en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 538 subscribers, ranking 8 326 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 538 subscribers.

According to the latest data from 04 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 26 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.64%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.41% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 139 views. Within the first day, a publication typically gains 2 395 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 538
Subscribers
-724 hours
-77 days
+2630 days
Posts Archive
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተቋሙ የተጣለበትን ተልዕኮ ለማሳካት ፋይዳዉ የጎላ መሆኑ ተገለፀ ……….///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ መሪዎችና ሠራተኞች በውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪነት በተካሄደው ሦስተኛዉ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች እንደተናገሩት መርሃ ግብሩ ተቋሙ ለሀገር እድገትና ለአህጉራዊ ትስስር መሰረት የሚሆን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት እየሰራ ያለውን ስራ ለማሳካት ፋይዳዉ የጎላ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ተቋሙ 90 በመቶ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ ኃል የሚያመነጨው ከውሃ በመሆኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ዝናብ እንዲጨምር በማድረግ ግድቦች የሚያስፈልጋቸውን ውሃ እንዲይዙ ለማድረግ ያግዛል፡፡ ይህም ተቋሙ ማመንጨት ያለበትን ኃይል በማመንጨት ለሀገር እድገትና ለአህጉራዊ ትስስር አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችለዋል ብለዋል፡፡ አቶ አሸብር እንዳሉት የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ እንዲሳተፉ ከማድረግ ባለፈ በቀጣይም የተተከሉትን ጭምር በመንከባከብ ስራ ላይ ትኩረት ይደረጋል፡፡ ተቋሙ የአረንጓዴ አሻራ ስራዉን በፋይናንስ በመደገፍ ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራው ግድቦች ለጎርፍ እንዳይጋለጡ፣ ለማድረግ እንዲሁም የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ እና ትዉልዱ ንፁህ አየር እንዲያገኝ ለማድረግ ፋይዳዉ የጎላ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ ደግሞ ሠራተኛው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ እንዲሳተፍ ለቀረበው ጥሪ ያሳየውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል፡፡ በመካሄድ ላይ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት አስተዋጽኦ ስለሚኖረው ችግኞችን ከመትከል አስቀድሞ ለቦታ መረጣና የሚተከሉ ችግኞች ለአካባቢው ተስማሚ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አታላይ ገለፃ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሳራ መርሃ ግብር ከዚህ በፊት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር የቅድመ ዝግጅት ስራው የተሻለ ነበር፡፡ የተቋሙ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ተወካይ አቶ መንግስቱ አባይነህ በበኩላቸው ከዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ በኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ እንዲሳተፉ ለማድረግ ከዘርፍ ማህበራት ጋር እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የስራ መሪዎችና ሠራተኞች በአረንጓዴ አሻራው ላይ መሳተፋቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀው በቀጣይ በሃገሪቱ በሚገናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ በቁርጠኝነት ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ችግኝ መትከል ብቻ ፋይዳ እንደሌለው የተናገሩት ተሳታፊዎቹ በቀጣይ በሚከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እና የተተከሉትን መንከባከብ ላይ ሁሉም በኃላፊነት መሳተፍ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጅማ አባጅፋርን አንድ ለባዶ አሸነፈ ………..////……… ወደ ፕሪሚየር ሊግ ለመግባት ከ6 ክለቦች ጋር እየተፎካከረ የሚገኘው የኢትዮ -ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ጅማ አባ ጅፋርን
+2
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጅማ አባጅፋርን አንድ ለባዶ አሸነፈ ………..////……… ወደ ፕሪሚየር ሊግ ለመግባት ከ6 ክለቦች ጋር እየተፎካከረ የሚገኘው የኢትዮ -ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ጅማ አባ ጅፋርን በሀዋሳ ከተማ አንድ ለባዶ በማሸነፍ የማለፍ ዕድሉን አለምልሟል። ውድድሩ የትግራይ ክለቦች በቀጣዩ ዓመት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የማይሳተፉ ከሆነ በምትካቸው በፕሪሚየር ሊጉ ለመሳተፍ የሚደረግ ነው፡፡ የክለቡ ዋና አሠልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ጅማ አባጅፋር ጠንካራ የመከላከል አቅም ያለው ቡድን ቢሆንም ኳስ ይዘን እና ወደፊት ተጭነን በመጫወታችን ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማግኘት ችለናል ብለዋል። የድሉን ብቸኛ ግብ አደም አባስ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። በቀጣይም ከኮልፌ እግር ኳስ ክለብ ጋር ወሳኝ ጨዋታ ያላቸው መሆኑን እና ይህንንም ጨዋታ በድል ለመወጣት በአካልም ሆነ በስነ ልቦና ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ምስል፡- ሶከር ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም

