en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 539 subscribers, ranking 8 340 in the Technologies & Applications category and 2 161 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 539 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 1 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.98%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.34% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 882 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 539
Subscribers
-424 hours
-147 days
+130 days
Posts Archive
photo content
+2

photo content
+9

ጣቢያው የካይዘን የአሰራር ሥርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ማከናወኑን ገለጸ .......///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራውን ለማቀላጠፍ የሚያግዝ የካይዘን የአሰራር ሥርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ማከናወኑን አስታወቀ። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ አቶ ሀብታሙ ጌቱ እንደተናገሩት ለጣቢያው ባለሙያዎች የካይዘን አሰራር ሥርዓት ስልጠና ተሠጥቶ ከ8 ወራት በፊት ወደ ተግባር ተገብቷል። የካይዘን የአሰራር ሥርዓት ከመተግበሩ በፊት የጣቢያው የዕቃ መጋዘን ደረጃውን ያልጠበቀና ዕቃዎቹም በአንድ ቦታ በዘፈቀደ የተቀመጡ እንደነበረ ባለሙያው አብራርተዋል። በዚህም ዕቃዎቹ ለሥራ ሲፈለጉ በቀላሉ የማይገኙና ሲገኙም ለአገልግሎት በማይመች ሁኔታ በመሆኑ ውጤታማ ሥራ ለመስራት አዳጋች ነበር ብለዋል። እንደባለሙያው ገለጻ የካይዘን ስልጠናን ከወሰዱ በኋላ የሚሰሩና የሚወገዱ የመለዋወጫ ዕቃዎችና መሣሪያዎች የመለየትና የማደራጀት ሥራ ተሰርቷል። ለጣቢያው አስፈላጊ የሆኑ የመለዋወጫ ዕቃዎች ተለይተው በመደራጀታቸው ጣቢያው ያሉትን ዕቃዎች አውቆ ሥራውን ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሰራ በማስቻሉ ለጥገና ይወስድ የነበረውን ጊዜና አላስፈላጊ ወጭ ማስቀረት መቻሉን አቶ ሀብታሙ ገልጸዋል። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ አቶ ሽፈራው ማሞ በበኩላቸው የተደራጁት ዕቃዎችና መሥሪያዎችን ከሞላ ጎደል መለያ ተሰጥቷቸው በዳታ ቤዝ ተመዝግበው በሶፍት ኮፒ መቀመጣቸውን ገልጸዋል። የካይዘን አሰራርን በመተግበር ዕቃዎቹን ከብልሽትና ተቋሙን ከአላስፈላጊ ወጭ በማዳን ጣቢያው ያሉትን ንብረቶች አውቆ ውጤታማ ሥራ እንዲሰራ እንዳስቻላቸው ባለሙያው ተናግረዋል። በቀጣይም በጣቢያው ሁሉም የሥራ ክፍሎች የካይዘን የአሰራር ሥርዓትን በመተግበር በፋይናንስ፣ በሰው ኃይልና በንብረት ላይ የሚያጋጥሙ ብክነቶችን በመቅረፍና በአግባቡ በመጠቀም በጣቢያው ቀጣይነት ያለው ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ባለሙያዎቹ አረጋግጠዋል። ካይዘን የጃፓን የአሰራር ፍልስፍና ሲሆን ብክነትን በማስወገድ፣ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጭን በመቀነስ የተሻለ ለውጥ የሚያመጣ የአሰራር ሥርዓት ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር በ2013 የካይዘን ትግበራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 09 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የሥልጠና ማዕከሉን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው .........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥልጠና ማዕከል በሚሰጡ የስልጠና ርዕሶች እና በመርሀ ግብሩ ላይ ክለሳ በማድረግ ብቃት ያለውና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል ለማፍራት በጥናት የተደገፈ ዝግጅት መጀመሩን በተቋሙ የሰው ኃይል ሥልጠናና ልማት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ እንደገለጹት የሥልጠና ማዕከሉ ለተቋሙ ስመጥር ባለሙያዎችን በማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ ማዕከሉን በአሰራር፣ በግብዓት እና በአደረጃጀት ለማዘመን ዝግጅት መጀመሩን ተናግረዋል።  