en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 544 subscribers, ranking 8 333 in the Technologies & Applications category and 2 158 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 544 subscribers.

According to the latest data from 27 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by -16 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.06%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.33% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 895 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 7.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 544
Subscribers
-1624 hours
-97 days
+1030 days
Posts Archive
ተቋሙ ለሰብዓዊ ድጋፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ ዕውቅና ተሰጠው ……..////………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰብዓዊ ድጋፍን ተደራሽ ለማድረግ እያከናወነ ላለው ሥራ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል። ሽልማቱን ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ እና ከክልሉ የቀይ መስቀል ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ እና አቶ ንጋቱ ዳንሳ የተረከቡት በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር እና የሰብዓዊ እርዳታውን ለመከታተል የተዋቀረው ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሞገስ መኮንን ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ እንደተናገሩት ተቋሙ በደንብ ከተሰጠው ኃይል የማመንጨት ተልዕኮ ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ሰብዓዊ ድጋፎች ላይ በትኩረት እየተሳተፈ ይገኛል። ባለፈው ዓመት በደቡብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ በዝናብ እጥረት ለድርቅ ለተጋለጡ አራት ወረዳዎች የተደረገውን የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ድጋፍንም ለአብነት አንስተዋል። ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የተበረከተው እውቅና በቀጣይ ተቋሙ በሰብዓዊ ድጋፎች ላይ በተሻለ መልኩ እንዲሰራ መልዕክት የሚያስተላልፍ እንደሆነ ጠቁመዋል። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶኩመንቴሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው ተቋሙ ለማህበራዊ ኃላፊነት ትኩረት በመስጠት በተቋም ደረጃ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አባል ሆኗል። ተቋሙ በየዓመቱ ከሚከፍለው የአባልነት መዋጮ በተጨማሪ ሠራተኞቹ የማህበሩ አባል እንዲሆኑ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የሰብዓዊ እርዳታውን ለመከታተል የተዋቀረው ኮሚቴ አባላት በበኩላቸው ተቋሙ ማህበራዊና አካባቢያዊ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ ፕሮጀክቶቹ ባሉባቸው አካባቢ የተደራጀ ጥናት በማድረግ እና ምላሽ በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡ ተቋሙ ለተሰጠው ዕውቅና በተቋሙ የተቋቋመው የሰብዓዊ ድጋፍ ኮሚቴ አባላት ሚና የጎላ እንደነበር ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

በደቡብ ኦሞ ዞን ለተደረገው የአስቸኳይ ምግብ እርዳታ የማጠቃለያ መርሀ ግብር ተካሄደ ..........///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኦሞ ዞን በአየር ንብረት ለውጥ የተነሳ አጋጥሞ ለነበረው የምግብ እጥረት ያደረገው የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ድጋፍ የማጠቃለያ መርሀ ግብር ተካሄደ። በዞኑ ሐመር፣ ዳሰነች፣ ኛንጋቶም እና ሳላማጎ ወረዳዎች የአስቸኳይ ምግብ እርዳታ ስርጭቱን ለመገምገም ያለመ  የማጠቃለያ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ተወካይና የክልሉ ቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቦርድ አባል አቶ ንጋቱ ዳንሳ መርሀ ግብሩን ሲከፍቱ እንደተናገሩት በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት በሚከሠቱ ሠው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የአስቸኳይ ምግብ እርዳታ ፈላጊ እየሆኑ ይገኛሉ። ባለፉት ዓመታት በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች ላይ ባጋጠመው የአየር ንብረት ለውጥ ምክንያትም በርካታ ዜጎች ለምግብ እጥረት ተጋልጠው እንደነበር አቶ ንጋቱ አስታውሰዋል። ያጋጠመውን የምግብ እጥረት ለመቅረፍ  ክልሉ ባቀረበው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ጥሪ መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 260 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ማድረጉን አቶ ንጋቱ ተናግረዋል። ተቋሙ የክልሉን ጥሪ  ተቀብሎ ላደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። ድጋፉ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንደተሰራጨና ከዚህም በርካታ ልምዶች እንደተገኙበት አቶ ንጋቱ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአካባቢው የሚስተዋለውን የተፈጥሮ አደጋ ለመቀነስና በዘላቂነት ለመፍታትም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል። ተቋሙ የማህበራዊ ድጋፎች ላይ እንዳደረገው ሁሉ በክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት  የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ዋና ፀሐፊ አቶ ጌታቸው ታዓ በበኩላቸው ማህበሩ በሀገሪቱ በሚከሰቱ የተለያዩ ችግሮች በህብረተሰቡ ላይ የሚደርሱ ስቃዮችን ለማቃለል ጥረት እያደረገ ይገኛል። በተጠናቀቀው ዓመትም ከ2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ ለ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። በደቡብ ኦሞ ዞን በአራቱ ወረዳዎች  ለተከሰተው የምግብ እጥረት በሁለት ዙር ለ191 ሺ 395 ዜጎች የተለያዩ ድጋፎችን ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ አንስተው ተቋሙ ማህበረሰቡ ድጋፍ በሚፈልግበት ጊዜ በመድረስ ላደረገው ወቅታዊ ምላሽ  አመስግነዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ተቋሙ ከኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ጎን ለጎን በጥናት ላይ በመመስረት የተለያዩ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በደቡብ ኦሞ ዞን የተደረገውን ድጋፍ የስርጭት ሥራ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር  ልምዱን ተጠቅሞ  እንዲያከናውን መደረጉን አስታውሰው ተቋሙም ሂደቱን በመከታተል እርዳታው በፍትሃዊነት ተደራሽ መደረጉን ማረጋገጥ ችሏል ብለዋል። ተቋሙ ካደረገው ጊዜያዊ ድጋፍ ባለፈ  በቀጣይ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። ከማህበራዊ ድጋፍ ሥራዎች በተጨማሪ በአካባቢው የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ መጀመሩን ጠቁመው ሁሉም ህብረተሰብ በአካባቢው ለሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶች ጥበቃ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ባጋጠመው የመሬት መንሸራተት ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ዳይሬክተሩ በተቋሙ ስም ሀዘናቸውን ገልፀዋል። ተቋሙ ካደረገው 259 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ውስጥ 258 ነጥብ 56 ሚሊዮኑ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 213 ነጥብ 27 ሚሊዮን ብሩ ለምግብና ምግብ ነክ፣ 28 ሚሊዮን ብሩ ለእቃ ማጓጓዝ እንዲሁም ቀሪው 18 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብሩ ደግሞ ለሌሎች አስተዳደራዊ ወጪዎች የዋለ መሆኑን በአውደ ጥናቱ ላይ ተመልክቷል። የድጋፉ ተጠቃሚ ከሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል አቶ ኩያ ሉኩ ተለምየ እና አቶ ሉቡኮ ላሌ ተቋሙ ባደረገው ድጋፍ ህይወታቸውን መታደግ እንደቻሉና በቀጣይ ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠይቀዋል። በማጠቃለያ አውደ ጥናቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ የኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የቀይ መስቀል ማህበርና አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የወረዳዎቹ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ድጋፍ የተደረገላቸው የማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል። በዕለቱም በክልሉ ጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቻ ሻቻ ጎዝዴ ቀበሌ ባጋጠመው የመሬት ናዳ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የህሊና ፀሎት ተደርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሀምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9