ኢትዮጵያን እናልብስ በሚል መሪ ቃል የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርን በይፋ ጀምረዋል ………..////………… የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማቱ የሦስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በፊንፊኔ ልዩ ዞን በረህ ወረዳ ሲሬ ጉዮ ቀበሌ ማህበር ለገዳዲ ግድብ አካባቢ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለው የአንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአፈር መሸርሸር ምክንያት ደለል ወደ ኃይል ማመንጫ ግድቦች እንዳይገባ በማድረግ ግድቦች ኃይል ለማመንጨት የሚያስፈልጋቸውን ውሃ በአግባቡ እንዲይዙ ያደርጋል፡፡ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሃገራችንን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም እና ስነ ምህዳርን ለመጠበቅ እንዲሁም የውሃ አጠቃቀምን በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም አብራርተዋል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሄዱ መርሃ ግብሮች ላይ ለአካባቢው ስነ- ምህዳር ተስማሚ የሆኑ ችግኞችን በመትከል በንቃት ሲሳተፉ እንደነበር አስታውሰው በዛሬው መርሃ ግብር በስምንት ሄክታር መሬት ላይ የተለያየ ዝርያ ያላቸው 10 ሺህ ሀገር በቀል ችግኞች መተከላቸውን ገልፀዋል፡፡ በቀጣይም በወንዝ ተፋሰሶች እና ሐይቆች አካባቢ ትኩረት በማድረግ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡ እንደሚኒስትሩ ገለፃ ችግኝ መትከል ብቻ ለውጥ ስለማያመጣ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ ለማድረግም ትኩረት ተሰጥቶት ይሰራል፡፡ ሁሉም ስነ -ምህዳርን መንከባከብ አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝቦ እንደ ሃገር የታሰበውን ለማሳካት በቀጣይ የአረንጓዴ አሻራ ስራን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። በኦሮሚያ ክልል የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ፍቃዱ ቱሉ በበኩላቸው በዛሬው ዕለት የተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአዲስ አበባ ከተማ የተጣራ ውሃ በማቅረብ ላይ የሚገኘውን የለገዳዲ ግድብን ከደለል ለመከላከል ያግዛል ብለዋል። አካባቢው ለአዲስ አበባ ቅርብ በመሆኑ ከተማዋን ከአየር ንብረት መዛባት ለመጠበቅ እንደሚያስችልም ጠቁመዋል። የውሃ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የጀመሩትን መልካም ተሞክሮ ሌሎች የፌዴራልና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት በአካባቢው ላይ በመምጣት እንዲያስቀጥሉና የአረንጓዴ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል። ለዚህም ልዩ ዞኑና ወረዳ አስተዳደሩ መሬት ከማዘጋጀት ጀምሮ ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው መርሃ ግብሩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከደለል ለመከላከልና ጣቢያዎቹ በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። በማመንጫ ጣቢያዎች አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ የአረንጓዴ አሻራ ስራውን ለማከናወን እቅድ መያዙንም ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ አነሳሸነት በተጀመረው በዚህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአራት ዓመት ውስጥ 20 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ ተይዞ እየተሰራ ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታትም ለመትከል ከታቀደው በላይ ችግኞችን መትከል ተችሏል፡፡ "ኑ ኢትዮጵያን እናልብሳት" በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይም በሃገር አቀፍ ጀረጃ 6 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ ተይዞ በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ በሃገር ውስጥ ከምታከናውነው የአረንጓዴ አሻራ ስራ በተጨማሪ በተያዘው ክረምት ለጎረቤት ሃገራት አንድ ቢሊዮን ችግኞችን በማቅረብ የአረንጓዴ አሻራን ወደ ቀጠናው ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶት በመሰራት ላይ ይገኛል። በውሃ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስቴር ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና በቪተን ኢቪደንስ ኢንተርናሽናል ማህበር አስተባባሪነት በተዘጋጀው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብ ላይ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ፣ የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ ፍቃዱ ቱሉን ፧ ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+7