የስልጠና ማዕከሉ ወደ ተቋሙ ለሚቀላቀሉ የቅድመ አገልግሎት ሥልጠና እና በተቋሙ ለሚሠሩ ሠራተኞች የሥራ ላይ ሥልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ ደምስ ገልጸዋል። ከቅድመ አገልግሎት ስልጠና ጋር በተያያዘ ከተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በሜካትሮኒክስ እስከ ሌቭል 4 የተማሩ እና ተቋሙን የተቀላቀሉ ሠራተኞችን ለ6 ወር በኤሌክትሮ ሜካኒካል ዘርፍ ሥልጠና በመስጠት ለኦፕሬሽን ዘርፎች ባለሙያዎችን እያፈራ እንደሚገኝ ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። የተቋሙ ሠራተኞች  ያሉባቸውን  የክህሎት፣ የአመለካከትና የዕውቀት ክፍተት ለመሙላት ልዩ ልዩ ሥልጠናዎች እንደሚሰጥም ጠቁመዋል። የሴቶችን አቅም ለማጎልበትና የአመራር ሚናቸውን ለማሳደግ በየዓመቱ 55 ለሚሆኑ የተቋሙ ሴት ሠራተኞች ከዲፕሎማ እስከ ሁለተኛ ዲግሪ እንዲማሩ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። የሥልጠና ማዕከሉ ተቋሙ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጣ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የሥልጠና ማዕከላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ደምስ ገለፃ የስልጠና ማዕከሉን አቅም በማሳደግ በምስራቅ አፍሪካ ተመራጭ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ በቢሾፍቱ ከተማ ዘመናዊ የሥልጠና ማዕከል ለመክፈት እየተሰራ ነው። ማዕከሉ አሁን ላይ እስከ 120 ሰልጣኞችን በአንዴ ተቀብሎ የማሰልጠን አቅም ያለው ሲሆን ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ 700 የሚሆኑ ሠልጣኞችን በማሰልጠን በኦፕሬሽን የሥራ ዘርፎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጓል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ጥር  08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+6

የተቋሙ ዋና መ/ቤት ቅጥር ግቢ የአስፓልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነ ነው ..........///........ በኮተቤ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ የአስፓልት ንጣፍ ሥራ በቀጣዮቹ 10 ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የአፈፃፀም ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ታረቀኝ እንዳስታወቁት ከግቢ ዕድሳቱ ቀሪ ሥራዎች ከፍተኛውን ድርሻ የያዘው የውስጥ ለውስጥ መንገድና የተሽከርካሪ ማቆሚያ ቦታዎች የአስፓልት ንጣፍ ሥራ ነው፡፡ የአስፓልት ንጣፍ ሥራውን በ2015 ግማሽ ዓመት ላይ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች ሥራውን በተያዘለት መርሃ ግብር ማጠናቀቅ እንዳልተቻለ አንስተዋል፡፡ ሥራውን በሚቀጥሉት አስር ቀናት ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ እንደ አዲስ ይከናወናሉ ተብለው ከተያዙት ሥራዎች ውጪ የማጠናቀቂያ ጊዜው በመራዘሙ ምክንያት የተጨመረ በጀት እንደሌለ አቶ አክሊሉ አስረድተዋል። በዋና መስሪያ ቤት ለውጥ ምክንያት የግቢ ጥገናና የማስዋብ ሥራዎች በመላው ሠራተኛ እና አመራሮች ድጋፍና ክትትል አሁን ካለበት የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ሊደርስ በመቻሉ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። የስፖርት ማዘውተሪያ እና የመዝናኛ ሥፍራዎች በቀጣይ የሚከናወኑ የማጠናቀቂያ ሥራዎች መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ አክሊሉ ሥራው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። የመሬት ቁፋሮ ሙሊት፣ የስር አስፓልት መንገድ ኮንክሪት ንጣፍ፣ የላይ አስፓልት መንገድ ኮንክሪት ንጣፍ እና የአስፓልት ኮንክሪት ማንጠፍ ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን እስካሁንም 79 ከመቶ መከናወኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ በአመዛኙ በጣቢያው ሠራተኞች እየተከናወነ ነው ..........///........... የወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ጣቢያ 80 በመቶ የሚሆነው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራ በጣቢያው ባለሙያዎች እየተከናወነ እንደሚገኝ የጣቢያው የሳይት ሥራ አስኪያጅ ተወካይገለፁ፡፡ የጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያ እና የሳይት ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ፀጋው ታዬ እንደገለፁት ጣቢያው ከሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች በቴክኖሎጂና በሚሰጠው አገልግሎት የተለየ በመሆኑ የኦፕሬሽን ሥራውን ለማከናወን የዕውቀትና ክህሎት ክፍተቶች ነበሩ፡፡ የዕውቀትና ክህሎት ክፍተቶቹን በመሙላት የኦፕሬሽን ሥራውን ለማቀላጠፍ የሚያግዙ የውጪና የሀገር ውስጥ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ተወካዩ ገልፀዋል፡፡ ባለሙያዎች ከዩኒቨርሲቲ ያገኙትን የንድፈ ሀሳብ ዕውቀት ወደ ተግባር ቀይረው አቅማቸውን ለማጎልበት የሚያስችላቸውን ሥልጠና ከሁለት ወራት በላይ በህንድ ሀገር በተግባር ታግዘው መከታተላቸውን ተወካዩ አስታውቀዋል። የተሠጠው ሥልጠና የነበሩ ክፍተቶችን ከመሙላቱ ባሻገር የባለሙያዎችን ክህሎትና በራስ መተማመን ማሳደጉን ተወካዩ ተናግረዋል፡፡ እንደ ተወካዩ ገለፃ ቀደም ሲል የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ በግንባታ ተቋራጩ ሲመንስ ኩባንያ በመታገዝ ሲካሄድ ነበር። በተሰጡት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች አሁን ላይ ከአንዳንድ የኦፕሬሽን ሥራዎች ውጪ በጣቢያው ባለሙያዎች እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በራስ አቅም የሚሰሩትን የኦፕሬሽን ሥራዎች በመለየት ከ80 በመቶ በላይ የኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎችን በጣቢያው ባለሙያዎች ማከናወን በመቻሉ ቀደም ሲል የኦፕሬሽን ሥራውን ሙሉ በሙሉ በውጪ ለማሰራት የነበረውን ሀሳብ ማስቀረት ተችሏል ነው ያሉት፡፡ ከሶፍትዌር ጋር የተያያዙ ውስብስብና ተጨማሪ ሥልጠና የሚፈልጉ ሥራዎች ለጊዜው በውጪ እንዲሰሩ ድጋፍ መጠየቁን ያነሱት ተወካዩ ይህም ወደ ፊት ሥራዎችን በራስ አቅም በማከናወን የዕውቀት ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ገልፀዋል፡፡ የኦፕሬሽን ሥራውን አስተማማኝ ለማድረግ ከሚሰጡት ሥልጣናዎች በተጨማሪ የጣቢያው ሠራተኞች እርስ በእርስ በመማማር ክፍተቶችን እየሞሉ መሆናቸውን ተወካዩ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ ..........///......... በ12ኛ ሳምንት የከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ስልጤ ወራቤ ከተማን አምስት ለባዶ በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ልዩ ሆኖ በዋለበት በዚህ ጨዋታ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቾች አቤል ሀብታሙ እና ያሬድ ብርሃኑ ሁለት ሁለት ጎል ያስቆጠሩ ሲሆን ቀሪዋን አንድ ጎል ደግሞ አንዋር ሙራድ ማስቆጠር ችሏል። በዛሬው ጨዋታ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ከፍፁም የጨዋታ የበላይነት ጋር የተጋጣሚውን የጎል በር በተደጋጋሚ መፈተሽ ችሏል። ስልጤ ወራቤ በበኩሉ አልፎ አልፎ ወደ ተጋጣሚው የግብ ክልል ከመድረሱ ባሻገር ሙሉ በሙሉ በመከላከል ላይ የተመሰረተ አጨዋወት ተግባራዊ ሲያደርግ ተስተውሏል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ እንዳለ ዘውገ የጨዋታው ኮከብ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በ28 ነጥብ እና በ13 ንፁህ ጎል ተከታዩን አዲስ አበባ ከተማ በአምስት ነጥብ በመብለጥ በሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአንደኛውን ዙር የመጨረሻ ጨዋታ ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር በመጪው ሐሙስ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content
+9

የማሰልጠኛ ማዕከሉን ስምና ዝና ቀድሞ ወደ ነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማሰልጠኛ ማዕከልን አቅም ለማሳደግና ወደ ቀደሞ ዝናው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ። የቀድሞ የኢትዮጵያ መብራትና ኃይል ባለስልጣን የስልጠና ኢንስቲትዩት የአሁኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስልጠና ማዕከል የ1975 ዓ.ም ተመራቂዎች የተመረቁትን 40ኛ ዓመት ትናንት በተለያዩ ፕሮግራሞች አክብረዋል። ፕሮግራሙ የወቅቱ ተመራቂዎች ለተቋሙ ያላቸውን ፍቅር፣ አብሮ ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ለማሳየት እንዲሁም ተቋሙ ዕለቱን ተቋማዊ በዓል እንዲያደርገው ለማሳሰብ ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚን ተወካይና የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ እንደተናገሩት የ1975 የኢንስቲትዩቱ ተመራቂዎች የሙያ ልደታቸውን ዓመት ማክበራቸው ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ተመራቂዎቹ ለተቋሙ ላደረጉት አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ላሳዩት ተምሳሌትም ጭምር ተቋሙ ያመሰግናቸዋል ብለዋል። ኢንስቲትዪቱ በየጊዜው አቅሙን በማሳደግ ብቃት ያላቸው ሠራተኞችን ለተቋሙ ሲያበረክት እንደነበር ያስታወሱት አቶ ውድነህ 1970ዎቹ ለተቋሙ "ወርቃማው ጊዜ" የሚባልበት እንደነበርም ገልፀዋል። ኢንስቲትዩቱ ለኃይል ልማት ዘርፍ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን እያፈራ የነበረ ቢሆንም በ1987 ዓ.ም የተቋሙ ከፊል ግቢ ለኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በጊዜያዊነት በመሰጠቱ ኢንስቲትዩቱ በቀድሞ ስምና ዝናው እንዳይቀጥል ፈተና ሆኖበት መቆየቱን አቶ ውድነህ አስታውሰዋል። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በኃይል ዘርፍ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን የሚያፈራ የልህቀት ማዕከል ለመገንባትና የቀድሞ ስሙን ለመመለስ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የነደፈውን ራዕይ ለማሳካት የቀረፀውን ስትራቴጅክ ዕቅድ ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክትም ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት   መሠረታዊ የሠራተኞች ማህበራት ሊቃነ መናብርት አቶ መኮንን ክፍሌ እና አቶ ኃይሉ ዘውዴ በበኩላቸው ሠራተኞቹ በጡረታና በሌሎች ምክንያቶች ከተቋማቶቹ ቢወጡም ከተቋሙ ያገኙትን ዕውቀት አስታውሰው ፕሮግራሙን ማዘጋጀታቸው ሃሳባቸው ሁሉ ከተቋማቶቹ ጋር እንደሆነ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ፕሮግራሙ ለሌሎች ተሞክሮ እንዲሆን እና በሌሎች ጉዳዮችም ከተቋማቶቹ ጋር አብሮ ለመስራት የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል። ከ1975 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች መካከል አቶ እስራኤል አድማሱ እና አቶ ተሠራ መርከቡ በሰጡት አስተያየት ከኢንስቲትዩቱ ያገኙት የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ዕውቀት አሁን ለደረሱበት መሠረት እንደሆነም አስታውቀዋል። 1975 ዓ. ም. ለተቋሙ ከፍተኛ መነቃቃት የተፈጠረበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰው ተመራቂዎቹ በተመደቡበት የሥራ ቦታ ሁሉ  ውጤታማ ሥራ በማከናወን ተቋሙ ዛሬ ለደረሰበት ጀረጃ የበኩላቸውን እንዳበረከቱ እንደሚያምኑ ተናግረዋል። ማሰልጠኛውን ወደነበረበት ስምና ዝና ለመመለስ በሚሰራው ሥራ ላይ የ1975 ተመራቂዎች ከተቋሙ ጋር ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑ አረጋግጠዋል። ለዚህም ከሁለቱ ተቋማት ጋር በትብብር ሊሰራ የሚችል ሃያ አንድ 1975 ኤሌክትሮ ሜካኒካል ኃ/የተ/የግል ማህበር የሚል አክሲዮን ማቋቋማቸውን ነው የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ተሠራ ያስታወቁት። በእንግሊዝ ሀገር ለንደን እየኖሩ ያሉትና በፕሮግራሙ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አቶ አለማየሁ ተሾመ በበኩላቸው ከ40 ዓመት በፊት አብረዋቸው ከተማሩ ጓደኞቻቸው ጋር በመገናኘታቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል። በዕለቱም የኢንስቲትዩቱ የ1978 እና የ1980 ዓ.ም ተመራቂዎች ተወካዮች መልዕክት አስተላልፈዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ለኬኒያ በስምምነቱ መሰረት ኃይል እየቀረበ ነው ..........///.......... ለኬኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በተደረገው ስምምነት መሰረት ኃይል እየቀረበ መሆኑን በወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ የኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በጣቢያው የጥገናና የኦፕሬሽን ባለሙያ መኮንን ካሴ እንደተናገሩት ለኬኒያ በስምምነቱ መሰረት ኃይል ለማስተላለፍ የኮንቨርተር ጣቢያውና የማስተላለፊያ መስመሩ ሲስተም በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ሁለቱ ሀገራት ባደረጉት ስምምነት መሰረት ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ባለበት ሰዓት 200 ሜጋ ዋት ኃይል በአስተማማኝ ሁኔታ እየቀረበ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የኃይል ሽያጭ ስምምነቱ ጭነት በሚበዛበትና በሚቀንስበት ሰዓት የተለያየ ቢሆንም ከ65 እስከ 200 ሜጋ ዋት ድረስ እንደስምምነቱ ኃይል እየቀረበ እንደሆነ ባለሙያው ተናግረዋል። ለኬኒያ በስምምነቱ መሰረት ኃይል ለማቅረብ በኢትዮጵያ ግሪድ ሲስተም ላይ እያጋጠመ ያለ ችግርም ሆነ ስጋት እንደሌለ ነው የተናገሩት፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ 2 ሺህ ሜጋ ዋት የማስተላለፍ አቅም እንዳለው እና በአሁኑ ወቅትም በሲስተሙ ላይ የኃይል እጥረት እንደሌለ አንስተዋል፡፡ ሲስተሙ በቀጣይ ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ ሲጀመር ሊመጣ የሚችለውን ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት የመሸከም አቅም እንዳለው ባለሙያው ጠቁመዋል። እንደ አቶ መኮንን ገለጻ መስመሩ በአስተማማኝ መልኩ ኃይል እንዲያስተላልፍ የጥገና ሥራው ከሪጅኖች ጋር በመቀናጀት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በሶዶ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ቴክኒሺያን የሆኑትና በኮንቨርተር ጣቢያው በማገልገል ላይ የሚገኙት አቶ እሸቱ ኦርጉዶ በበኩላቸው ኮንቨርተር ጣቢያው ከወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር ሲነፃፀር በኪሎ ቮልት መጠኑና በተገጠመለት ቴክኖሎጂ የሚለያይ በመሆኑ ለቴክኖሎጂ እና ዕውቀት ሽግግር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል። በጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ ላይ በመሳተፋቸው የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተጠቃሚ መሆናቸውን በመጥቀስ የጣቢያው ዘመናዊ መሳሪያዎች ሥራን በተቀላጠፈ መልኩ ለማከናውን የሚያግዙ ስለመሆናቸው አመልክተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

ባለፉት 6 ወራት አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ ከ66 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል .........///........... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2016 የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችን በማስገድ 66 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን በተቋሙ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንዳስታወቁት ገቢው አገልግሎት የማይሰጡ ተሸከርካሪዎችን፣ ቁርጥራጭ ብረቶችን፣ አሉሙኒየምና መዳቦችን በማስወገድ የተገኘ ነው፡፡ ተቋሙ በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት 60 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዶ 66 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ ከዕቅዱ የ10 ነጥብ 3 በመቶ ብልጫ አፈፃፀም እንዳስመዘገበ ሥራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል። የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ14 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ እንዲወገዱ ከተለዩ ከ200 በላይ የተቋሙ ተሸከርካሪዎች መካከል በ3 ዓመት ውስጥ 150 የሚሆኑት መወገዳቸውን ወ/ሮ ስመኝ አስታውቀዋል፡፡ ተቋሙ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ የሚያገኘው ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የገለፁት ወ/ሮ ስመኝ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 150 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ ከሜቴክ እና ከመልካ ሰዲ ፕሮጀክት የተረከባቸውን ንብረቶች ጨምሮ ሲወገዱ በቢሊዮን የሚቆጠር ገቢ ሊያስገኙ የሚችሉ ንብረቶች እንዳሉት ሥራ አስፈፃሚዋ ጠቅሰዋል፡፡ ይሁን እንጂ ንብረቶችን አስወግዶ የታሰበውን ገቢ ለማግኘት ከንብረት ርክክብ፣ ከጨረታና ከባለቤትነት ጋር ማረጋገጫ ሰነድ ጋር የተያያዙ ችግሮች በሥራው ላይ ጫና እያሳደሩ መሆኑን ወ/ሮ ስመኝ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚዋ ገለፃ የተሸከርካሪዎችን ሰነድ በማጣራትና የባለቤትነት ማረጋገጫ በማውጣት ንብረቶችን ለማስወገድ እየተሰራ ሲሆን ወደ ፊት መሰል ችግሮች እንዳያጋጥሙ ከተሸከርካሪ ግዥና ርክክብ ጋር የተገናኙ ሰነዶችን የማረጋገጥ ሥራ በጥንቃቄ እንደሚከናውን አረጋግጠዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 02 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5