en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 528 subscribers, ranking 8 328 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 528 subscribers.

According to the latest data from 06 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 6 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.05% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 323 views. Within the first day, a publication typically gains 2 492 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 528
Subscribers
-324 hours
-97 days
+630 days
Posts Archive
በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል ……………/////……………… ዛሬ ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል፡፡ በቴክኒክ ችግር የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የቴክኒክ ክፍል ባልደረቦቻችን ርብርብ በማድረግ ላይ ናቸው። በቀጣይ አንድ ሰዓት ውስጥ ደረጃ በደረጃ ኃይል የማገናኘት ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል። ህዳር 15 ቀን 2013

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ ……………….///…………….. የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይ
+2
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ ……………….///…………….. የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው አልፎ አልፎ የሚያጋጥመውን የግብዓት አቅርቦት እና የጥገና ሥራዎች ዙሪያ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ከተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡ በማመንጫው በሚከናወን የጥገና ስራ፣ የተረፈ ምርት አወጋገድ እና የኬሚካል አቅርቦት ላይ እየተሰሩ ስላሉ ሥራዎች ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ ተደርጎለታል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ከተቋሙ ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አረጋግጠዋል፡፡ በ2010 ዓ.ም መጨረሻ ተመርቆ ከወራት የሙከራና ፍተሻ ሂደት በኋላ ሥራ የጀመረው ረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ በዓመት በአማካይ 185 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ባለፈው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ኢነርጂ ማምረት ከቻሉ የኃይል ማመንጫዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ምክትል ከንቲባዋ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ሥፍራውን የጎበኙ ሲሆን ከሠራተኞች ጋርም ተነጋግረዋል፡፡ ህዳር 14 ቀን 2013 ዓ.ም.

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
+3
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ ……………./////…………… የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እና የዕድገት መሰላል ትግበራ የተቋሙን የአፈፃፀም አቅም ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ የኢትየጵያ ኤሌክት
+1
የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ ……………./////…………… የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እና የዕድገት መሰላል ትግበራ የተቋሙን የአፈፃፀም አቅም ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ ገለፁ፡፡ ተቋሙ 27 ለሚሆኑ የስራ መሪዎችና ሠራተኞች የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እንዲሁም የዕድገት መሰላል ቀረፃና ትግበራ ላይ ያተኮረ የ5 ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ሠልጣኞች በቆይታቸው በብቃት ማዕቀፍ ሞዴል፣ የብቃት ማዕቀፍ አስተዳደር ጥቅሞች ፣ የብቃት ማዕቀፍ ማፒንግ፤ የዕድገት መሰላል ዕቅድ እና ልማት እንዲሁም በሌሎች ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮች የፅንሰ ሃሳብና የክህሎት ስልጠና አግኝተዋል፡፡ በተቋሙ የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ እንዳሉት በእያንዳንዱ የስራ መደብ የተለያዩ እርከን ያላቸው የብቃት ማዕቀፍ ደረጃዎች ተዘጋጅተዋል፡፡ የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት ተግባራዊ በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ካላቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ-ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ልምድ መወሰዱን ዶ/ር ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ላይ የተገኙ ግብአቶችን በማካተት በቀጣይ አንድ ተጨማሪ ውይይት ከተካሔደ በኋላ ወደ ትግበራ እንደሚገባም ነው ዶ/ር ወንድወሰን ያስታወቁት፡፡ ህዳር 09 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

photo content
+9

photo content
+9

‹‹ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ›› መርሃግብር በፎቶ

የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አጋርነታቸውን ገለፁ …………………………….///……………………………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ‹‹ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማ
+2
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አጋርነታቸውን ገለፁ …………………………….///……………………………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ‹‹ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ›› በሚል መሪ ቃል ለሠራዊቱ ድጋፋቸውን ገልፀዋል፡፡ በዋና መስሪያ ቤት በተካሄደው መርሃ ግብር ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል፡፡ ሁሉም ተሳታፊዎች ለአንድ ደቂቃ ቀኝ እጃቸውን በግራ ደረታቸው ላይ አድርገው በመቆም ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ክብር የገለፁ ሲሆን፤ ለአንድ ደቂቃ ባለማቋረጥ ጭብጨባ በማሰማት ለሠራዊቱ ያላቸውን አጋርነት ገልፀዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ህግን ለማስከበር ተሰማርቶ ከፍተኛ ድል እየተቀዳጀ ላለው ለኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ክብር በመስጠት እንዲሁም፤ በህዝብና መንግስት የተጣለባቸውን ግዳጅ ሲወጡ በጁንታው ሀይል ክህደት የተሰዉ የመከላከያ ሠራዊት አባላትም ተዘክረዋል፡፡ ህዳር 08 ቀን 2013 ዓ/ም

የተከዜ ኃይል ማመንጫ ግድብ ተመቷል ተብሎ የተናፈሰው ወሬ ሀሰት ነው ………………../////………….. የተከዜ ሀይል ማመንጫ ግድብ በቦምብ ተመቷል ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን በትግራይ ክል
የተከዜ ኃይል ማመንጫ ግድብ ተመቷል ተብሎ የተናፈሰው ወሬ ሀሰት ነው ………………../////………….. የተከዜ ሀይል ማመንጫ ግድብ በቦምብ ተመቷል ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን በትግራይ ክልል እየተካሄደ ካለው ህግን የማስከበር እርምጃ ጋር ተያይዞ መረጃ ለህዝብ እያደረሰ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ በማህበራዊ ድረገጹ እንዳስታወቀው ተከዜ ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ልክ እንደ ሌሎቹ የኃይል ማመንጫ ግድቦች ሁሉ በፌደራል መንግሥት የተገነባና የሚያስተዳድረውም የፌደራል መንግሥት ነው። አምነስቲ ኢንተርናሽናል የህወሓት ሚልሻዎች በማይካድራ በንጹሀን ዜጎች ላይ የፈፀሙትን ጭፍጨፋ አስመልክቶ ሪፖርት ባወጣበት በህዳር 3፣ 2013 ዕለት፣ የህዝብን የትኩረት አቅጣጫ ለማስቀየር የተከዜ ግድብ በቦንብ እንደተመታ የሚያትት ሆን ተብሎ የተቀናበረ፣ የሀሰት መረጃን ህወሓት በቴሌቪዥን አሰራጭቷል ብሏል። ባለሁለት ክበብ ቅስት ያለው እና በውሀ የተሞላ ግድብ በቦንብ ቢመታ ሊያስከትል የሚችለው መጥለቅለቅ እና ጥፋት ማንም ሊገምተው የሚችል መሆኑን የመረጃውን ሀሰተኛነት በቀላሉ ያረጋግጣል ሲል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ገልጿል፡፡ ሕዳር 4 ቀን 2013 ዓ.ም

ተቋሙ በ6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የአማካሪ ግዢ ሥምምነት ተፈራረመ ............./////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለደብባዊ የኃይል ቋት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ
+3
ተቋሙ በ6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የአማካሪ ግዢ ሥምምነት ተፈራረመ ............./////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለደብባዊ የኃይል ቋት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ የኢንጂነሪንግ፣ ግዥና ኮንስትራክሽን ሥራዎች የአማካሪ ቅጥር ግዥ ስምምነት ተፈራረመ፡፡ BYUCKSAN Power Construction የተባለው አማካሪ ድርጅት ተቋሙ በደቡባዊ ግሪድ የሚያሰራውን የኢንጂነሪንግ፣ የግዥና ኮንስትራክሽን ሥራ የሚያማክር ነው፡፡ ሥራውን ለማከናወንም የ6 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻና እና የኩባንያው ተወካይ ሚስተር ጅንግ ውን ጅኦንግ ናቸው፡፡ ህዳር 04 ቀን 2012 ዓ/ም

የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማስፈን የአሰሪና ሠራተኛ ግንኙነት ትልቅ ሚና እንዳለው ተጠቆመ …………./////……….. የሠራተኛ ማህበራት የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ከማስከበር ባለፈ የሠራተኛው ማህበራዊ ግንኙነት እንዲጠናከር ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባቸው ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር በኢንዱስትሪ ግጭት መነሻ ምክንያቶችና መከላከያ ዘደዎች ዙሪያ ለአባላቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ስልጠናውን የሰጡት የሀገር አቀፍ የኃይል ማመንጫ፣ ኬሚካልና ማዕድን ሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ዋና ፀኃፊ አቶ ፀሐዬ አክሎክ እንደገለጹት በአሰሪና ሰራተኛ መካከል የሚፈጠር አለመግባባትን ለመከላከልና የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማስፈን ዘመናዊ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት መፍጠር ትልቅ ሚና አለው ብለዋል፡፡ አሰሪዎችና ሠራተኞች ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት ሲሉ አለመግባባት እንደሚከሰት የጠቆሙት አቶ ፀሐዬ በየተቋማት የሚመሰረቱ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበራት ግጭቶችን ለመፍታት ድርሻቸው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ማንኛውም ድርጅት ሆነ የሠራተኛ ማህበር የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማስፈን የሚያግዝ መተዳዳሪያ ደንብ ሊኖራቸውና ተፈፃሚነቱን ሊከታተሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ የሠራተኛ ማህበራት ሲደራጁ ከተፅዕኖ ነፃ በሆነና አንድነትን ባጠናከረ መልኩ መሆን እንዳለበት አንስተዋል፤ ይህም በአሰሪዎች በኩል ተቀባይነት ያለው ማህበር ያደርገዋል ነው ያሉት፡፡ አቶ ፀሐዬ እንዳሉት በየተቋማቱ የሠራተኞችን አንድነትን ለማጠናከርና መብቶቻቸውን በተደራጀ መንገድ ለመጠየቅ ሠራተኞችን በአባልነት ለማቀፍ ማህበራት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል፡፡ የሠራተኛ ማህበራት የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስከበር ከመስራት በተጨማሪ የሠራተኛው ማህበራዊ ግንኙነት እንዲጠናከር እና ማህበራዊ ህይወቱ እንዲሻሻል ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል ነው ያሉት አቶ ፀሐዬ፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ መካከል የሚከሰቱ አለመግባባቶችን ለማስወገድ ላለመግባባቱ መንስኤ የሚሆኑ ነገሮችን መለየትና በውይይት መፍታት እንደሚገባ ዋና ፀሐፊው አስረድተዋል፡፡ እንደ አቶ ፀሐዬ ገለፃ በድርጅቱ እና በሠራተኞች መካከል የሚፈጠሩ የተለያዩ ግጭቶች በድርድር፣ በሁለቱ ተከራካሪ ወገኖች በኩል በሚመረጥ 3ኛ ወገን አስማሚ፣ በአሰሪና ሰራተኛ ወሳኝ ቦርድ እና በህግ አግባብ መፈታት ሊፈቱ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም የኢንዱስትሪ ሠላምን ለማስፈን መንግስት፣ አሠሪዎችና ሠራተኞች የየራሳቸውውን ሚና በአግባቡ እንዲወጡ አቶ ፀሐዬ አሳስበዋል፡፡ ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ፣ በኢንዱስትሪ ግጭቶች መነሻ ምክንያቶችና መከላከያ ዘዴዎች፣ በኢንዱስትሪ ሰላምና ግንኙነት እንዲሁም በግጭት አፈታትና በህብረት ስምምነት ላይ በተመለከተ ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ.ም

የትውውቅ መድረክ ተካሄደ ………../////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ወደተቋሙ ለተቀላቀሉ አዳዲስ የኤሌትሪክ እና የመካኒካል መሐንዲሶች የትውውቅ መድረክ አካሄደ፡፡ በትውውቅ መርሃግብሩ ላይ
+1
የትውውቅ መድረክ ተካሄደ ………../////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ወደተቋሙ ለተቀላቀሉ አዳዲስ የኤሌትሪክ እና የመካኒካል መሐንዲሶች የትውውቅ መድረክ አካሄደ፡፡ በትውውቅ መርሃግብሩ ላይ የተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሣ እንደተናገሩት አዳዲሶቹ መሐንዲሶች በኃይል ማመንጫዎች፣ በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችና የኦፕሬሽን የስራ ክፍሎች የሚመደቡ ናቸው፡፡ ቀደም ሲል በነበሩት ጊዜያት ሠራተኞች ወደ ተቋሙ ሲቀጠሩ በተደራጀ መልኩ በቂ መረጃ ሳያገኙ ወደ ሥራ መግባታቸው ተቋሙ በፍጥነት ለሚጠብቀው ውጤታማነት እንቅፋት እንደሆነባቸው በመገንዘብ የትውውቅ መድረኩ መዘጋጀቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የትውውቅ መርሃግብሩ ዋና ዓላማ የተቋሙን ራዕይ፣ ተልዕኮ እንዲሁም ተቋሙ ሊያሳካ የሚፈልጋቸውን ጉዳዮች፣ አደረጃጀቶች እና አሰራር ተቋሙን ለተቀላቀሉ አዳዲስ ሠራተኞች ለማሳወቅ ነው፡፡ ከሰራተኞቹ የሚጠበቀውን በመለየት በአዕምሮ ዝግጁ ሆነው ወደ ሥራ ለማስገባት እንደሆነ ዶ/ር ወንደሰን ጠቁመዋል፡፡ በጊዮን ሆቴል በተካሄደው መድረክ ላይ የተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ጨምሮ ከፍተኛ የስራ መሪዎች ተገኝተዋል፡፡

የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው ……………..////………….. በኦሞ ወንዝ ላይ እየተገነባ የሚገኘውን የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እየተፋጠነ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ምክትል ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር አባይነህ ጌትነት እንዳሉት ፕሮጀክቱ ከፋይናንስ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች የታሰበውን ያህል በፍጥነት ባይጓዝም ወሳኝ የሚባሉ የተለያዩ ሥራዎች ግን ተሰርተዋል፡፡ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ በግንባታ ሂደት ላይ ለሚገኘው ለዚህ ፕሮጀክት መንግስት ትልቅ ትኩረት በመስጠቱና የሚስተዋሉ ችግሮችን መቅረፍ በመቻሉ በተያዘው መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በአብዛኛው ከግድቡ ግንባታ ጋር የተያያዙ የወንዙን ተፈጥሯዊ አቅጣጫ የማስቀየስ፣ የዋና ግድብና የኃይል ማመንጫ ቤቶች (power houses) ግንባታ የመሰረት ቁፋሮ የተከናወነ ሲሆን የቁፋሮ ስራዎቹ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው የዋናው ግድብ የኃይል ማመንጫ ቤት መሰረት የአርማታ ኮንክሪት RCC ሙሌት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ በአሁን ሰዓት የሠራተኞች መኖሪያ ቤቶችና ቢሮዎች እንዲሁም መንገዶች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ገልፀዋል፡፡ እንደ ምክትል ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የብረታ ብረትና ሜካኒካል ስራዎች በጨረታ ሂደት ላይ ቢሆኑም የግድቡ ውሃ ማስተንፈሻ ቁፋሮ ግን ከሌሎች የሲቪል ስራዎች ጋር ጎን ለጎን እየተከናወነ በመሆኑ ፕሮጀክቱ በተያዘው መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ከጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ተነስቶ ፕሮጀክቱ ድረስ የሚደርስ የ400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ዝርጋታ እና የስዊች ያርድ ግንባታ ከ80 በመቶ በላይ ተጠናቋል፡፡ ለፕሮጀክቱ የተገነባው 80 ኪ.ሜ. የሚሸፍን መንገድ የአካባቢውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ሁለት ወረዳዎችን የሚያገናኝ 170 ሜትር ርዝመት ያለው ድልድይ እንዲሁም የትምህርት ቤቶችና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታና የማስፋፊያ ስራዎች ተከናውነው ለማህበረሰቡ መተላለፋቸውን አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ኃይል ከማመንጨት በተጨማሪ 129 ኪሜ ርዝመት ያለው ሰው ሰራሽ ሀይቅ የሚፈጥር ነው፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ካለው የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ ጋር በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ስራ ከፍተኛ የቱሪዝም ማዕከል በመሆን ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ትልቅ ድርሻ እንደሚያበረክት ይታሰባል፡፡ የኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀከት የማመንጨት አቅሙ 2160 ሜጋ ዋት ሲሆን በዓመት በአማካይ 6460 ጊጋ ዋት ሰዓት እንዲያነጭ ታስቦ እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ነው፡፡ ይህም በማመንጨት አቅሙ በሀገሪቱ ካሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንዲቀመጥ ያስችለዋል፡፡ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታውን የሲቪል ስራ የቀድሞ ሳሊኒ የአሁኑ ዊ ቢዩልድ እያከናወነ ሲሆን ለፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጭ 2 ነጥብ 525 ቢሊየን ዩሮ ተመድቦለታል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 39 በመቶ ደርሷል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ.ም.

የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው
+4
የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለነቢዩ መሀመድ ልደት(መውሊድ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሠላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይመኛል፡፡

ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) ተግባራዊ ለማድረግ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋል ተባለ .....///.…... ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን በተቋሙ ተ
ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) ተግባራዊ ለማድረግ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋል ተባለ .....///.…... ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን በተቋሙ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የሥራ ክፍሎች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሞደርናይዜሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደገለፁት ተቋሙ ያሉትን ሀብቶች በአንድ የመረጃ ቋት ውስጥ መዝግቦ ለማስተዳደር የኢ.አር.ፒ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት በተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ዝግጅት እየተደረገ በመሆኑ በየደረጃው ያሉ የሥራ ክፍሎች በባለቤትነት ስሜት በትብብር ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ የአሰራር ሥርዓቱን ለመተግበር ከሀብት ምዝገባ ጋር የተያያዙ የመረጃ ክፍተቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የጠቆሙት ኃላፊው ችግሩን ለመቅረፍም ሁሉም የሥራ ክፍሎች በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እንደ አቶ ገነቱ ገለፃ ኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓት ሁለንተናዊ የሆነ ተቋማዊ ለውጥ ከማምጣት ባሻገር መረጃዎችን በአግባቡ በመመዝገብ የሀብት ብክነትን ያስቀራል፡፡ ኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓት የፋይናንስና ቁጥጥር፣ የሰው ሀብትና ፔሮል፣ የመረጃ ማዕከል፣ የንብረት አስተዳደርና የዕቃ ግምጃ ቤት እንዲሁም መሰል አስተዳደራዊ ሞጁሎች ያሉት ዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሳፕ ከተባለው የጀርመን ሶፍትዌር አምራች ኩባንያ የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓት ሶፍትዌር ፈቃድ ለመግዛት በሂደት ላይ ይገኛል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 18 ቀን 2013 ዓ.ም.

የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስምምነት ተፈረመ …………….////………………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ኢን
+5
የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስምምነት ተፈረመ …………….////………………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የተሰኘ የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም ተፈራርመዋል፡፡ ሥምምነቱ በዋናነት የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን ከተቋሙ የሥራ ባህሪ አንፃር የመተግበር እና የማዘመን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ሥምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓትን ከሰባት ዓመት በላይ የተገበረውና ውጤታማ አፈፃፀም ያስመዘገበበት በመሆኑ ተቋሙ በቀላሉ ወደ ትግበራ እንዲገባ እና የተሻለ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ ይረዳዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም በበኩላቸው ሁለቱ ተቋማት በርካታ ሥራዎችን በትብብር በመስራት መልካም ግንኙነት መመስረታቸውን ተናግረዋል፡፡ ስምምነት የተፈረመበትን የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስራ በተያዘለት በጀትና ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም.

የአዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ …………./////……….. በአዋሽ ወንዝ ሙላት ሳቢያ በጎርፍ ተጥለቅልቆ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ከነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሞ ነበር፡፡ በወቅቱ ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ ተውጠው እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል። ለሁለት ወራት አካባቢ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው ጣቢያ አንድ ዩኒት ወደስራ ማስገባት በመቻሉ ጣቢያው በከፊል ስራ የጀመረ ሲሆን ቀሪውን አንድ ዩኒት ስራ ለማስጀመር በሂደት ላይ ይገኛል። ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ/ም

ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………………….////……………….. የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክትን የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ግንባታ በማጠናቀቅ
+2
ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………………….////……………….. የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክትን የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ግንባታ በማጠናቀቅ የሙከራና ፍተሻ ሥራ ለመስራት መታቀዱን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጁ አቶ ኢዮሲያስ ኃይለማርያም እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ የማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቤት፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል፣ የመኖሪያ እና የቢሮ ግንባታዎች በመከናወን ላይ ነው፡፡ የግንባታ ስራው ህዳር 2011 ፕሮጀክቱ ለአፍዴራ እና አካባቢው ነዋሪዎች ብሎም ለጨው ማምረቻና የአዮዲን ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ አልሞ የተገነባ ነው፡፡ በአፍዴራ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ የኃይል ትራንስፎርመር እንደሚገጠምለት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በረሃማ በሆነ አካባቢ የሚገኝ ቢሆንም ተቋራጩ ጥልቅ ቁፋሮ በማካሔድ ለግንባታ እና ለመጠጥ የሚያገለግል ውሃ ማቅረቡንና ይህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ሥራ ሲጀምር ለጣቢያው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክት አካል የሆነውና 195 ኪ.ሜ የሚረዝመው የሠመራ-አፍዴራ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም.

EEP Communication - Statistics & analytics of Telegram channel @eepcommuication