photo content

የሀዘን መግለጫ ...///... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ላይ በደረሰው የመሬት መንሸራተት ሳቢያ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን እየገለፁ በአደጋው ቤተሰቦቻቸውን እና ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ላጡ ወገኖቻችን እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መፅናናትን ይመኛሉ።

የተግባር ፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአርክቴክት 1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 02 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ ስለሆነም ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ከ50% በላይ ያገኛችሁ ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት በኢንጅነሪንግ ሰፖርት መምሪያ ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እያሳሰብን፣ ስማችሁ ያልተገለጸ አመልካቾች የማለፊያ ነጥብ ያላመጣችሁ መሆኑን እናሳውቃለን። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 17 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ የመታሰቢያ ፕሮግራም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተካሄደ ......//...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አመራሮችና ሠራተኞች ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት የቀድሞ ሳሊኒ ኩባንያ የአሁኑ ዊ ቢውልድ ግሩፕ መስራች እና ባለቤት ለነበሩት ለሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ የመታሰቢያ ፕሮግራም አካሂደዋል፡፡ በመታሰቢያ ፕሮግራሙ ላይ በአሁኑ ወቅትም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን እየገነባ የሚገኜው ዊ ቢውልድ የቀድሞው ሳሊኒ ኩባንያ በኢትዮጵያ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ጉልህ አስተዋፆ እያደረገ እንደሚገኝ ተነግሯል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የዊቢውልድ ግሩፕ መስራች እና ባለቤት በነበሩት ለሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል፡፡ ለሲሞን ፔትሮ ያከናወኑት ሥራ በሁሉም የፕሮጀክቱ ሠራተኞችና አመራሮች  ዘንድ  ሲታወስ እንደሚኖርና ይህንም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ በማጠናቀቅ አሻራቸው ዘላለማዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በፕሮጀክቱ አመራሮችና ሠራተኞች ሥም ለሲሞንፔትሮ ሳሊኒ ቤተሰብ እና ለ‘ዊ-ቢልድ ግሩፕ’ ኩባንያ ሠራተኞች እንዲሁም ለወዳጆቻቸው መፅናናትን ተመኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሀምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች ለሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ የመታሰቢያ ፕሮግራም አካሄዱ .......////......... የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት የቀድሞ ሳሊኒ ኩባንያ የአሁኑ ዊ ቢውልድ ግሩፕ መስራች እና ባለቤት ለነበሩት ለሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ የመታሰቢያ ፕሮግራም አካሂደዋል። በዊ ቢውልድ ኩባንያ የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር  ስቲፋኖ ሲልቪ በፕሮግራሙ ላይ እንደተናገሩት በሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ አመራር ሰጭነት ኩባንያው በኢትዮጵያ በርካታ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት ለአገልግሎት አብቅቷል። ኩባንያው በኢትዮጵያ በለገዳዲ የመጠጥ ውሃ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ ላይ ሥራ እንደጀመረም ጠቁመዋል። ኩባንያው በኃይል መሠረተ ልማት ዘርፉም የጊቤ 1፣2፣ 3 እና ጣና በለስ ማመንጫ ጣቢያዎችን በመገንባት ለአገልግሎት ማብቃት የቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና ኮይሻ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ይገኛል። ሲሞን ፔትሮ ያከናወኑት ሥራ እና አሻራቸው በሁሉም አዕምሮ  ሲታወስ የሚኖር ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ  ሌጋሲያቸውን ለማስቀጠል የኩባንያው ሠራተኞች በቡድን ስሜት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ሥራ አስኪያጁ በሲሞን ፔትሮ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን ገልፀው ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የዊቢውልድ ግሩፕ እና ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ ማመንጫ ፕሮጀክት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አባይነህ ጌትነት በበኩላቸው ኩባንያው በኢትዮጵያ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን በጥራት በመገንባት ለኃይል ልማት ዘርፉ ዕድገት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። ኩባንያው ከፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም የሠለጠነና ልምድ ያለው ባለሙያ በማፍራት ለእውቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር የራሱን አስተዋፅዖ  እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ዊ ቢውልድ በኢትዮጵያ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳለውና የሌሎች ኩባንያዎች አመራሮችም በአቋራጭ ሳይሆን በረጅም ጊዜ ዕቅድ ውጤታማ እንደሚሆኑ ከሳሊኒ ትምህርት ሊወስዱ ይገባል ብለዋል። የ10 ልጆች አባት የነበሩት ሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ በተወለዱ በ92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም እንደተለዩ የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