photo content

ኢትዮጵያን እናልብስ መርሃ ግብር በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ ሠራተኞች በይፋ ተጀምሯል ……….////……….. የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የአስሩ ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች
+3
ኢትዮጵያን እናልብስ መርሃ ግብር በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ ሠራተኞች በይፋ ተጀምሯል ……….////……….. የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የአስሩ ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች በኢትዮጵያን እናልብስ መርሃ ግብር 10 ሺህ ችግኞችን ተክለዋል። የችግኝ ተከላ መርሃግብሩ ዛሬ ማለዳ በፊንፊኔ ልዩ ዞን በረህ ወረዳ ሲሬ ጉዮ ቀበሌ ገበሬ ማህበር በለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ግድብ አካባቢ ተካሂዷል፡፡ "ኢትዮጵያን እናልብስ" በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው 3ኛው ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ላይ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለን ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማቱ የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። ችግኙ የተተከለበት አካባቢ ለአዲስ አበባ የውሃ አቅርቦት ከሚሰጡ የውሃ መገኛዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ መርሃግብሩን ያስተባበሩት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድርና የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋራ በመሆን ነው፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአራት ዓመት 20 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምጦ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የራሱን አሻራ እያሳረፈ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

ለዳያስፖራው ማህበረሰብ ምቹ የድጋፍ ማድረጊያ ዌብሳይትና የሞባይል መተግበሪያ እየተዘጋጀ ነው ………..///………. ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የገንዘብ ማሰባሰቢያ የሚያገለግል ዌብሳይትን መሠረት ያደረገ የገንዘብ ማስተላለፊያ ሶፍትዌርና የሞባይል መተግበሪያ ተሰርቶ በሥራ ላይ ሊውል መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ መንግሥቱ አስታወቁ፡፡ ዌብሳይትን መሠረት ያደረገ የገንዘብ ማስተላለፊያ ሶፍትዌሩ እየበለፀገ ያለው ቻፓ ሶሊዩሽን ኮርፖሬሽን በተባለ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ተቋም ሲሆን የሞባይል መተግበሪው ደግሞ በለንደን በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጎ ፍቃደኞች የበለፀገ ነው፡፡ ቻፓ ሶሊዩሽን ኮርፖሬሽን ከአንድ ሃገር ወደ ሌላ ሃገር በሚደረጉ የገንዘብ ዝውውሮች ውስጥ ገንዘብ ነክ የይለፍ ሥርዓቶችን ለማመቻቸት እንደተቋቋመ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ በውጭ ሃገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከቦንድ ግዢ ባሻገር ግድቡን በገንዘብ መርዳት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ እስካሁን በስጦታ መልክ ገንዘብ ለመርዳት የሚያስችሉ ቀላል መንገዶች እንዳልነበሩ አለመኖራቸውን ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ ግን ዲያስፖራው ቆንስላ ጽ/ቤት ድረስ መጓዝ ሳይጠበቅበት ጊዜ እና ገንዘቡን ቆጥቦ በተዘጋጀው ሲስተም ኢንተርኔትን በመጠቀም ብቻ መገልገል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ለህዳሴ ግድብ ገንዘብ ማሰባሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተሰራ ሲስተም በመሆኑ ግድቡ የኔ ነው የሚል ሁሉም ኢትዮጵያዊ የገንዘብ ማስተላለፊያ ሲስተሙን በመጠቀም ግድቡን እንዲደግፍ ያስችለዋል ብለዋል፡፡ የበለፀገው ዌብሳይትና የሞባይል መተግበሪያ የግድቡን ግንባታ በስጦታ መልክ በገንዘብ ለማገዝ ከመርዳቱም ባሻገር የውጭ ምንዛሬ አቅምን ለማጎልበት ከማስቻሉም በተጨማሪ ህዝቡ ከግድቡ ጎን መሰለፉን ማረጋገጫ መንገድም እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ ዌብሳይትን መሰረት ያደረገው ይህ ሶፍትዌር ከገንዘብ ማስተላለፊያ መንገድነቱ ባሻገር ኢትዮጵያውያን ግድቡ የደረሰበትን ደረጃ እንዲከታተሉ ጭምር መረጃዎችን ለማግኘት ይረዳቸዋልም ሲሉ አቶ አለማየሁ ገልፀዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን በጎ ፈቃደኞች የተዘጋጀው ይህ የገንዘብ ማስተላለፊያ ሲስተም ለግድቡ ግንባታ መፋጠን ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም

የሻምቡ የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት የፍተሻና ሙከራ ሥራ በመከናወን ላይ ነው ……….///……… የሻምቡ ባለ 230 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት አብዛኛዎቹ የሲቪልና ኤሌክትሮ-ሜካኒካል ሥራዎች ተጠናቀው የፍተሻና ሙከራ ሥራ መጀመሩን የፕሮጀክቱ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን ተናግረዋል፡፡ ተወካዩ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ አማካይ አፈፃፀም 92 በመቶ የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ ሥራውን በቀጣዩ ወር በማጠናቀቅ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ እያንዳንዳቸው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፈርመሮች፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል እና ከኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያ ስርዓት ጋር የሚገናኘው የባስባር ገጠማ ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም ነው ተወካይ ኃላፊው የገለፁት፡፡ በተጨማሪም ከፊንጫ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ሻምቡ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ ለመዘርጋት ከታቀዱት 83 የኃይል ተሸካሚ ማማዎች መካከል የ53 ማማዎች ተከላ እና የኤሌክትሪክ ገመድ ዝርጋታ መከናወኑን አቶ አሸናፊ አስታውቀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት መሐንዲስ አቶ ሚኒልክ ሠለሞን በበኩላቸው ሻምቡ ከተማ ዳርቻ በዘጠኝ ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ የሚገኘው የሻምቡ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር አንድ ባለ 230 ኮሎ ቮልት ገቢ እና ስድስት 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ይኖሩታል ብለዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ግንባታ አራት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ሶስት ሚሊዮን ብር የተበጀተለት ሲሆን ከዚህም ውስጥ 85 በመቶው ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር እንዲሁም 15 በመቶው ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ በዋና ተቋራጭነት፤ ሀገር በቀሉ መላ ኢንጂነሪንግ ደግሞ የሲቪል ሥራውን በንዑስ ተቋራጭነት በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የጣሊያኑ ኢ.ኤል.ሲ ኤሌክትሮ ኮንሰልታንት ደግሞ የማማከር ሥራውን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አቶ ሚኒልክ አስታውቀዋል፡፡ ከአዲስ አበባ በ335 ኪ.ሜ ርቀት በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፤ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፤ በሻንቡ ከተማ የተገነባው የማከፋፈያ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለአካባቢው ማህበረሠብ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ለ140 ያህል የአካባቢው ነዋሪዎችም ጊዜያዊ የስራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 19 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+5

ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ነገ ክፍት ይሆናሉ ......./////....... ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ነገ ክፍት ሆነው እንደሚውሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ገለጹ። ለ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ሰኞ በሚዘጉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ምትክ ቅዳሜ የሥራ ቀን እንደሚሆን መንግስት አስታውቆ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ነገ ክፍት ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አሳስበዋል። ሰኔ 18 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+3

