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ  ነው። በዚህ ሂደት ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  ከግሩፑ ጋር አብሮ እንደሚሰራ  ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልፀዋል። የበላይነህ ክንዴ ብረታብረት ኢንጂነሪንግ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ1400 በላይ የከባድ ደረቅ ጭነት እና የፈሳሽ ጭነት  ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም 216 በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሚኒባሶችን ገጣጥሟል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 09 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ብቃትን መሠረት ያደረገ አሰራር ለማስፈን እየተሰራ ነው …….///……… የአመራር እና ሙያ ብቃትን ማዕከል ያደረገ አሰራር ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ስልጠና እና ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥር ለሚገኙ የኃይል ማመንጫ ኃላፊዎች እና ዳይሬክተሮች በውጤት ተኮር አመራር ብቃት ላይ ያተኮረ ሥልጠና በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ማሰልጠኛ ተቋም መሠጠት ጀምሯል፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሥልጠናው የስራ መሪዎች ብቃትን መሰረት ያደረገ ድጋፍ እና ክትትል እንዲሁም የላቀ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ለማከናወን ያግዛል፡፡ የስልጠና እና ልማት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ አዲስ ዓለም ብርሃኔ በበኩላቸው ሥልጠናው በዋናነት የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት እና የአመራር ክህሎትን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሥልጠናው ላይ በሥራ አመራር ብቃት ዘርፍ የክህሎት፣ የዕውቀት እና የአመለካከት አድማስን የሚያሰፉ ርዕሰ ጉዳዮች እንደሚነሱ ይጠበቃል፡፡ ሥልጠናው ለተቋሙ የስራ መሪዎች ለአምስተኛ ዙር እየተሰጠ ሲሆን ለስምንት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 07 ቀን 2016 ዓ.ም

የሥራ ማስታወቂያ ህዝብ 2 እና ህዝብ 3 ወይም 4ኛ እና 5ኛ መንጃ ፍቃድ ላላችሁ
የሥራ ማስታወቂያ ህዝብ 2 እና ህዝብ 3 ወይም 4ኛ እና 5ኛ መንጃ ፍቃድ ላላችሁ

photo content
+5

የስድስት ጉድጓዶች የምርት ሙከራ ሥራ ተጠናቋል .........///........ በአሉቶ ላንጋኖ የከርሰምድር እንፋሎት ፕሮጀክት ከተቆፈሩት 10 የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ጉድጓዶች መካከል የስድስት ጉድጓዶች ቁፋሮ ተጠናቆ የምርት ሙከራ ሥራ መከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጂኦተርማል ሴክተር ልማት ፕሮጀክት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መሳይ ፈቃዱ እንደተናገሩት የቀሪ አራት ጉድጓዶች የሙከራ ሥራ እስከ ታህሳስ 2016 ዓ.ም ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ የአራት ተጨማሪ ጉድጓዶች ቁፋሮ ለማከናወን ከዓለም ባንክ ጋር ስምምነት ላይ በመደረሱ የፕሮጀክቱ ሥራ እስከ መስከረም 2017 ዓ.ም መራዘሙን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ የምርት ሙከራ ከተከናወነባቸው ስድስት ጉድጓዶች 25 ሜጋ ዋት ኃይል መገኘቱንም ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ ከዓለም ባንክ በብድር በተገኘ 143 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እየተከናወነ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 24 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላሩ በድጋፍ የተገኘ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት፡፡ የእንፋሎት ኃይል ግንባታ ዘርፍ በሀገራችን አዲስ እንደመሆኑ ከፕሮጀክቱ ባሻገር በዘርፉ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ መሳይ የተቋሙ ባለሙያዎች በሥራ ላይ ስልጠና ተጨባጭ እውቀት እና ክህሎት ማግኘታቸውን አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ለ110 ኢትዮጵያዊያን ቋሚ፣ ለ40 ዜጎች ደግሞ ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ 70 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የታለመ ሲሆን የመጀመሪያ ምዕራፍ 35 ሜጋ ዋት ከተከናወነ በኋላ ሁለተኛው ምዕራፍ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ለመላው ኢትጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ እያልኩኝ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ በመጠናቀቅ ላይ ያለው 2015 ዓ. ም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዳዲስ ዕድሎችና መልካም አጋጣሚዎች የተፈጠሩበት ዓመት ነበር፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዩኒት ሥራ የጀመረበት፣ በከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ የተገነባው የኢትዮ ኬንያ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ወደኬንያ በይፋ ኃይል ማስተላለፍ የጀመረበት፣ በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የተጎዱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች መልሶ ጥገና ሥራ የተጠናቀቀበት፣ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ተደጋጋሚ የታወር ስርቆት የተከሰተበት፣ በኃይል ኤክስፖርት ሽያጭ ዙሪያ ከሀገራት ጋር ፈታኝ ድርድሮች የተካሄዱበት ዓመት ነበር፡፡ በመሆኑም ያገባደድነውን ዓመት ስናስብ ትውስታችን በብዙ መልካምና ፈታኝ አጋጣሚዎች ተሞልቶ እናገኘዋለን፡፡ ኤሌክትሪክ አኗኗራችንን ቀላል ካደረጉ የሰው ልጅ የፈጠራ ውጤቶች መካካል አንዱ ሲሆን ከጥቃቅን እስከ ግዙፍ የኢኮኖሚ ዘርፎች የጀርባ አጥንት ሆኖ ከመገኘቱ በተጨማሪ ለምንመገበው ምግብ፣ ለምንለብሰው ልብስ፣ ለምንኖርበት ከባቢ ዓለም ወሳኝ በመሆኑ በአሁን ዘመን ከሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶች መካከል አንዱና ወሳኝ መሆኑ እሙን ነው፡፡ በአፄ ምኒልክ ዘመነ መንግስት በ1890 ዓ.ም በነዳጅ በሚሰራ ትንሽ ጀነሬተር ሥራውን አንድ ብሎ የጀመረው የዛሬው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ጊዜያት ልዩ ልዩ አደረጃጀቶችና መጠሪያዎችን ተጠቅሟል፡፡ ለአብነት በ1940 ዓ.ም “የሸዋ መብራት ኃይል”፣ በ1948 ዓ.ም “የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ባለሥልጣን”፣ በ1989 ዓ.ም ደግሞ “የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን” በመባል የኤሌክትሪክ ኃይልን በማቅረብ ለሀገራችን ስልጣኔ መስፋፋት የበኩሉን ሚና ሲወጣ የቆየ አንጋፋ ተቋም ነው፡፡ መንግስት እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ ሁኔታ ለማሟላት እና አገልግሎቱን የተሳለጠ ለማድረግ በ2006 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት በሚል የተለያየ ሚና ወዳላቸው ሁለት ተቋማት አንዲከፈሉ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተሻሻለው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 381/2008 የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡ ለተቋሙ ከተሰጡት ተልዕኮዎች መካከል የኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እንዲሁም ማስተላለፊያ መስመሮችን መገንባትና አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ እንዲሁም የግንባታ ሥራዎች የአዋጭነት ጥናት፣ የንድፍ እና ቅየሳ ሥራዎችን ማከናወን፣ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በአማካሪ ማሰራት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል በጅምላ መግዛት እና መሸጥ የሚሉት ዋንኞቹ ናቸው፡፡ ተቋማችን በህዝብና በመንግስት የተጣለበትን ሀገራዊ ግዴታ በብቃት ለመወጣት “የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል መሆን” የሚል ራዕይ ሰንቆ በሀገሪቱ ካሉ የተለያዩ ታዳሽ የኃይል ምንጮች የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን እና ከ132 – 500 ኪሎ ቨልት መጠን ያላቸው የተለያዩ የኃይል ማከፈፈያ ጣቢያዎችን እንዲሁም ማስተላለፊያ መስመሮችን በመገንባት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ከምንጊዜውም በላይ እየተጋ ይገኛል፡፡ በየዓመቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት ተቋማችን በአሁኑ ወቅት እያደረገ ካለው እንቅስቃሴ በመጠንም ሆነ በጥራት የተሻለ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራችና አቅራቢ ተቋም መሆን የሚያስችለውን የ3 ዓመት፣ የ10 ዓመት እና የ25 ዓመት መሪ ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ከገባ ወራት ተቆጥረዋል፡፡ የተከበራችሁ የተቋማችን አመራርና ሠራተኞች ተቋማችን በረጅም፣ በመካከለኛ እና በአጭር ጊዜ ለመተግበር ለነደፋቸውን ዕቅዶች መሳካት ሁላችንም በተሰማራንበት ሙያ መስክ በቅንነትና በታማኝነት፣ በተቆርቋሪነት እንዲሁም በአብሮነት ከምንጊዜውም በላይ ተግታችሁ እንድትሰሩ አደራ እላለሁ፡፡ በመጨረሻም ተቋሙ ከፍተኛ ኃይል በማምረትና መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት መላው የሀገሪቱን ሕዝብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል፡፡ ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በፍትሐዊነት ለማስፋፋት በጀመረው ጥረት ላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ተሸካሚ ብረቶች ስርቆት ትልቅ ፈተና ሆኖበታል፡፡ በመሆኑም በየትኛውም አካባቢ የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ስርቆቶችን እና ጉዳት የሚፈፅሙ ብርሃን ነጣቂዎችን መከታተልና ለህግ ማቅረብ የሁሉንም ህብረተሰብ እና በየደረጃው ያሉ አመራር አካላት እገዛ የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብና አመራሩ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡ አዲስ ዓመት ተስፋ ሰጪ በመሆኑ ሁሌም አዲስ ነው፣ አዳዲስ መፍትሄዎች እና ሞቅ ያለ ምኞት ለሁላችን እየተመኘሁ መጪው አዲስ ዓመት በሀገራችን የሚስተዋሉ የፀጥታ ስጋቶች ተቀርፈው በሀገራችን ሠላም፣ ደስታ፣ ዕድገትና ብልፅግና የምናይበት ዓመት እንዲሆንልን ከልብ እመኛለሁ፡፡ መልካም አዲስ ዓመት አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

photo content

ለአዲስ ዓመት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል ………////……… ለ2016 አዲስ ዓመት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ የማነ ኢሳይያስ እንደገለፁት ካለፉት ዓመታት የበዓል የኃይል አጠቃቀም አዝማሚያ በመነሳት በዘንድሮ አዲስ ዓመት እስከ 3 ሺህ 83 ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚያስፈልግ ተተንብይዋል፡፡ በመሆኑም በሁሉም የኃይል ማመንጫዎች አስቀድሞ የጥገናና የፍተሻ ሥራ በማከናወን እስከ 3 ሺህ ስድስት መቶ ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በበዓሉ ዋዜማና በበዓሉ ዕለት የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎችም ሆነ ኃይል ኤክስፖርት የሚደረግባቸው ሀገራት ቀድሞ ይጠቀሙ የነበረውን ኃይል ያለምንም ችግር እንዲጠቀሙ እስከ አምስት መቶ ሜጋ ዋት ድረስ በመጠባበቂያነት መያዙንም ነው የገለፁት፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም ሆነ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ኃይል የሚያገኙ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎች እና ግዙፍ ኢንደስትሪዎች የሚጠቀሙባቸው መስመሮች በኃይል እጥረት የተነሳ እንደማይቋረጡ ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል፡፡ በኃይል ማመንጫዎች፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎችና በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ አስቀድሞ የፍተሻ እና የጥገና ሥራ መከናወኑን የጠቆሙት አቶ የማነ ድንገተኛ ችግር ቢያጋጥም አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ቡድን ዝግጁ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ለማድረስ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመወያየት የዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

ተቋሙ የትውልድ ቀጣይነት ላይ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው .........////........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በአሉቶ እና አካባቢው ትምህርት ቤቶችን ገንብቶና ጠግኖ ለአዳሚ ቱሉ ጂዶ ኮምቦልቻ ወረዳ አስተዳደር አስረከበ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጂኦተርማል ሴክተር ልማት ፕሮጀክት ዳይሬክተር አቶ መሳይ ፈቃዱ እንዲሁም የአዳሚ ቱሉ ጂዶ ኮምቦልቻ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ሹሚ ገለቶ በተገኙበት የርክክብ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል፡፡ የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከ29 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ ስድስት የመማሪያ ብሎኮችን ጨምሮ የቤተ-መፅሃፍት፣ የመምህራን ቢሮ እና የቤተ ሙከራ ብሎኮችን በመገንባት ለወረዳው አስተዳደር ማስረከቡን አቶ መሳይ ተናግረዋል፡፡ አቶ መሳይ እንደገለፁት ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ በወረዳው በሚገኙ ጎልባ አሉቶ እና አበያ ደነባ ቀበሌዎች ሁለት አዳዲስ ትምህርት ቤቶች የገነባ ሲሆን በሁለት ነባር ትምህርት ቤቶች ላይ ደግሞ የዕድሳት እና የማስፋፊያ ግንባታ አከናውኗል፡፡ ተቋሙ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ጥራታቸውን የጠበቁ ከ710 በላይ ወንበሮች፣ ጠረጴዛዎች፣ ጥቁር ሰሌዳዎች እና የመፅሃፍት መደርደሪያ ሸልፎች ድጋፍ ማድረጉን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም 38 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአካባቢውን ማህበረሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ የፕሮጀክቱ አፈፃፀምም 50 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል፡፡ የአካባቢውን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግም 24 ሚሊዮን ብር በመመደብ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል እንዲገነባ ስምምነት ላይ መደረሱንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት፡፡ አቶ መሳይ እንደገለፁት በአጠቃላይ ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ ማህበረሰብ ተኮር ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን በፕሮጀክቱ ምክንያት ከቦታቸው ለተነሱ የአካባቢው ነዋሪዎችም 5 ሚሊዮን ብር በመመደብ በንግድ፣ በእንስሳት ማድለብ እና በመስኖ ልማት እንዲሰማሩ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ ተችሏል፡፡ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ በበኩላቸው ከዚህ በፊት የነበሩ ትምህርት ቤቶች ያረጁና የጭቃ ክፍሎች እንደነበሩ አስታውሰው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገነቡት ትምህርት ቤቶች በብሎኬት የተገነቡና ወለላቸውም ሲሚንቶ በመሆኑ ለተማሪዎች ምቾት ይፈጥራል ብለዋል፡፡ የተገነቡት ትምህርት ቤቶች በአጠቃላይ ከ720 ተማሪዎች በላይ እንደሚያስተናግዱ የገለፁት ኃላፊው የትምህርት ተደራሽነትን እና የትምህርት ጥራትን ከማሳደግ አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡ አቶ ደጀኔ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክቶችን በሚገነባበት ወቅት ለአካባቢው ማህበረሰብ እያደረገ ያለው አስተዋጽኦ እያደገ የመጣ ሲሆን በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት በርካታ ማህበራዊ ተቋማትን በመገንባት የህዝብ ተቋም መሆኑን አረጋግጧል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 በጀት ዓመት ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በርካታ የማህበረሰብ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ከመገንባቱም ባሻገር በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ለሚገኙ የማህበረሠብ ክፍሎች የምግብ፣ የአልባሳት እና የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ጳጉሜን 05 ቀን 2015 ዓ.ም

የህዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት በስኬት ተጠናቋል ........///.......... የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አራተኛ ዙር ሙሌት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል
የህዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት በስኬት ተጠናቋል ........///.......... የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አራተኛ ዙር ሙሌት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በገንዘባችሁ፣ በዕውቀታችሁ፣ በጉልበታችሁና በጸሎታችሁ በሥራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ  እንኳን ደስ አላችሁ፤ ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል ብለዋል። የግድቡ አራተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ጳጉሜን 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9

የጣቢያው ሠራተኞች የሥራ ቅልጥና እና የዕርስ በዕርስ ግንኙነታቸውን የሚያሳድግ ተግባራት ላይ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ ነው ……..///……… የሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የሥራ ቅልጥፋናን ለማሳደግና የዕርስ በዕርስ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር የሚያግዝ መርሃግብር በየዓመቱ እያዘጋጁ መሆናቸውን የጣቢያው ሠራተኞችና አመራሮች ተናገሩ። ሠራተኞቹ በየዓመቱ የጳጉሜ ቀናት የተለያዩ የበጎ አድራጎት እና የዘመቻ ሥራ በማከናውን የሠራተኞችን ቀን ሲያከብሩ በጣቢያው ሰርተው በጡረታ የተሰናበቱ ሁለት ሠራተኞችንም በክብር ሸኝተዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደተናገሩት የጣቢያው ሠራተኞች እያካሄዱት ያለው ዓመታዊ መርሃ ግብር የተሰጣቸውን ተልዕኮ በቅንጅት ለመፈፀም ከማገዙም በተጨማሪ በቡድን የመስራት ዕሴቶችን ጠብቆ ለማቆየት ያግዛል። የጣቢያው ሠራተኞች በየዓመቱ ባሉ የጳጉሜ ቀናት ለሚያከናውኗቸው የበጎ አድራጎት ሥራዎች ዘርፉ በቀጣይ ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል። የሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዓለሙ እና የጣቢያው ሠራተኞች እሸቴ እንዳየሁ እና አማኑኤል ሰንበቶ በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት በየዓመቱ የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች መከበራቸው በአዲሱ ዓመት በአዲስ መንፈስ ወደ ሥራ እንድንገባ ያግዘናል ብለዋል። እንደ አስተያየት ሰጪዎቹ ገለፃ ቀኑ የሠራተኛውን የዕርስ በዕርስ መረዳዳትና ግንኙነቱን ለማጠናከር፣ በበጎ አድራጎት ሥራ ላይ እንዲሳተፍ ለማድረግ፣ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ እና ሥራዎችን በመተሳሰብና በመረዳዳት በተቀላጠፈ መልኩ ለማከናወን ዕድል ፈጥሯል። የሠራተኞች ቀን ሠራተኛው ዕርስ በዕርስ በመገማገም ከክፍተቱ የሚማማርበት እና በአፈፃፀም የደከመውን ለማበረታታት