en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 697 subscribers, ranking 8 049 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 697 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 141 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 487 views. Within the first day, a publication typically gains 2 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 697
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+14130 days
Posts Archive
photo content
+1

photo content
+9

በከርሰምድር እንፋሎት ኃይል ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ይገባል .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከርሰምድር እንፋሎት ኃይልን በአግባቡ ለመጠቀም በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት እንደሚገባ በተቋሙ የጂኦተርማል ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡ ተቋሙ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በተከፈተው 4ኛው ዓመታዊ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (MINTEX Ethiopia 2025) ላይ በከርሰምድር እንፋሎት የኃይል ልማት ላይ እያከናወናቸው የሚገኙ ሥራዎችን እና የዘርፉን የወደፊት ዕቅዶች የሚያሳዩ መረጃዎችን ለዕይታ አቅርቧል። የኤግዚቢሽኑ አስጎብኚ የጂኦተርማል ከፍተኛ ባለሙያው አቶ ሰለሞን ከበደ እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ስብጥርን ለማሳደግና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት የሚያስችሉ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ በከርሰምድር እንፋሎት ሀብት በተፈጥሮ የታደለች መሆኗን የጠቀሱት ባለሙያው ይሁን እንጂ ዘርፉ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እና የሰለጠነ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ እምቅ ሀብቱን በአግባቡ መጠቀም እንዳልተቻለ ገልፀዋል፡፡ በዚህም ተቋሙ የከርሰምድር እንፋሎት ኃይል ግንባታ ዘርፍን ለማሳደግ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል፡፡ እንደ አቶ ሰለሞን ገለፃ ኤክስፖው የከርሰምድር እንፋሎት በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ ያለውን ድርሻ እና ፋይዳ ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ይረዳል፡፡ በማዕድን ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት እና በማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት በጋራ የተዘጋጀው 4ኛው ዓመታዊ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ እስከ ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለጎብኝዎች ክፍት መደረጉም ታውቋል። ኤክስፖውን የተቋሙ  ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች ጎብኝተውታል።                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

Geothermal Solutions Expo – Mining Sector Growth Watch the TikTok video for more info 👇 https://www.tiktok.com/@ethio_power/video/7572543701210172684 EEP continues advancing clean and reliable energy for national development. The Geothermal initiative is creating sustainable power solutions that support Ethiopia’s mining sector and strengthen green economic growth. 💡 "Clean Energy for a Better Life!" #EEP #GeothermalEnergy #Ethiopia #MiningSector #CleanEnergy #SustainablePower #RenewableEnergy Official EEP Links 📌Facebook: https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌Telegram: https://t.me/EEPCommuication 📌Twitter: https://twitter.com/EEPethiopia 📌 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power-የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኃይል 📌YouTube: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌TikTok: https://tiktok.com/@ethio_power 📌 Website: https://www.eep.com.et

የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ከአደጋ ለመከላከል አባላቱ በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ ……///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ አባላት  የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ከስርቆት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ፡፡ አገልግሎቱ በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ለተመለመሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በቁልፍ ተቋማት መሰረተ ልማት ጥበቃ ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን አባላቱ ስለቁልፍ ተቋማት ምንነት፣ ሀገራዊ ፋይዳ፣ ደህንነት እና ስጋቶች በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ደህንነት እንዲያስጠብቁ ለማስቻል ያለመ ነው፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በአዋጅ ቁጥር 1278/2014 መሰረት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ቁልፍ የመሰረተ ልማቶችን ደህንነት ደረጃ(standard) የማውጣት እንዲሁም በደህንነት ጥበቃ ላይ ለሚሰማሩ ባለሙያዎች ሥልጠና የመስጠት ተልዕኮ እንዳለውም ተገልጿል፡፡ በዚህም ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ የሆነውን የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ደህንነት ለማረጋገጥ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በየ24 ሰዓቱ መረጃ በመለዋወጥ እና ጥናቶችን በማድረግ በትብብር እየሰራ መሆኑም ተብራርቷል፡፡ በቁል መሰረተ ልማቶች ጥበቃ ዙሪያ እየተሰጠ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና የሁለቱ ተቋማት ትብብር ማሳያ መሆኑንም ነው የተጠቆመው፡፡ ሠልጣኝ አባላቱ በተመደቡባቸው ሪጅኖች ከሥልጠናው ያገኟቸውን ዕውቀቶች በመተግበር፣ መረጃዎችን በማደራጀት፣ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀድሞ በመለየት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ተጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም አባላቱ ነባራዊ ሁኔታዎችን እና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ከግምት በማስገባት የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ከአደጋ የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት ተግባራትን ማከናወን እንዳለባቸው ተብራርቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በቀጣይም የ24 ሰዓት የመረጃ ልውውጡን በማጠናከር እና በኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት ላይ ያሉ ስጋቶችን በየጊዜው በመተንተን ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ሥራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አረጋግጧል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