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ክለብ የነሃስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ ………///………. የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ክለብ በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን አዘጋጅነት በተካሔደው ሻምፒዮና ሶስተኛ በመውጣት የነሃስ ሚዳሊያ እና የሰባት ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል፡፡ በሁለት ምድብ ተከፍሎ በተካሔደው የማጣሪያ ውድድር ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ወደ መጨረሻው የዋንጫ ፉክክር የገባው የኤሌክትሪክ ክለብ ከስድስት ክለቦች ጋር እጅግ ፈታኝ ፉክክር በማድረግ ከአምስት ጨዋታዎች ስምንት ነጥብ ሰብስቦ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል፡፡ በዚህ ውድድር ተጋባዥ የሆነው የአዳማ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ክለብ የዋንጫ ባለቤት ሲሆን የመድን እግር ኳስ ክለብ ደግሞ የብር ሜዳሊያ አግኝቷል፡፡ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን ኮሚሽነር አስራት ኃይሌ ባደረጉት ንግግር የአዲስ አበባ እግር ኳስን በማሳደግ እና ተሳታፊዎችን በማብዛት በስፖርቱ ዘርፍ ለሀገር የሚጠቅሙ ተተኪ ወጣቶችን ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት በሚደረገው ጥረትም በከተማዋ የሚገኙ ባለሀብቶች በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያደርጉ ኮሚሽነር አስራት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን የ2013 ዓ.ም የእግር ኳስ ውድድሮች መጠናቀቃቸውን አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት የመዝጊያ መርሀ ግብር በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም ያዘጋጀ ሲሆን በዕለቱም ታዋቂ የስፖርት ቤተሰቦች ተገኝተዋል፡፡ በዕለቱ ለአሸናፊ ክለቦች የዋንጫ እና የሜዳሊያ ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ለምስጉን ዳኞች፣ ለኮከብ ተጫዋቾች እና ኮከብ አሰልጣኞች የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት መርሀ ግብሩ ተጠናቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 07 ቀን 2013 ዓ.ም

በሪጅኑ ያሉት ማከፋፈያ ጣቢያዎች በጥሩ ሁኔታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ……….///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምዕራብ ሪጅን በአካባቢው የሚፈጠሩ የኢንቨስትመንት ዘርፎችን ለማስተናገድ የሚያግዝ በቂ የኤሌክትሪክ አቅርቦት መኖሩን አስታወቀ። የሪጅኑ የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ዳይሬክተር አቶ ቶማስ መለሰ እንደተናገሩት በሪጅኑ ውስጥ የሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች አሁን ያለውንና ሊመጣ የሚችለውን የኃይል ፍላጎት ለማስተናገድ አቅም አላቸው፡፡ በመሆኑም በሪጅኑ ውስጥ የሚገኙትን የተለያየ የኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው 11 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ማሳደግ ሳያስፈልግ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ በሥራ ላይ ያሉት ማከፋፈያ ጣቢያዎች በአሁኑ ወቅት በጥሩ ሁኔታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። በአሁኑ ሰዓት በሪጅኑ ለህብረተሰቡ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል በአማካይ 1 መቶ 16 ሜጋ ዋት መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ በቀጣይ ኢንቨስተሮች ወደ አካባቢው ቢገቡም ጥያቄያቸውን ማስተናገድ የሚያስችል የኤሌክትሪክ አቅርቦት መኖሩን ጠቁመዋል። ይሁንና በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል በመኖሩ ብቻ የኃይል ፈላጊውን ጥያቄ መመለስ ስለማይቻልና በመስመር ብልሽት ምክንያት የኃይል መቆራረጥ እንዳይከሰት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ብለዋል። ሪጅኑ ከማከፋፈያ ጣቢያዎች በተጨማሪ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን ከ2 ሺህ 58 ኪሎ ሜትር በላይ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በማስተዳደር የፍተሻ እና አስቸኳይ የጥገና ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት። እንደ አቶ ቶማስ ገለፃ ሪጅኑ ለምዕራብ ፣ ምስራቅ፣ ሆሮጉድሩ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች እና ለቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል እንዲሁም ለምዕራብ ሸዋ ዞን የተወሰኑ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 07 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