እያገዘ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የዘንድሮው የሠራተኞች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ባለው "የአምራችነት ቀን" መከናወኑ ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀው ሠራተኛው የተመረተውን ኃይል ለተጠቃሚው በአግባቡ እንዲደርስ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል። በጣቢያው ላይ ሠራተኛ የነበሩትና በጡረታ ከስራ የተሰናበቱት አቶ ሰሎሞን ዮሴፍ በተቋሙ ላይ ከ34 ዓመታት በላይ በተለያዩ የሥራ በታዎች ላይ እንዳገለገሉ ገልፀው በሥራ ባልደረቦቻቸው ስለተደረገላቸው ሽኝትም አመስግነዋል። በተቋሙ በቆዩባቸው ጊዜያት ሠራተኞች ሥራቸውን በፍቅር እንዲያከናውኑ፣ በማከፋፈያ ጣቢያው የሚያጋጥሙ ችግሮች በወቅቱ እንዲፈቱ እንዲሁም በሠራተኛውና በተቋሙ መካከል ጤናማ ግንኙነት እንዲፈጠር የሚያግዙ ሥራዎችን ማከናወናቸውን አስታውቀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው እያከናወነ ያለውን የሠራተኞች ቀን በሌሎች ጣቢያዎች ለማስፋፋት መታሰቡን ከመርሀግብሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤን ጨምሮ የማዕከላዊ ሪጂን 3 የሥራ መሪዎች፣ በሪጂኑ ሥር የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች፣ የጣቢያው ሠራተኞችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የተቋሙ ሠራተኞች ተገኝተዋል። “ንፁህ ታዳሽ ኃይል ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ዘኢትዮጵያን ሄራልድ ላይ የታተመ የዋና ሥራ አስፈፃሚያችን የአዲስ ዓመት ምኞት
ዘኢትዮጵያን ሄራልድ ላይ የታተመ የዋና ሥራ አስፈፃሚያችን የአዲስ ዓመት ምኞት

photo content
+3

የማመንጫ ጣቢያዎቹ ሠራተኞች በከተማ ግብርና ላይ ውጤታማ ሥራ እያከናወኑ ነው ……..///……. የአዋሽ 2 እና 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሠራተኞች ከተሰጣቸው ኃይል የማመንጨት ተልዕኮ በተጨማሪ በከተማ ግብርና ውጤታማ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን የጣቢያዎቹ የጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሮቤል አበበ እንዳስታወቁት በጣቢያዎቹ እየተከናወነ የሚገኘው የጓሮ እርሻ ልማት በጣቢያዎቹ የሠራተኞች የመረዳጃ ዕድር በባለቤትነት የሚተዳደር ነው፡፡ የጣቢያዎቹ ሠራተኞች በቅርብ የሚደርሱ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን እያለሙ ከራሳቸው አልፎ ለአካካቢው ማህበረሰብ እና ነጋዴዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ ከልማቱ በፍትሐዊነት ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አቶ ሮቤል ተናግረዋል፡፡ የጓሮ እርሻ ልማቱ ሠራተኛው ሰዓቱን በአግባቡ እንዲጠቀም ለማድረግ እና በተቋሙ ላይ የባለቤትነት ስሜት ተሰምቶት ሥራውን በአግባቡ እንዲያከናዉን ለማድረግ እንዳገዘም ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡ በጣቢያው እየተከናወነ ያለው የልማት ሥራ ከዚህ በፊት በነበሩ የተቋሙ አመራሮች እውቅና ተሰጥቶት ሲሰራ የነበረው ሲሆን የአሁኑ ትውልድ ሠራተኞችም የተጀመረውን በማስቀጠል ለቀድሞ አመራሮች እውቅና መስጠት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡ የጓሮ እርሻ ልማቱን ሠራተኞች በትርፍ ጊዜያቸው በራሳቸው አቅም እና የተወሰኑ ሠራተኞችን በመቅጠር እያከናወኑት እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ ይህም በአካባቢው ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ሮቤል የማመንጫ ጣቢያዎቹ የሚገኙበት አካባቢ በደን የተሸፈነ መሆኑ የግብርና ሥራው አካባቢውን ጽዱ ለማድረግና ምቹ የሥራ ቦታ ለመፍጠር አግዟል ብለዋል፡፡ የጓሮ እርሻ ልማቱ ጣቢያው ባለው ውስን ቦታ ላይ በመስራት ከሠራተኞቹ አልፎ ወገንንም መጥቀም እንደሚችል ያሳየበትና "አዋሽ የአትክልት ቦታ ማዕከል ናት” የሚለውን ያረጋገጠ መሆኑን አቶ ሮቤል አንስተዋል፡፡ “ንፁህ ታዳሽ ኃይል ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 04 ቀን 2015 ዓ.ም