en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 555 subscribers, ranking 8 397 in the Technologies & Applications category and 2 165 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 555 subscribers.

According to the latest data from 21 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.74%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 14.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 003 views. Within the first day, a publication typically gains 2 323 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 22 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 555
Subscribers
+124 hours
+87 days
+1030 days
Posts Archive
ተቋሙ በደሴ ከተማ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀመረ ‎……...///…….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደሴ ከተማ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀመረ። በግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ ዓሊ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከተማዋን ዕድገትና የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል  እያከናወነ ላለው በጎ ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ128 ዓመታት በላይ የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ የህዝብ ተቋም ነው። ተቋሙ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ከመላው ህዝብ ጋር በመሆን ከተስፋ ወደሚጨበጥ ብርሃን የቀየረ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያውያን በላባቸው፣ በደማቸውና ባላቸው አቅም ሁሉ ላደረጉት አበርክቶ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ተቋሙ ከሚያከናውናቸው በርካታ የኃይል መሠረተ ልማቶች ጎን ለጎን በልዩ ልዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝም ነው ያብራሩት። እንደ ኢንጂነር አንዱዓለም ገለፃ ከደሴ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር የተጀመረው የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ ተቋሙ በመላ ሀገሪቱ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚያከናውነው አካል ነው። የተቋሙ ባለሙያዎች መሟላት የሚገባቸውን የዲዛይን እና መሰል ጉዳዮች ለሥራ አመራሩ እንዳቀረቡ የቤቱን ግንባታ በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ እንደሚሰራ ቃል ገብተዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ በአማራ ክልል ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታዎችን እያከናወነ ይገኛል። ተቋሙ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ አካባቢዎች የህብረተሰቡን ፍላጎት ያማከሉ ውጤታማ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱንም አስታውሰዋል። የደሴ ከተማን የኃይል አቅርቦት ለማሻሻል የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተገነባ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሙላት ከዚሁ ጎን ለጎን በከተማዋ ለሚኖሩ አረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ኑሮ መሻሻል የቤት ግንባታ መጀመሩ ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የተቋሙ የሥራ አመራሮች እና የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ አሊ በደሴ ከተማ ‎የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አከናውነዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ የተከናወነው በከተማዋ በሚገኘው የቅዳሜ ገበያ አጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በደሴ ባለ 230 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ቅጥር  ግቢ ውስጥ ነው። የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ ፅዱና አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት አንድ አካል በመሆኑ በዕለቱ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዛፎች ተተክለዋል፡፡ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የከተማው የግብርና ቢሮ፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ በተቋሙ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን እና የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

ጳጉሜ 1፣ የጽናት ቀን ይህ ቀን የሀገራችን ሁሉን አቀፍ ስኬት ለማረጋገጥ በማያቋርጥ ጽናትና ብርታት ለተፋለሙ ጀግኖች ክብር የምንሰጥበት ቀን ነው። በዚህም በቅርቡ በሚመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳ
+1
ጳጉሜ 1፣ የጽናት ቀን ይህ ቀን የሀገራችን ሁሉን አቀፍ ስኬት ለማረጋገጥ በማያቋርጥ ጽናትና ብርታት ለተፋለሙ ጀግኖች ክብር የምንሰጥበት ቀን ነው። በዚህም በቅርቡ በሚመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጨምሮ ተቋሙ በሚያከናውናቸው ትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ በጽናት ለተሳተፉ የተቋማችን ሠራተኞች እና መሐንዲሶች ክብር እንሰጣለን። የእነርሱ ጽናት እና የማይናወጥ ቁርጠኝነት ሁሉንም ፈተናዎች ተቋቁሞ ታላቅ ህልምን ወደ ተጨባጭ እውነታ ቀይሯል። እነሱ የጽናት ሕያው ምሳሌዎች ናቸው 💧💡 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ማብሰሪያ ነው ….///….. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ማብሰሪያ ነው አሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ሞገስ መኮንን የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅንና ለምርቃት ዝግጁ መሆንን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት ኃይል ከማመንጨት ባሻገር ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው የህዳሴ ግድብ ብዙ ጫናዎችን ተቋቁሞ በቆራጥ የአመራር ውሳኔ ተጠናቋል፡፡ የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ 54 በመቶ ላይ የሚገኘውን የኃይል ተደራሽነት ሽፋን ለማሳደግና የጎረቤት ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር የጎላ ሚና እንዳለውም አብራርተዋል፡፡ ለረጅም ዘመናት በውጫዊ ጫናዎች እና በነበረብን ድህነትና ኋላ ቀርነት ምክንያት ዐባይን መሰል ድንበር ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብታችንን ተጠቅመን የኃይል ፍላጎታችንን ለማሟላት ሳንችል ቆይተናል ብለዋል፡፡ ይህን ችግር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በመቅረፍ በተፈጥሮ ሀብቷ ተጠቅማ ከድህነት ተላቃ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በራስ አቅም፣ ዕውቀትና ገንዘብ ገንብታ ማጠናቀቋን አንስተዋል፡፡ ግድቡ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር በዓሳ ምርት፣ በቱሪዝም፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በኢንዱስትሪ ልማት እና ቀጣናዊ ትስስርንና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ በኩል ጉልህ ሚና እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች በማድረግ የኢትዮጵያን የመልማት አቅሟን መገደብ እንደማይቻል ዐቢይ ማሳያ መሆኑን ያነሱት አቶ ሞገስ የግድብ ግንባታው መጠናቀቅ ኢትዮጵያ ስታራምድ የቆየችውን የጋራ ተጠቃሚነት መርህ በተግባር በማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን እና የመደራደር አቅሟን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድግ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የላብና የደም ጠብታ ያረፈበት የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ማብሰሪያ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ግድቡ ኢትዮጵያ በጽናት ማደግ እንደምትችል ያሳየ ነው ......///........ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን ያሰቡትን እና ያቀዱትን ከግብ ማድረስ እንደሚችሉ ያሳየ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ተናግረዋል። አቶ ሞገስ እንደገለፁት የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዐባይ ግድብ ላይ ለመጠቀም የነበራት የዘመናት ህልም እውን የሆነበት እና የአይቻልም መንፈስ የተሰበረበት ታሪካዊ ድል ነው። ይህ ግድብ ኢትዮጵያ የራሷን ሀብት በአግባቡ የመጠቀም መብቷን እውን ያደረገችበት የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት። ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ የሚገጥሙ ጫናዎችን ተቋቁማ ለስኬት እንደምትበቃ ያረጋገጠ ነውም ብለዋል። መላው ኢትዮጵያዊያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበት፣ በዲፕሎማሲ እና በመስዋዕትነት ያፀኑት ታሪካዊ ግድብ ነው መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በፍትሐዊነት መጠቀምን መርህ  አድርጋ እየሰራች መሆኑን የገለፁት አቶ ሞገስ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትም ይህን በመረዳት ተባባሪ ሊሆኑ እንደሚገባ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

‎ግድቡ በራስ አቅም የመልማት አቅማችን ዐቢይ ማሳያ ነው‎ .....///..... ‎ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በራስ አቅም የመልማት አቅማችን ዐቢይ ማሳያ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። ‎ ‎ተቋሙ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅንና ለምርቃት መዘጋጀትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ‎ ‎መግለጫውን የሰጡት የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምርቃት ዝግጁ ሆኗል። ‎ ‎ግድቡ ከፋይናንስ ምንጩ፣ በሚይዘው የውሃ መጠን፣ በሚሰጠው ትርጉም ከሌሎች የኃይል ማመንጫዎች ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል። ‎ እስካሁን ያለው ‎የግድቡ ግንባታ ወጪ ከ233 ቢሊዮን ብር በላይ መሆኑንና ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት መሸፈኑን የጠቆሙት አቶ ሞገስ ከዚህ ውስጥ 91 በመቶው ከንግድ ባንክ እንዲሁም ቀሪው 23 ቢሊዮን ብሩ ወይም 