I am deeply saddened by the passing of SimonPietro Salini. My condolences to his family and the @webuild_group. His remarkable work on Tanabeles, Gilgel Gibe I, II & III HEP plants and GERD, and Koysha HEP projects has been impactful. May his soul RIP. Ashebir Balcha, CEO,EEP

ሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ አረፉ ...//... የቀድሞው ሳሊኒ ኩባንያ የአሁኑ ዊቢውልድ ግሩፕ ሥራ አስፈፃሚ  የነበሩት ሲሞን ፒትሮ ሳሊኒ በ92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ይህን ተከትሎም ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሲሞንፒየትሮ ሳሊኒ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ገልፀዋል። ዊ ቢውልድ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ መሠረተ ልማቶች ግንባታ ላይ አሻራውን ያኖረ ግንባር ቀደም ኩባንያ ነው። ኩባንያው የግልገል ጊቤ 1፣ ጊቤ 2፣ ጊቤ 3 እና ጣና በለስ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ ያደረገ ሲሆን በአሁን  ወቅት ደግሞ በግንባታ ሒደት ላይ የሚገኙትን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ እና የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን በመገንባት ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በሲሞን ፔትሮ ሳሊኒ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን ገልፀው ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የዊቢውልድ ግሩፕ መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

በኮይሻ ጉብኝት ያደረጉት የፌደራል ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አሻራቸውን አኖሩ .........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የተለያዩ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አከናውነዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ግድቦች በደለል እንዳይሞሉና ተጨማሪ ውሃ እንዲይዙ እያገዘ ይገኛል። የተቋሙ ሠራተኞች በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉ ተቋሙ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን እየተከለ  እንደሆነ ገልፀዋል።  ሠራተኛው በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ላይ በስፋት መሳተፍ እንደሚኖርበት አሳስበዋል። የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ የአካባቢውን ሥነ ምህዳር በመጠበቅ የሥራ ቦታዎችን ለኑሮ ምቹ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የአዳማ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ ባልቻ እና በገቢዎች ሚኒስቴር የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛው በኩረፂዮን በኮይሻ ፕሮጀክት አካባቢ የአረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፋቸው እንደተደሰቱ ገልፀዋል። መርሃ ግብሩ የአካባቢን ገፅታ ለመቀየርና አረንጓዴ  አካባቢን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እና በዩ ቢዩልድ ኩባንያ የኢንቫይሮሜንታል መሃንዲስና የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ አስተባባሪ ሄኖክ ቼኮል እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ምክንያት የተጎዱ ቦታዎችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ሲባል የችግኝ ተከላ ሥራው በሀገር አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከመከናወኑ በፊት መጀመሩን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ሠራተኛ የችግኝ ተከላ ሥራውን እንደ ዋና ሥራ በመያዝ መኖሪያ ቦታውን ምቹ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ በየዓመቱ የተተከሉት ችግኞች አሁን ላይ ፍሬ ማፍራት መጀመራቸውን እና ሠራተኛውም ለምግብነት እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ተገልጿል። የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "የምትተክል ሃገር፣ የሚያፀና ትውልድ" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሀምሌ 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content