በ2022 ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ብቻ ከ2.7 ቴራ ዋት ስዓት በላይ ኃይል ያስፈልጋል …....///.....… በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቁጥር ተከትሎ የተሽከርካሪዎች የኃይል ፍላጎት በ2017 ዓ.ም ከነበረበት 489 ሜጋ ዋት በ2022 ዓ.ም ወደ 2.7 ቴራ ዋት እንደሚያድግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያስጠናው አንድ ጥናት አመለከተ፡፡  ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ተፅዕኖ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግሪድ ሲስተም  ላይ በሚል ርዕስ ያስጠናውን ጥናት ይፋ አድርጓል፡፡  ጥናቱ የተሸከርካሪዎቹ የኃይል ፍላጎት፣ መሰረተ ልማቶች ላይ ያላቸው ተጽዕኖ፣ የቮልቴጅ መረጋጋትን ከማስተካከል አኳያ እና እነዚህን ተፅኖችን ለመቋቋም የሚያስችሉ የመፍትሄ ሀሳቦችን በዝርዝር ዳሷል፡፡ የኢፊዲሪ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ያዘጋጀውን ስትራቴጂክ እቅድ መሰረት በማድረግ የተከናወነው ጥናቱ ከ2017-2022 ዓ.ም ያለውን ጊዜ የኃይል አጠቃቀም አዝማሚያ  የሚዳስስ እንደሆነ የጥናቱ ቡድን መሪ ኢንጅነር ሀብታሙ አበበ ገልፀዋል፡፡ እንደ ኢንጅነሩ ገለፃ በዚህ ጥናት የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች በዓይነት እና በፍጆታ መጠናቸውን መለየታቸውን አመልክተው ባሶች በኃይል ፍጆታ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ ይህን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ የሚያስችል አቅም መገንባቱን  የገለፁት ኢንጂነር ሀብታሙ የብሔራዊ ኃይል ቋቱ ላይ የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከወዲሁ መስራት እንደሚገባዉ ጠቁመዋል፡፡   ጥናቱ በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል፣ በፖሊሲ ፕሮሰስ እና ለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ፣ በፕሮጀክት ቢሮ እንዲሁም ከምርምር እና ልማት ክፍል በተውጣጡ የተቋሙ ባለሙያዎች የተሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በመድረኩ የተገኙት የኢትዮ-ፓዎር አካዳሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ ውስጣዊ ትብብርን በማጠናር የተቋሙን ያልተዳሰሱ ገፅታዎች በጥናት ማስተዋወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

በቅንጅት በመስራት የዘርፉን የፋይናንስና ግዥ ሥራዎች ለማሻሻል እየሰራሁ ነው -ዘርፉ ……..///…….. ቅንጅታዊ አሰራሮችን በመዘርጋት የፋይናንስ እና ግዢ ሥራዎችን ለማሻሻል እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ የፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ግምገማ አካሂደዋል፡፡  የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ እንደገለፁት የግምገማ መድረኩ በዘርፉ የፋይናንስ እና ግዥ ሥራዎች ላይ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። መምሪያው ከግዥና ፋይናንስ ጋር የተያያዙ አሰራሮችን በማዘመን የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በማሻሻል በኩል ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም መምሪያው የዘርፉን ውጤታማነት ከፍ የሚያደርጉ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው መሰል የግምገማ መድረኮች መዘጋጀታቸው በቀጣይ አመራሩ እና ሠራተኛው ለተሻለ የሥራ አፈፃፀም እንዲነሳሱ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቶችን የፋይናንስ ወጪና ገቢ ክትትል ማድረግ፣ በወቅቱ ለሚቀርቡ የግዥ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት፣ ለሠራተኞች የሳፕ የአሰራር ሥርዓት ሥልጠና መስጠት መቻሉ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖች መሆናቸውም በግምገማ መድረኩ ላይ ተነስቷል፡፡ መምሪያው በሩብ ዓመቱ የ2017 እና 2018 በጀት ዓመት የሒሳብ ማስታረቅ ሥራ በሳፕ የአሰራር ሥርዓት መሰረት ማከናወን መቻሉ በመድረኩ ተጠቅሷል፡፡ የዘርፉ የ2017 የግማሽ በጀት ዓመት የሒሳብ ሥራዎች በውጭ ኦዲተር የማስመርመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው የተገለፀው፡፡ በዕቅድ አፈፃፀሙ ላይ በተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

የፈተና አሰጣጥ ተአማኒነትን ለማሳደግ የሚያስችል ዲጂታላይዝ የፈተና ስርዓት መተግበሪያ ተዘጋጅቷል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የበለፀገው የዲጂታል ፈተና ስርዓት መተግበሪያ ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም ከተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች እና ከሠራተኛ ማህበር አመራሮች ለተውጣጡ የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች በዲጂታል የፈተና ስርዓት አተገባበር ዙሪያ በተዘጋጀው ሥልጠና ላይ እንደተናገሩት የበለፀገው የፈተና ስርዓት  ወጪ እና ጊዜን በመቆጠብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል፡፡ የዲጂታል የፈተና ስርዓቱ የፈተና አሰጣጡን ምቹ ከማድረጉም ባሻገር የፈተና ውጤት ተአማኒነትን እንደሚያሳድግም ነው የገለፁት። በፈተና ስርዓቱ ላይ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ የሳይበር ሴኪዩሪቲ፣ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የሥራ ክፍሎች እና ተፈታኞች ከፍተኛ ሚና ያላቸው መሆኑን የገለፁት ደግሞ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ መምሪያ የኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነር ቃለአብ አየለ ናቸው። ከእያንዳንዱ የሥራ ክፍል ሁሉንም የሙያ መደቦች ለመለካት የሚያስችል የመመዘኛ ጥያቄዎች በፈተና ቋት ውስጥ እንዲቀመጡ ይደረጋልም ብለዋል። ይህ ዲጂታላይዝ የፈተና ስርዓት የደረጃ ዕድገት፣ዝውውር፣ የቅጥር እና ሌሎች የምዘና ፈተናዎችን ለመስጠት የሚያስችል መተግበሪያ መሆኑ ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