9 በመቶው በሕብረተሰብ ተሳትፎ የተገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ከፋይናንስ ተሳትፎ በተጨማሪ ሕብረተሰቡ በዕውቀት፣ በዲፕሎማሲ፣ በጉልበት እና በሀሳብ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደነበረው አብራርተዋል። ይህም ግድቡ በጫናዎች ሳንበገር በፍትሐዊነት በራሳችን አቅም የመልማትና ብሔራዊ ጥቅማችንን የማስጠበቅ ጽኑ ፍላጎታችንን ለዓለም ያሳየ ነው ብለዋል። አሁን ላይ የግድቡ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለምርቃ ዝግጁ መሆኑን ያወሱት አቶ ሞገስ በህዳሴ ደዴሳ ሆለታ እና በበለስ መስመር በኩል ኃይሉ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እየገባ መሆኑን አብራርተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

‎ተቋሙ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅንና ለምርቃት መዘጋጀትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። ‎ ‎መግለጫውን የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በመስጠት ላይ ናቸው። ‎ ‎ጋዜጣዊ መግለጫው በግድቡ ታሪካዊና ብሔራዊ ጠቀሜታ፣ የግድቡ የቴክኒክ እና የኦፕሬሽን ስኬት፣ ለሀገር ኢኮኖሚና ልማት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እንዲሁም ተግዳሮቶች እና የወደፊት ዕቅዶች ዙሪያ ትኩረት ያደርጋል። ‎ ‎እኛም በጋዜጣዊ መግለጫው የሚነሱ ኃሳቦችን እየተከታተልን በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የዘንድሮው የመውሊድ በዓል ስናከብር የዘመናት ቁጭ የወለደው እና የአይቻልም
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የዘንድሮው የመውሊድ በዓል ስናከብር የዘመናት ቁጭ የወለደው እና የአይቻልምን መንፈስ በይቻላል የቀየረውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠናቀን በምናከብረው የምረቃ ዋዜማ  ላይ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ  ማድረግ መቻላችን እኛ ኢትዮጵያውያን የምናስበውን ለማሳካት ምንም ዓይነት ፈተና የድል አድራጊ አርበኛ ልጆች መሆናችን ለዓለም ህዝብ ያስመሰከርንበት ነው። በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ በድጋሜ እንኳን ለመውሊድ በዓልና ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማጠናቀቂያ የድል ብስራት ቀን አደረሳችሁ! ኢድ-ሙባረክ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነሐሴ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል አቅርቦት አቅም በአራት እጥፍ ያሳድጋል ……...///……… የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል አቅርቦት አቅም በአራት እጥፍ እንደሚያሳድግ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። በምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ የተመራ የልዑካን ቡድን በመገንባት ላይ ያለውን የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በመስክ በመገኘት ገምግሟል። ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት ከተሞቻችን የሚያስፈልጋቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማሟላት ተቋሙ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የደሴ ከተማን የኤሌክትሪክ ፍላጎት አቅም ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት መሸከም የሚችል ነው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት ዕቅድ መያዙን የጠቀሱት ኢንጂነር አንዱዓለም የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን ለመገንባት ከተማ አስተዳደሩ ለካሳና ተያያዥ ጉዳዮች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚያስፈልጉ ተጨማሪ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎችን በቅርቡ ወደ ሳይት የማጓጓዝ ሥራዎች ይጀመራሉ፡፡ ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ አይደለም ያሉት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከተማ አስተዳደሩ የግንባታውን ሂደት በቅርበት እየተከታተለ እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ ዓሊ እንደገለፁት በከተማዋ የሚስተዋለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ፍላጎት ያለመጣጣም ችግር  ለመቅረፍ ከተማ አስተዳደሩ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅርበት ይሰራል፡፡ ከፕሮጀክቱ ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ከተማ አስተዳደሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋሙ ከ8 መቶ ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የትምህርት ግብዐቶች ድጋፍ አደረገ ‎........///........ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደሴ ከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኘው የጢጣ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተለያዩ የትምህርት ግብዐቶችን ድጋፍ አደረገ። ‎ ‎ድጋፉን የተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ ለከተማ አስተዳደሩ ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ አሊ አስረክበዋል። ‎ ‎የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ ዓሊ በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ድጋፉ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ እገዛ ያደርጋል። ‎ ‎የተደረገው ድጋፍ ወቅቱን የጠበቀ በመሆኑ የትምህርት ግብዓቶችን መግዛት ለማይችሉ ወላጆች ትልቅ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል። ‎ ‎የጢጣ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት አቅራቢያ እንደሚገኝ የጠቀሱት ተወካይ ከንቲባው ይህም ህብረተሰቡ በፕሮጀክቱ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲሰማው እንደሚያደርግ አብራርተዋል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለትምህርት ዕድገት እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ አድንቀው በቀጣይ መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። ‎ ‎በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ትምህርት አምራች ትውልድን ለመፍጠር ትልቅ መሳሪያ መሆኑን ስለሚረዳ ከትምህርት ገበታቸው የራቁ ተማሪዎችን ለመመለስ እየተደረገ ያለውን ጥረት ተቋሙ ይደግፋል። ‎ ‎ድጋፉ 250 ለሚደርሱ የጢጣ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የጽህፈት መሳሪያዎች እና የደብተር መያዣ ቦርሳዎችን ያካተተ ሲሆን ለዚህም ተቋሙ 825 ሺህ ብር ወጪ ማደረጉን ተናግረዋል። ‎ ‎ተቋሙ የትምህርት ጥራትን ለማረጋጋጥ በትውልድ ልማት ሥራዎች ላይ አሻራውን እያሳረፈ እንደሚገኝ ጠቅሰው በቀጣይም መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። ‎በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካዮች ተገኝተዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እውቅና ተሰጠው …....///…..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት በወጪ ንግድ ያስመዘገበውን ከፍተኛ ገቢ ተከትሎ ከኢ.ፌዲሪ. ንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እውቅና አግኝቷል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት “የኢትዮጵያን ይግዙ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው 2ተኛው የንግድ ሳምንት መርሀ ግብር በወጪ ንግድ ዘርፍ ለተገኘው ስኬታማ ውጤት ተቋማት በወጪ ንግድ ገቢ አፈፃፀምን መሰረት ያደረገ የእውቅና መርሀግብር አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ብቻ ከ118 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የሙስና መጠቆሚያ መተግበሪያ ይፋ ሆነ፤ …..///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ምስጢራዊነቱን በጠበቀ መልኩ ለመጠቆም የሚያስችል መተግበሪያ (https://Whistleblowing.eep.com.et) ወደ ሥራ መግባቱን የተቋሙ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ደረጀ አጥናፌ እንደገለፁት መምሪያው በተቋሙ የሚስተዋሉ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የተቋሙን አፈፃፀም ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡ ችግሩን አስቀድሞ ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከማከናወን በተጨማሪ ሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት ምስጢራዊነቱን በጠበቀ መልኩ ጥቆማ ለመስጠት የሚያስችል መተግበሪያ በተቋሙ መበልፀጉን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ መተግበሪያው በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በሳይበር ደህንነት መምሪያዎች ተረጋግጦ ሥራ ላይ እንዲውል ይሁንታ ማግኘቱንም ተናግረዋል፡፡ ጥቆማው የተፈጸመው ወይም ሊፈጸም የታሰበው ድርጊት ምን እንደሆነ፣ የተጠርጣሪ ሙሉ ስም፣ መለያ ቁጥር እና የሚሠራበት የሥራ ክፍል፣ በድርጊቱ የተገኘ ወይም ወደ ፊት ሊገኝ የሚችል ጥቅም እንዲሁም የደረሰ ወይም ሊደርስ የሚችል ጉዳት ማካተት እንዳለበትም ተናግረዋል። በተቋሙ የሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች የሥነ-ምግባር ደንብ አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት የሚቀርቡ ጥቆማዎች እውነተኛ፣ ያልተዛባ፣ ከበቀል የፀዳ፣ አሳሳች ያልሆነ እና ምክንያታዊ በሆነ እምነት ላይ የተመሠረተ መሆን እንደሚኖርበትም አስገንዝበዋል። መተግበሪያው ሠራተኞች እንዲሁም ማንኛውም አካል ባሉበት ቦታ ሆነው ያለምንም ተፅዕኖ ጥቆማ ለመስጠት እንደሚያስችላቸው የጠቆሙት አቶ ደረጀ ጠቋሚው ፈቃደኛ ከሆነ በአካል ቀርቦ ስለ ጉዳዩ ማስረዳት እና የምርመራ ሂደቱን ማገዝ እንደሚችልም ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ተቋሙ አብዛኛውን በጀቱን ለኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚያውል ገልፀዋል፡፡ ይህ በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውልና ፕሮጀክቶች ከሙስናና ብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ በታቀደላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የቁጥጥር ሥራው መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሠራተኞች እንዲሁም ጥቆማ ያለው አካል በበለፀገው መተግበሪያ ትክክለኛ ጥቆማ በመስጠት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም