en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 543 subscribers, ranking 8 332 in the Technologies & Applications category and 2 157 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 543 subscribers.

According to the latest data from 27 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by -16 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.06%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.33% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 895 views. Within the first day, a publication typically gains 2 539 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 7.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“EEP Communication”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 543
Subscribers
-1624 hours
-97 days
+1030 days
Posts Archive
የኃይል መቆራረጥን በዘላቂነት ለመቅረፍ በቅንጅት እየተሰራ ነው ……//…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን ከትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽ/ቤት ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር የኃይል መቆራረጥን በዘላቂነት ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገብረ እግዚአብሔር እንደገለጹት ሪጅኑ ሁለት ደንበኞች ያሉት ሲሆን እነሱም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው፡፡ ሁለቱ ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት ተያያዥነት ያለው በመሆኑ በከፍተኛ አመራሮቻቸው በኩል የጋራ መድረክ እንዳላቸው የገለጹት አቶ ሮቤል ሪጅኑ ባለው አቅም የሚሰጠው አገልግሎት የደንበኞቹን እርካታ የሚያሳድግና የህብረተሰቡን ፍላጎት ያማከለ እንዲሆን በጋራ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ እንደ አቶ ሮቤል ገለጻ በክልሉ ያለውን የኃይል መቆራረጥ በዘላቂነት በመቅረፍ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር ተቋማቱ ያላቸውን የሰው ኃይል፣ ሀብትና ቁሳቁስ በማቀናጀት እና የጋራ መድረኮችን በመፍጠር እየሰሩ ነው፡፡ የትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽ/ቤት ሥራ አሥፈጻሚ አቶ መስፍን ገብረ መድህን በበኩላቸው በክልሉ በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በደረሰ ጉዳት እና የማሰራጫ መስመሮች ኔትወርክ በማርጀቱ የኃይል መቆራረጥ መኖሩን ተናግረዋል፡፡ የኃይል መቆራረጡን በዘላቂነት ለመቅረፍና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ የኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግር ካጋጠመ ህብረተሰቡን በአግባቡ ማገልገል ስለማይቻል ተቋማቱ ያላቸውን ሀብት አቀናጅተው በመጠቀም የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 09 ቀን 2016 ዓ.ም Facebook Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

photo content
+3

ለጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው .........//........ ለጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተከዜ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አስታወቀ፡፡ የጣቢያው የሰው ኃይል፣ ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ መኮንን ገ/ሊባኖስ እንደተናገሩት የጣቢያው ሠራተኛ ምቹ የሥራ ከባቢ ተፈጥሮለት ሥራውን ተረጋግቶ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያከናውን የተለያዩ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ሠራተኛው አገልግሎት የሚያገኝበት እንዲሁም አቅሙን የሚያጎለብትበት የአሰራር ሥርዓት እየዘረጋን ነው የሚሉት ኃላፊው ለሠራተኛውና ለልጆቹ የሚሆን የመዋኛ ገንዳ፣ የዲ ኤስ ቲቪ አገልግሎት እና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮችን መፈጠሩን ተናግረዋል። ከወረዳው ትምህርት ቢሮ ጋር በመነጋገርና ፍቃድ በማውጣት የሠራተኛው ልጆች የሚማሩበት ከኬጂ እስከ 4ኛ ክፍል የሚያስተምር ትምህርት ቤት በጣቢያው ተከፍቶ በማስተማር ላይ መሆኑን አቶ መኮንን ገልጸዋል። የትምህርት ቤቱን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል ዕቅድ ተዘጋጅቶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ ከ4ኛ ክፍል በላይ ለሆኑትና ሲቦኩ ከተማ ሄደው ለሚማሩት የሠራተኛው ልጆች በትምህርት መግቢያና መውጫ ሰዓት የሰርቪስ አገልግሎት በመሰጠት ላይ መሆኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል ከኃይል ማመንጫ ቤት እስከ ሠራተኛ መኖሪያ ያለውን 9 ኪሎ ሜትር መንገድ የኮንክሪት አስፓልት ለማድረግ የሚያስችል ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል። የጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ ተፈጥሮላቸው ተረጋግተ ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲያከናውን የሚያስችሉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ መኮንን አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 09 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ ሥራ ከ12 በመቶ በላይ ደርሷል ………////…… የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአርባ ምንጭ 2ኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ግንባታ ሥራ 12 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን በፕሮጀክቱ የሳይት 1 ሥራ አስኪያጂ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አንዱአለም መላኩ እንደተናገሩት የአርባ ምንጭ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ሺግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ኃይል ለመቀበልና ለመስጠት (LILO) ከሚዘረጋው መስመር ላይ በመቀጠል ኃይል ያገኛል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 125፣ ሁለት ባለ 63 እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች፤ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር ገቢ መስመር እንዲሁም አንድ ባለ 132፣ 10 ባለ 33 እና 5 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እንደሚኖሩት አቶ አንዱአለም አስረድተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የጣቢያው የመሬት ቁፋሮና ቆረጣ ሥራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን የመሬት ሙሌት 69 በመቶ፣ የዲዛይን ሥራ 92 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የማምረት ሥራ 58 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍል እና የትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ የመሰረት ቁፋሮ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ያነሱት ሥራ አስኪያጁ የታችኛው የመሰረት ኮንክሬት (pad) ሙሌት እና ብረት የማቆም ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ የግንባታ ሥራው ህዳር 2016 ዓ.ም የተጀመረው የአርባ ምንጭ ማከፋፈያ ጣቢያ አጠቃላይ የሲቪል ግንባታ ሥራ 12 ነጥብ 5 በመቶ ላይ መድረሱን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል ፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ለ50 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ጠቁመዋል። ከ37 ነጥብ 09 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት እየተገነባ የሚገኘው የአርባ ምንጭ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ሲጠናቀቅ በአካባቢው ሊገነባ ለታቀደው የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ አስተማማኝ እና በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የአርባ ምንጭ ቁጥር 2፣ የሺግዳንና ቲርጋ የአዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን፣ የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 እና አርባ ምንጭ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የማስፋፊያ እንዲሁም የ424 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ ከ178 ነጥብ 27 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት እየተከናወነ የሚገኘው የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ሀዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን (Hyosung heavy industries corporation) በተሰኘ የደቡብ ኮሪያ ኩባንያ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ሥራው ላይ ደግሞ ባዩክሰን ፓወር (Byucksan power co.ltd) የተሰኘ ኩባንያ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ ሥራ ከ12 በመቶ በላይ ደርሷል ………////…… የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአርባ ምንጭ 2ኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ግንባታ ሥራ 12 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን በፕሮጀክቱ የሳይት 1 ሥራ አስኪያጂ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አንዱአለም መላኩ እንደተናገሩት የአርባ ምንጭ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ሺግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ኃይል