መምሪያው የትውውቅ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማካሄድ ጀመረ ….///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ደህንነት መምሪያን ለተቀላቀሉ አዳዲስ ባለሙያዎች እና በመከላከያ ሚኒስቴር ተመልምለው የተላኩ የቀድሞ መከላከያ ሚኒስቴር አባላት የትውውቅ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የትውውቅ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ዋና ዓላማ የተቋሙን ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ ተቋማዊ ስትራቴጂ፣ የተቋሙ አደረጃጀቶች እና አሰራር ተቋሙን ለተቀላቀሉ አዳዲስ ሠራተኞች ለማሳወቅ ነው፡፡ በትውውቅ መርሐ ግብሩ ላይ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ እንደተናገሩት አዳዲሶቹ ባለሙያዎች እና በጡረታ ተሰናብተው የተቋሙን የንብረት እና የሰው ሀብት ደህንነት ሥራን ለማገዝ የተቀላቀሉ የቀድሞ መከላከያ አባላት በሀገሪቱ በሚገኙ የተቋሙ ሪጅኖች ምድብ ተሰጥቷቸው ይሰማራሉ፡፡  ዳይሬክተሩ በሰጡት ቃል ባለፉት ሶስት ዓመታት እንደ ተቋም እና ሀገር በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ውድመት መድረሱን ይፋ አድርገው በተቋም ደህንነት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ የበላይ አመራሩ እና ቦርዱ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ በመሆኑም መድረኩ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት መምሪያውን ለተቀላቀሉ ባለሙያዎች ስምሪት ከመዉሰዳቸው በፊት የሥራ ደርሻቸውን በማሳወቅ በተቋመ ላይ የሚከሰቱ የአደጋ ስጋቶች ለመከላከል ያለመ መሆኑን በመድረኩ ተመላክቷል፡፡ ባለፈው ሩብ ዓመት መምሪያው በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የተቋሙን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችሉ ሥራዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መሰራቱን የገለፁት አቶ ከሊል መምሪያውን የተቀላቀሉ ባለሙያዎች ለሥራዉ መቀላጠፍ የጎላ ድርሻ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ከፓዎር አካዳሚ ጋር በመተባብር የተዘጋጀዉ ይህ የትውውቅ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ዛሬን ጨምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ እንደሆነ በመድረኩ ተገልጿል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ጣቢያው የሲስተም ማዘመን ስራ እየሰራ ነው ……..///…………   የግልገል ጊቤ 1 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመቆጣጣሪያ የስካዳ ሲስተሙን የማዘመን ስራ እየሠራ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ ገለፁ። ሲስተሙን ማዘመን  ያስፈለገው ጣያቢው ከሃያ ዓመት በላይ የቆየ በመሆኑ ቀደም ሲል ይጠቀምበት የነበረውን ሲስተም  አሁን ካለው ቴክኖሎጂ ጋር  አጣጥሞ ለመስራት እና ኃይል  የማመንጨት ሂደቱን አስተማኝ ለማድረግ በማስፈለጉ እንደሆነ አቶ ደሳለኝ  ተናግረዋል። አዲሱ ስካዳ 250  የተባለው ሶፍትዌር የስካዳ ሲስተሙ ከዋናው ኃይል መቆጣጠሪያ ግሪድ የሚተላለፉ መልዕክቶችን በፍጥነት መቀበል፣  ማስተላለፍ እና ኃይል  በማመንጨት ሂደት  ወቅት በዩኒቶች ላይ የሚፈጠሩ ችግሮችን ከነምክያታቸው መዝግቦ ማቆየት የሚችል እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ  አብራርተዋል። ለሲስተም ማሻሻያው የሚያስፈልጉ የቅድመዝግጅት እና የኢንስታሌሽን ሥራዎች በጣቢያው የጥገና ሰራተኞች መሰራቱን ገልፀዋል። በጀነሬሽን ቢዝነስ የኮንትሮል እና ኢንስትሩመንቴሽን ሥራአስኪያጅ አቶ ዳንኤል አበባው  የስካዳ ሲስተም ማሻሻያ የሲስተሙ አምራች ከሆነው የኦስትሪያው አንድሪዝ ሃይድሮ ጋር በተደረገው ስምምነት ሥራው መጀመሩን ገልፀዋል ። በስምምነቱ መሰረት  የግልገል ጊቤ 1  እና በጣና በለስ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ሲስተም የማዘመን ስራ የሚሚሰራ በመሆኑ ጊቤ 1 ማመንጫ ጣቢያ  የማዘመን ሥራው መጠናቀቁን አስረድተዋል፡፡ በጣና በለስም የማሻሻያ ሥራውን ለማከናወን አስፈላጊ ዕቃዎቸወ በመጓጓዝ ላይ መሆናቸውን አቶ ዳንኤል ገልፀዋል። እንደ አቶ ዳንኤል ገለፃ አንድሪዝ ሃይድሮ ዕቃዎችን ማቅረብ፣ የኦፕሬቲነግ ሲሰተም ማስተካከል  እና የፍተሻ ሥራዎችን የሚያከናውን ሲሆን  በተጨማሪም ከሁለቱ ጣቢያዎች ለተውጣጡ የኦፕሬሽን የጥገና ባለሙያዎች በሁለት ዙር ሥልጠና የሚሰጥ ይሆናል። ከሁለቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለተውጣጡ የጥገና ባለሙያወች በመጀመሪያው ዙር ሥልጠና መስጠት የተጀመረ ሲሆን ሥልጠናው ለወደፊት የሚያስፈልጉ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም ለመስራት መደላድል ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

የውጤት ማስታወቂያ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነሀሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም በኢንቫይሮመንታሊስት 1ኛ ፣ በሶሾሎጂስት 1ኛ እና በኦኩፔሽናል ሄልዝና ሴፍቲ የስራ መደብ ማስታወቂ
+4
የውጤት ማስታወቂያ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነሀሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም በኢንቫይሮመንታሊስት 1ኛ ፣ በሶሾሎጂስት 1ኛ እና በኦኩፔሽናል ሄልዝና ሴፍቲ የስራ መደብ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል በኢንቫይሮመንታሊስት 1ኛ ፣ በሶሾሎጂስት 1ኛ እና በኦኩፔሽናል ሄልዝና ሴፍቲ የስራ መደቦች ከተ.ቁ 1 እስከ 4 ያላችሁ በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከህዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የትራንስሚሽን ቢዝነስ ቅጥርና ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮይሻ የውሃ ኃ/ማ/ፕሮጀክት ሲቪል መሐንዲስ 1ኛ (ፒአር1) ጂኦሎጂስት 1ኘሰ (ፒአር1) እና ጂኦቴክኒካል ላብ ቴክኒሻያን 1ኛ (ኤስፒ 1) የስራ መደ
+1
የውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮይሻ የውሃ ኃ/ማ/ፕሮጀክት ሲቪል መሐንዲስ 1ኛ (ፒአር1) ጂኦሎጂስት 1ኘሰ (ፒአር1) እና ጂኦቴክኒካል ላብ ቴክኒሻያን 1ኛ (ኤስፒ 1) የስራ መደቦች ላይ የውጭ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 10 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት መስፈርቱን አሟልታችሁ የፅሁፍ እና የቃል ፈተናውን ወስዳችሁ ያለፋችሁ አመልካቶች ከጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በሲቪል ኢንጂነር እና በጂኦሎጂስት የሥራ መደቦች ላይ ያለፋችሁ ተወዳዳሪዎች የፋይዳ መታውቂያ ትምህርት ማስረጃችሁን እና ኮስት ሼሪንግ በመያዝ እንዲሁም ለጂኦቴክኒካል ላብ ቴክኒሺያን 1ኛ ያለፋችሁ ተወዳዳሪዎች የፋይዳ መታወቂያ፣ የትምህርት ማስረጃ እና ሲ.ኦ.ሲ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

‎በደሴና እና ኮምቦልቻ ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ተከስቷል ‎.....///..... ‎በደሴና እና ኮምቦልቻ ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ማጋጠሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን አስታወቀ። ‎ ‎በሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና መምርያ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለጹት የኃይል መቋረጡ ያጋጠመው በኮምቦልቻ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል በአንደኛው ላይ ባጋጠመ የእሳት አደጋ  ምክንያት ነው። በአደጋው የትራንስፎርመሩ ታፕ ቸንጀር ላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል። ‎ ሪጅኑ ‎የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ርብርብ እያደረገ በመሆኑ የኃይል መቋረጥ ባጋጠመባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም