en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 548 subscribers, ranking 8 340 in the Technologies & Applications category and 2 158 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 548 subscribers.

According to the latest data from 26 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 27 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.05%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.01% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 053 views. Within the first day, a publication typically gains 2 491 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 27 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 548
Subscribers
-724 hours
+147 days
+2730 days
Posts Archive
photo content
+1

photo content
+2

photo content
+9

የመሻገር ቀን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ነው ......///........ የመሻገር ጥሪቶች፣ የአዲስ ብርሃን ወረቶች" በሚል መሪ ሃሳብ ጳጉሜን 1 የመሻገር ቀን በሚል ስያሜ በሳይንስ ሙዚየም
የመሻገር ቀን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ነው ......///........ የመሻገር ጥሪቶች፣ የአዲስ ብርሃን ወረቶች" በሚል መሪ ሃሳብ ጳጉሜን 1 የመሻገር ቀን በሚል ስያሜ በሳይንስ ሙዚየም እየተከበረ ይገኛል፡፡ ቀኑ ኢትዮጵያን ለማሻገር በተደረጉ ጥረቶች፣ የተገኙ ስኬቶችንና በሂደቱ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች የሚታሰቡበት ነው፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታን ጨምሮ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ እና በቱሪዝም ዘርፎች ላይ የተመዘገቡት ድሎች ለመሻገር ቀን  ማሳያዎች ሆነው ተመርጠዋል፡፡ በዕለቱ ሀገሪቱን ለማሻገር  አስተዋፅዖ ላበረከቱ እና ለመሻገር ቀን ምልክት ለሆኑ ተቋማት እውቅናና ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚደንት አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም

ዛሬ በመላዉ ሀገሪቱ "የመሻገር ቀን" በተለያዩ ሁነቶች ተከብሮ ይዉላል። ዕለቱም "የመሻገር ጥሪቶች፣ የአዲስ ብርሃን ወረቶች" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ
ዛሬ በመላዉ ሀገሪቱ "የመሻገር  ቀን" በተለያዩ ሁነቶች ተከብሮ ይዉላል። ዕለቱም "የመሻገር ጥሪቶች፣ የአዲስ ብርሃን ወረቶች" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም

ለዘመን መለወጫ በዓል የኃይል አቅርቦት ቅድመ ዝግጅት ተጀምሯል …….///……. በአዲስ አበባ ከተማ በበአል ወቅት በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ሊከሰት የሚችልን ከፍተኛ የኃይል ጭነት ለመቆጣጠር ቅድመ ዝግጅት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የማዕከላዊ 3 ሪጅን እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምዕራብ፣ ደቡብ እና ሰሜን አዲስ አበባ ዲስትሪክቶች የጋራ ስብሰባ በሪጅኑ ቢሮ አካሂደዋል፡፡ በስብሰባው ላይ እንደተነሳው በዲስትሪክቶቹ በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚታየው የአቅም ውስንነት ዘላቂ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል፡፡ የኃይል ጭነት ከሚበዛባቸው መስመሮች መካከል የተወሰኑትን ወደ ሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማዘዋወር ሥራ ትኩረት እንዲሰጠውም መክረዋል፡፡ በአንፎ - ጦር ኃይሎች፣ በኮልፌ - አዲስ ዌስት፣ በጎፋ፣ እና በካራቆሬ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ያለውን የኃይል ጭነት መቅረፍ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል፡፡ በቀረበው ምክረ ሀሳብ መሰረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኮልፌ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ጥቁር አንበሳ ማከፋፈያ ጣቢያና ወደ ሸጎሌ ማከፋፈያ ጣቢያ፣ ከአንፎ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ኮልፌ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም ከቃሊቲ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ኮዬ አቦ የተወሰኑ መስመሮችን የማዘዋወር ሥራ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደግሞ ከሰበታ 1 ወደ ረጲ በተዘረጋው 132 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ ያለውን የኮንዳክተር መርገብ በፍጥነት እንዲስተካከል እንዲሁም በጥቁር አንበሳ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚታየው የሴቲንግ ችግር እንዲያስተካክል ሀሳብ ቀርቧል፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ ባስተላለፉት መልዕክት የኃይል አቅርቦት ችግሩን የሚፈቱ ተመሳሳይ ውይይቶች በየወሩ እንደሚከናወኑ ገልፀው ለዘመን መለወጫ በዓል የተሰጡ ሥራዎች አፈፃፀም ሪፖርት እንደሚቀርብ አረጋግጠዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር የሚያስችል የብሬከር ቅያሪ ተከናውኗል .......///...... በሆሳዕና ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያን የመቆጣጠሪያ ክፍል የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራ መከናወኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊዋ ወ/ሮ ማህደር ገብረ መስቀል እንደገለጹት በ1978 ዓ.ም የተገነባው የሆሳዕና ማከፋፍያ ጣቢያ በአንድ ትራንስፎርመር በ132 ኪሎ ቮልት አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ከጊዜ በኋላ በተደረገለት ማሻሻያ በሦስት ትራንስፎርመር ወደ 230 ኪሎ ቮልት አድጓል። ሆኖም በብሬከሩ ምክንያት የሚያጋጥመውን የኃይል መቆራረጥን ለማስወገድና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን የሚያስችል የብሬከር ቅየራ ሥራ ተከናውኗል። ቀደም ሲል የነበረውን የ33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ብሬከር በጋዝ በሚሰራ ጂ.አይ.ኤስ (Gas Insulated System) መቆጣጠሪያ በመቀየሩ የጣቢያውን የቁጥጥር ሥራ ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ለማከናወን ማስቻሉን ኃላፊዋ ተናግረዋል። የጂ.አይ. ኤስ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራው በአንድ ላይ ይወጡ የነበሩ ሁለት ወጪ መስመሮች በተናጠል እንዲወጡ ከማድረጉም ባሻገር የ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን ቁጥር ከአራት ወደ ስድስት ከፍ ማድረጉን አብራርተዋል። ሁለቱ መስመሮች በአንድ ላይ ወጪ በሚሆኑበት ጊዜ ችግሮች ሲያጋጥሙ ጥገና ለማካሄድ የኃይል መቆራረጥን ያስከትል እንደነበረ አስታውሰዋል። የተከናወነው የብሬከር ቅየራ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር የሚያግዝ በመሆኑ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናቸውን ወ/ሮ ማህደር ተናግረዋል። በጣቢያው የኦፕሬሽን ቴክኒሽያን የሆኑት አቶ ብርሀኑ ፀጋዬ በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው ብሬከር ችግሮች ሲያጋጥሙ የጥገና ሥራ ለማከናወን ረዘም ያለ ጊዜ ይወስድ እንደነበር አስታውሰዋል። የመቆጣጠሪያው መቀየር የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚረዳም ነው ባለሙያው የተናገሩት። የሆሳዕና ማከፋፍያ ጣቢያው በሦሥት ትራንስፎርመሮች 175 ሜጋ ቮልት አምፒዬር የመጫን አቅም አለው። ማከፋፍያ ጣቢያው 132 ኪሎ ቮልት ከጊቤ አንድ እንዲሁም ከወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ 230 ኪሎ ቮልት የሚቀበል ሲሆን ባለ 15 ኪሎ ቮልት 7 እና ባለ 33 ኪሎ ቮልት 3 ወጭ መስመሮች አሉት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ለፕሮጀክቶች አፈፃፀም ፈተና የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት ሁሉም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ ………///……. የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ግንባታ በተያዘላቸው መርሀ ግብር መሰረት ለማከናወን የታወር አካላት ስርቆት፣ የወሰን ማስከበር እና የፀጥታ ችግሮች ፈተና እንደሆኑበት የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የአፈፃፀም ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ታረቀኝ እንዳስታወቁት በ2016 በጀት ዓመት ስድስት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ታቅዶ ሁለቱን ብቻ ማጠናቀቅ ተችሏል፡፡ በበጀት ዓመቱ የቡታጅራ - ወራቤ፣ ባህርዳር - ወልዲያ፣ ደጀን - ደብረ ማርቆስ፣ አዘዞ - ጭልጋ፣ የአዋሽ - ወልዲያ የባቡር ኃይል አቅርቦት ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም የኮተቤ ጊቢ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ታቅዶ ሲሰራ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይሁን እንጂ ከቡታጅራ- ወራቤ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም ከኮተቤ ግቢ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክቶች ውጪ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ እንዳልተቻለ አቶ አክሊሉ አስታውቀዋል፡፡ በዕቅዳቸው መሰረት ያልተጠናቀቁ አራቱ ፕሮጀክቶች ከ80 ነጥብ 7 እስከ 96 ነጥብ 4 በመቶ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ መድረሳቸውንም አስረድተዋል፡፡ እንደ አቶ አክሊሉ ገለጻ የወሰን ማስከበር፣ የታወር አካላት ስርቆት እና የጸጥታ ችግሮች ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት እንዳይጠናቀቁ ምክንያት