ከ65 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የነጆ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተመረቀ ……….///………. ከአዲስ አበባ በ500 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ከተማ የተገነባው ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በአቶ ሽመልስ አብዲሳ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል። ዛሬ በተካሄደው የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን፣ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጅነር ስለሽ በቀለ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻን ጨምሮ የፌደራልና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ አባ ገዳዎችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል፡፡ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ባለሃብቶች እና ኢንቨስተሮች በአካባቢው በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሳተፉ እድል ይፈጥራል። ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ተመርቀው አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይ በኤሌክትሪክ ኃይል አና በሌሎች ዘርፎች የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሠረት ለማጠናቀቅ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል ለአንድ ሀገር ሁሉ ነገር በመሆኑ በቀጣይ በክልሉ የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶት ይሰራል ብለዋል። ባለሀብቶች የተፈጠረላቸውን ዕድል በመጠቀም በግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች እና በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች በመሳተፍ አካባቢያቸውን ለመቀየር ጠንክረው እንዲሰሩ አሳስበዋል። የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ ትኩረት በማድረግ ለሀገር እድገትና ለአህጉራዊ ትስስር መሰረት የሚሆን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየሠራች ትገኛለች ብለዋል። በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እና የመነጨውን ኃይል ለተጠቃሚው ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ላይ ትኩረት ተሠጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 40 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃያል የማስተላለፍ አቅም እንዳለው የጠቆሙት ሚኒስትሩ ጣቢያው ለነጆ ከተማና አካባቢው ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ከማቅረብ ባለፈ በአካባቢው የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት ፋይዳው የጎላ ነው። ባለሃብቶች በአካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮ ሃብቶችን በአግባቡ በመጠቀም አካባቢያቸውን እንዲያለሙም ዶ/ር ስለሽ ጥሪ አቅርበዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር እና አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ያሉት ሲሆን የተገነባውም በተቋሙ የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል ቢሮ ነው። ለማከፋፈያ ጣቢያው ከ65 ሚሊዬን ብር በላይ ወጪ የተደረገ ሲሆን ይህም በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+5

በዋግ ኽምራ ዞን የተቋረጠው ኤሌክትሪክ መልሶ ተገናኝቷል ........///........ በምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ላለፉት ሁለት ሳምንታት ተቋርጦ የቆየው የዋግ ኽምራ ዞን ኤሌክትሪክ የጥገና
በዋግ ኽምራ ዞን የተቋረጠው ኤሌክትሪክ መልሶ ተገናኝቷል ........///........ በምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ላለፉት ሁለት ሳምንታት ተቋርጦ የቆየው የዋግ ኽምራ ዞን ኤሌክትሪክ የጥገና ስራ ተጠናቆ አካባቢው ኤሌክትሪክ አግኝቷል፡፡ በአካባቢው ከግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም፣ ጀምሮ ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የቆየው በሶስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ስርቆት በመፈፀሙና በመውደቃቸው ነበር። ወደስፍራው ለጥገና የተንቀሳቀሰው ቡድን የተሰረቁትንና የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች አካል በአዲስ በመተካት መልሶ ለመትከል ጊዜ ስለሚወስድ በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶዎች በመተካት አካባቢው ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ማድረግ ችሏል፡፡ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ኦፍላ ወረዳ ፋላ ቀበሌ በሦስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በደረሰ ጉዳት በዞኑ ሰባት ወረዳዎች እና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ላይ ለሁለት ሳምንታት ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ታገል ደገፉ የጥገና ቡድኑ አባላት ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ አስቸጋሪ በሆነ መልክዓ - ምድር በእግር በመጓዝና ከ36 ሠዓት በላይ ያለምግብ በመስራት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በማሳካት አካባቢው ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ በማድረጋቸው ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2013 ዓ.ም

ኢትዮጵያና ጅቡቲ የነበራቸውን የኃይል ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ ………////……….. ኢትዮጵያና ጅቡቲ በመካከላቸው ያለውን የኃይል አቅርቦት ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ፡፡ በኢፌዲሪ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ የተመራና የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ልዑካን ቡድን ከጅቡቲ አቻው ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ በውይይቱም ግንባታው እየተገባደደ ካለው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚመነጨውን የኤሌክትሪክ ሀይል ከኢትዮጵያ ወደ ጂቡቲ ከተዘረጋው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ጋር ለማገናኘት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡ የሚሰራውን ሥራ በተመለከተም አንድ የውጭ ድርጅት በጋራ በመምረጥ ለማስጠናት ከመግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡ በሀገራቱ መካከል ያለውን የኃይል ትስስር የበለጠ ለማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ጽኑ አቋም በመግለፅ በዘርፉ የሚደረገውን ቀጣይ ውይይት በአዲስ አበባ ለማድረግ ተስማምተዋል፡፡ በሶማሌ ክልል ሺኒሌ ዞን አይሻ ወረዳ እየተገነባ ያለው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የሚያመነጩ 48 ተርባይኖች ያሉት ሲሆን እስከ 120 ሜጋ ዋት ሀይል የማመንጨት አቅም ያለው ነው። ፕሮጀክቱ በ257 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ምንጭ - በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 04 ቀን 2013 ዓ.ም