ሆነዋል፡፡ የወሰን ማስከበር ችግሮችና የታወር አካላት ስርቆት ባለፈው በጀት ዓመት ይጠናቀቃሉ ተብለው ከነበሩ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በግንባታ ላይ በሚገኙ ሌሎች ፕሮጀክቶች ላይም ይስተዋላል። ለፕሮጀክቶቹ አፈፃፀም ፈተና የሆኑ ችግሮቹን ለመፍታት በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳደር አካላት፣ የጸጥታ ኃይሎች እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ቢካሄዱም ባለድርሻ አካላታ መግባባት ላይ በተደረሰው መሰረት በቁርጠኝነት ወደ ተግባር ባለመግባታቸው ውጤት ሊመጣ አለመቻሉን ነው የገለጹት፡፡ የውጭ ምንዛሪ እጥረት፣ የሥራ ተቋራጮች አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን፣ ከውጭ የሚገቡ የፕሮጀክት ዕቃዎች የባህር ላይ ጉዞ መዘግየት እና የግንባታ ግብዓቶች እጥረት ተቋሙ በዕቅድ የያዛቸውን ሥራዎች በአግባቡ እንዳያከናውን ተፅዕኖ እያሳደሩ ካሉ ተጨማሪ ችግሮች መካከል እንደሚጠቀሱም አቶ አክሊሉ አመልክተዋል፡፡ በፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ላይ እያጋጠሙ ያሉ የተለያዩ ችግሮች ለፕሮጀክቶች አፈፃፀም ፈተና ከመሆናቸውም ባለፈ በተለያዩ ምክንያቶች ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪዎች እየዳረጉት እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለሀገር የሚኖራቸውን ፋይዳ በመረዳት ለመሠረተ ልማቱ ጥበቃ ከማድረግ ጀምሮ ለአፈፃፀም ፈተና የሆኑ ችግሮች እንዲፈቱ ሁሉም የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን ስርቆት ለመከላከል አስተዳደሩ እየሰራ ነው ………..///………… የወራቤ ከተማ አስተዳደር በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚፈጸምን ስርቆት ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ። የከተማ አስተዳደሩ የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አክመል ጀማል እንደገለጹት በኢነርጅ አዋጅ 810/2006 እና በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ደህንነት ለመጠበቅ በወጣው አዋጅ 464/97 መሠረት የከተማ አስተዳደሮች የመሰረተ ልማት ስርቆትን የመከላከል ኃላፊነት አለባቸው። ይህን መሠረት በማድረግም በወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያና በከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ታወሮች ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን በመከላከል በኩል የጸጥታ አካላት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛል ብለዋል። የመሠረተ ልማት ስርቆቱን ለመከላከል ከሚደረገው ጥረት ባሻገር ስርቆቱ ተፈጽሞ ሲገኝ በአዋጁ መሠረት በአጥፊዎች ላይ አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ተናግረዋል። በዚህም በልዩ ሁኔታ ከ15 ቀን ባነሰ ጊዜ ውስጥ በተጠርጣሪዎች ላይ ክስ በመመስረት ለፍርድ እንዲቀርቡ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት የታክቲክ ምርመራ አስተባባሪ ረዳት ኢንስፔክተር ራህመቶ ሙስጠፋ በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያው ሲገነባም ሆነ ከተገነባ በኋላ ስርቆት እንዳይፈጸም ፓሊስ ከሕብረተሰቡ ጋር እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በአካባቢው ማህበረሰብ የአውጫጭኝ ሥርዓት መሰረት ስርቆት ሲፈጸም አጥፊዎች ላይ ክትትል በማድረግ እርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል፡፡ በዚህም የታወር ብረቶች ላይ ስርቆት የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ከአምስት ዓመት እስከ ስድስት ዓመት በሚደርስ እስራት መቀጣታቸውንና የሰረቁትን ብረትም ለጣቢያው መመለሱን ተናግረዋል። ረዳት ኢንስፔክተር ራህመቶ አክለውም በአሁኑ ወቅትም ከማከፋፊያ ጣቢያው ኬብል ገመድ የሰረቀ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑንም ተናግረዋል። በኮሚኒቲ ፖሊሲንግ አማካኝነት ሕብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ ኖሮት ችግሩን በኃላፊነት እንዲከላከል እየሰራን ነው የሚሉት ረዳት ኢንስፔክተር ራህመቶ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸም ስርቆት በሕብረተሰቡ ላይ የሚያደርሰውን ከፍተኛ ጉዳት ከግምት በማስገባት ከሌሎች መዝገቦች ቅድሚያ በመስጠት አጥፊዎችን ለሕግ የማቅረብ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። አስተዳደሩ በሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ አሁን ላይ ማህበረሰቡ ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ጥበቃ የሚሰጠው ትኩረት በማደጉ አሁን ላይ ችግሩ እየቀነሰ መምጣቱንም ገልጸዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት የአካባቢውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ጨምሯል ..........///…....... የቡኢ ማከፋፈያ ጣቢያ የከተማዋንና የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እያፋጠነ መሆኑን የቡኢ ከተማ አስተዳደር ገለጸ። የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ እንደገለጹት የቡኢ ማከፋፈያ ጣቢያ ከመገንባቱ በፊት ከተማዋ የመብራት አቅርቦት ከቡታጅራ ማከፋፊያ ጣቢያ ስታገኝ የነበረ በመሆኑ በከተማዋና አካባቢው የሚመጡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ እንቅፋት ፈጥሮ ቆይቷል። የቡኢ ባለ 132 ማከፋፈያ ጣቢያ ከተገነባ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ግን የአካባቢው የኢንቨስትመንት ፍሰት እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በዚህም ከፍተኛ ኃይል የሚጠይቁ ከ40 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ፍቃድ ወስደው ስድስቱ ወደ ማምረት ሲገቡ ቀሪዎቹ ደግሞ በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አሁን በከተማውና አካባቢው ያለውን አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ከግምት ውስጥ በማስገባት በርካታ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑንም አቶ በለጠ አብራርተዋል። የአካባቢውን የመልማት አቅምና ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በማድረጉም አመስግነዋል። የቡኢ ማከፋፈያ ጣቢያው የኦፕሬሽን ባለሙያ አቶ አይሸሹም አበረ በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 4 ከተሞችና 3 ወረዳዎች እንዲሁም አጎራባች የኦሮሚያ ክልል ወረዳዎችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረጉን ገልጸዋል። ጣቢያው 45 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ሲሆን አሁን በጥቅም ላይ የዋለው ግን ዘጠኝ ከመቶው ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም ቡኢ ከተማን ጨምሮ በአካባቢው በመገንባት ላይ ለሚገኙ ፋብሪካዎችም ሆነ በቀጣይ የሚመጡ ኢንቨስትመንቶች የሚፈልጉትን የኃይል ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ የሚያስችል አቅም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

በሚዛን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ኃይል ተቋርጧል ………////……… በሚዛን ባለ 132/66/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የ132 ኪሎ ቮልት ብሬከር ብልሽት ሳቢያ በአሁኑ ሰዓት ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ኤሌክትሪክ ሲያገኙ በነበሩ ዞኖች እና ከተሞች የኃይል አቅርቦት መቋረጡን ደቡብ ምዕራብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት በተፈጠረው የብሬከር ብልሽት ምክንያት ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ያገኝ የነበረው የቴፒ 66/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይም ኤሌክትሪከ ተቋርጧል። የኃይል መቋረጡን ለማስተካከል ጥረት የተጀመረ ሲሆን ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ኃይል የተቋረጠባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ሪጅኑ ጠይቋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በማከፋፈያ ጣቢያው የውሀና አፈር መከላከያ ግንብ ስራ እየተከናወነ ነው ---///--- በሸጎሌ ማከፋፈያ ጣቢያ የሠራተኞች የመኖርያ ቤት መግቢያ በር እና የውሀና አፈር መከላከያ ግንብ ስራ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የራስ ኃይል የሲቪል ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የፕሮጀክቱ ሳይት ማናጀር ወ/ሮ ፅጌ ጥላሁን እንደገለፁት የግንባታ ሥራው 25 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የክረምቱ ዝናብ መጠናከርና የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መናር ሥራውን በተያዘው ዕቅድ እንዳይጓዝ ሊያደርግ ቢችልም እስከ መስከረም 2017 ዓ.ም. መጨረሻ ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙን የሳይት ማናጀሯ አስረድተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6