ለመቀበልና ለመስጠት (LILO) ከሚዘረጋው መስመር ላይ በመቀጠል ኃይል ያገኛል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 125፣ ሁለት ባለ 63 እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች፤ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር ገቢ መስመር እንዲሁም አንድ ባለ 132፣ 10 ባለ 33 እና 5 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እንደሚኖሩት አቶ አንዱአለም አስረድተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የጣቢያው የመሬት ቁፋሮና ቆረጣ ሥራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን የመሬት ሙሌት 69 በመቶ፣ የዲዛይን ሥራ 92 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የማምረት ሥራ 58 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍል እና የትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ የመሰረት ቁፋሮ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ያነሱት ሥራ አስኪያጁ የታችኛው የመሰረት ኮንክሬት (pad) ሙሌት እና ብረት የማቆም ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ የግንባታ ሥራው ህዳር 2016 ዓ.ም የተጀመረው የአርባ ምንጭ ማከፋፈያ ጣቢያ አጠቃላይ የሲቪል ግንባታ ሥራ 12 ነጥብ 5 በመቶ ላይ መድረሱን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል ፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ለ50 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ጠቁመዋል። ከ37 ነጥብ 09 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት እየተገነባ የሚገኘው የአርባ ምንጭ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ሲጠናቀቅ በአካባቢው ሊገነባ ለታቀደው የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ አስተማማኝ እና በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የአርባ ምንጭ ቁጥር 2፣ የሺግዳንና ቲርጋ የአዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን፣ የወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 እና አርባ ምንጭ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የማስፋፊያ እንዲሁም የ424 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ ከ178 ነጥብ 27 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት እየተከናወነ የሚገኘው የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ሀዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን (Hyosung heavy industries corporation) በተሰኘ የደቡብ ኮሪያ ኩባንያ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ሥራው ላይ ደግሞ ባዩክሰን ፓወር (Byucksan power co.ltd) የተሰኘ ኩባንያ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 08 ቀን 2016 ዓ.ም

ሪጂኑ መስመሩን ከጎርፍ አደጋ ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየሠራ ነው ……///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 2 ሪጂን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የኢትዮ- ኬንያ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በተፈጥሮ አደጋዎች ጉዳት እንዳይደርስበት የቅድመ መከላከል ሥራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ፋይበር ኦፕቲክስ ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉብርሃን ሐዱሽ እንዳስታወቁት የተወሰኑ የመስመሩ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እንደሆኑ በተካሄዱ የፍተሻ ሥራዎች ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ምሰሶዎቹ በጎርፍ ከመጎዳታቸው በፊት መከላከል የሚያስችሉ የቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍበት የጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሼሌ መሌ ቀበሌ አካባቢ የጎርፍ ስጋት የተጋረጠበትን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ከመውደቅ ለመከላከል የሚያስችል የአፈር መሸርሸር መከላከያና የጎርፍ ማስቀየሻ ግንብ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አቶ ሙሉብርሃን ተናግረዋል፡፡ ምሰሶው ሲተከል ከወንዙ ከ35 ሜትር በላይ ርቀት የነበረው ቢሆንም በአካባቢው ከጥቅምት 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባጋጠመ ከፍተኛ ጎርፍ ምክንያት በአሁኑ ወቅት ከወንዙ ያለው ርቀት ከ3 እስከ 4 ሜትር ብቻ እንደሆነ ነው የጠቆሙት፡፡ በአካባቢው ያለው አፈር ልል በመሆኑ ችግሩ አሁን ካለበት ቦታ ላይ በፍጥነት ሊደርስ እንደቻለ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ በአካባቢው ዝናብ ቶሎ ባለማቋረጡ ምክንያት ችግሩን በወቅቱ መቅረፍ አልተቻለም ብለዋል፡፡ መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ.ም የተጀመረው ይህ ሥራ አስፈላጊው ጥናት እና ዲዛይን ተሰርቶለት በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በሥራው ላይም 87 ሜትር ርዝመትና 5 ሜትር ቁመት ያለው የአፈር መከላከያ ግንብ ሥራ በሪጂኑ አቅም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ አሁን እየተከናወነ ካለው ሥራ በተጨማሪ በመስመሩ ላይ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ተጨማሪ አራት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች መለየታቸውን እና ችግሩ ሳይሰፋ ቀድሞ ለመከላከል የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

+2
2.jpg0.91 KB

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ መሪነቱን የሚያጠናክርበት ድል አስመዝግቧል ………////……… ትናንት በተከናወነው 20ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ጅማ አባ ቡናን ሁለት ለባዶ በመርታት ግስጋሴውን አሳምሯል። የማሸነፊያ ጎሎቹን የአጥቂ መስመር ተጫዋቾቹ አቤል ሀብታሙ እና ልዑልሰገድ አስፋው በ11ኛው እና በ14ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የጨዋታ ብልጫ ወስዶ ባጠናቀቀው በዚህ መርሐ ግብር ጅማ አባ ቡናዎች አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃት ግብ ለማስቆጠር ጥረት ከማድረጋቸው በስተቀር የጎላ እንቅስቃሴ ማሳየት አልቻሉም። በዕለቱ አንድ ጎል ያስቆጠረው እና ጥሩ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው ልዑልሰገድ አስፋው ኮከብ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል። መርሐ ግብሩ ሊጠናቀቅ ስድስት ጨዋታዎች ብቻ በቀሩት የከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ46 ነጥብ ሊጉን ሲመራ ዛሬ ተስተካካይ ጨዋታውን የሚያከናውነው ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በ35 ነጥብ ሁለተኛ ሆኖ ይከተላል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ሚያዚያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከተከታዩ ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ክለብ ጋር ወሳኙን ፍልሚያ የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ጣቢያው በራስ አቅም ባከናወናቸው የጥገና ሥራዎች ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድኗል .........///…...... የጊቤ II የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ አቅም በ3 የማመንጫ ዩኒቶች ውስጥ በሚገኙ የውሃ መቆጣጠሪያ ኖዝሎች ላይ ባከናወናቸው የጥገና ሥራዎች ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳኑን የጣቢያው ሼል አስኪያጅ አስታወቁ። ሼል አስኪያጁ አቶ ሹመት በላቸው እንደገለፁት የኃይል ማመንጫው ካሉት 4 ዩኒቶች ውስጥ በ3ቱ ላይ የጥገና ሥራው ተከናውኗል። ወደ ተርባይን የሚገባውን የውሃ መጠን ለመቆጣጠር በሚያገለግሉት ሹል ጫፎች ያላቸው የብረት ኖዝሌች በመበላታቸው በመዝጊያው በኩል ዘይት ማፍሰስ ጀምሮ እንደነበር ጠቁመዋል። በ3ቱ የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች ውስጥ በሚገኙት የውሃ መቆጣጠሪያ ኖዝሎች ላይ በተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የጣቢያውን የማመንጨት አቅም ዳግም ከፍ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል። የውሃ መቆጣጠሪያ ኖዝሎቹ ተጠግነው ወደ ሼል መግባታቸው ይስተዋል የነበረውን የውሃ አጠቃቀም ችግር ከመቅረፉ ባሻገር ዩኒቶቹ ወደ ሲስተም የሚገቡበትን ጊዜ ማሳጠሩን ሼል አስኪያጁ ጠቁመዋል። እንደ አቶ ሹመት ገለፃ በአሁኑ ወቅት ጥገና የተከናወነላቸው 3ቱ ዩኒቶች በሙሉ አቅማቸው የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጩ ነው። በቀረው አንድ ዩኒት ላይ ጥገና ለማከናወን የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል። የኖዝል የጥገና ሥራው በውጭ ኩባንያዎች ቢከናወን ኖሮ ጉዳት የደረሰባቸውን ዕቃዎች ከመጠገን ይልቅ ወደ መቀየር ሊገባ ይችል እንደነበር የጠቀሱት ሼል አስኪያጁ ይህም ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ ይዳርገው እንደነበር ገልፀዋል። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከጊዜ ወደ ጊዜ በራስ አቅም እየተከናወኑ የሚገኙ የጥገና ሥራዎች እየጨመሩ መምጣታቸውን አቶ ሹመት áŠ áˆ˜áˆáŠ­á‰°á‹‹áˆá˘ በማመንጫ ጣቢያው አጠቃላይ የጥገና እና የኦፕሬሽን ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዙ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች መጀመራቸውንም ሼል አስኪያጁ አብራርተዋል። የዲጂታላይዜሽን ሥራዎቹ የጣቢያውን የጥገናና የኦፕሬሽን ሂደቶች በመከታተልና ያጋጠሙ ችግሮችን በፍጥነት በመለየት ለመፍታት የማይተካ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የእኔነት ስሜትን የሚያሳድጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው ………///……… በተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉና በጣቢያው ላይ የእኔነት ስሜት እንዲኖራቸው የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን በጣቢያው የሰው ኃይል፣ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ መኮንን ገ/ሊባኖስ እንደገለጹት ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው። በግድቡ ዙሪያ የሚገኙትን የሲቦኩ ከተማና ሁለት የገጠር ቀበሌዎች ጣቢያው የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረጉን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። እንደ አቶ መኮንን ገለፃ በግድቡ በፈጠረው ሠው ሰራሽ ሀይቅ ዓሳ በማስገር ሥራ ለተሰማሩ ሰባት ማህበራት የመስሪያ ቤት፣ የመብራትና የመጠጥ ውሃ በነፃ እያቀረበ ነው። ሰባቱ ማህበራት እያንዳንዳቸወ ከ30 እስከ 50 አባላት እንዳሏቸው የገለጹት ሥራ አስኪያጁ ማህበራቱ በየዓመቱ ለተጨማሪ 50 ወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥሩበት አሰራር መዘርጋቱንም ተናግረዋል። በተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ዓሳ በማስገር ሥራ ላይ የተሰማሩት አቶ ገረሴ ግደይ እንደገለጹት ጣቢያው ባመቻቸላቸው ዕድል በማህበር ተደራጅተው ዓሳ ማስገር ከጀመሩ አስር ዓመት አልፏቸዋል። በዚሁ ሥራ በሚያገኙት ገቢ በከተማ ቤት እንደሰሩና ሰባት ልጆቻቸውን እንደሚያስተዳድሩ በመግለጽ ማህበራቸው ፍሪጆችንና ጀልባዎችን በመግዛት ሥራቸውን እያሰፉ መሆኑንም አብራርተዋል። ጣቢያው ባሰራው ቧንቧ ውሃ ሲቀዱ ያገኘናቸው ወ/ሮ ትብራ ብርሃኑ በበኩላቸው ከአሁን ቀደም ንጹህ የመጠጥ ውኃ ለማግኘት ሲሉ ረጅም ርቀት ይጓዙ እንደነበር ገልጸዋል። ጣቢያው ቧንቧ ካሰራላቸው ወዲህ ግን ንጹህ የመጠጥ ውኃ በአቅራቢያ ከማግኘታቸውም ባለፈ ለእንስሳዎቻቸው መጠጥና ለመስኖ አገልግሎት ጭምር በማዋል ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን ተናግረዋል። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በአካባቢው እያከናወነ ላለው የልማት ስራ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ማህበረሰቡ በጣቢያው ላይ ያለው የባለቤትነት ስሜት እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል። ከኃይል ማመንጫ ግቢው እስከ ሲቦኩ ከተማ ያለውን መንገድ በኮንክሪት አስፓልት ደረጃ ለመስራት በሂደት ላይ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው ጣቢያው የእኔነትን ስሜት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎችን በመስራት ማህበራዊ ኃላፊነት መወጣቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ በከፍተኛና መካከለኛ አመራር ልማት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በተመከተ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሰራው ዘገባ ተከታዩ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” https://www.facebook.com/share/v/cjv5NBaqnJFKtuqQ/?mibextid=oFDknk

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ለቀጣናዊ የኃይል ትስስር አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ……….///……….. የኢትዮ-ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር አስተማማኝ ኃይል እንዲያስተላልፍ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 2 ሪጂን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመሮችና የፋይበር ኦፕቲክስ ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉብርሃን ሐዱሽ እንዳስታወቁት የተጀመረውን ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣት ሪጂኑ ከሚያስተዳድራቸው ሌሎች መስመሮች በተለየ መልኩ ለኢትዮ-ኬንያ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የቅርብ ክትትል ይደረግለታል፡፡ መስመሩ በሠው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ኃይል ማስተላለፍ እንዳያቋርጥ ለማድረግ ከመደበኛ የፍተሻና የጥገና ሥራዎች በተጨማሪ የድንገተኛ ፍተሻዎች እንደሚከናወኑም አስታውቀዋል፡፡ ለዚህም በመስመሩ ላይ ብቻ የፍተሻና የጥገና ሥራዎችን የሚያከናውን ቡድን ተዋቅሮ እየሰራ እንደሚገኝ ነው አቶ ሙሉብርሃን የተናገሩት፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት በፍተሻ ሥራው ለጎርፍ አደጋና ለሥርቆት ተጋላጭ የሆኑ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተለይተው የተለያዩ የቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከቅድመ መከላከል ሥራዎች በተጨማሪ ስርቆት የተፈፀመባቸውን ምሶሶዎች በመከታተል የጥገና ሥራዎች በወቅቱ እየተከናወኑ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ የፍተሻ ሥራዎቹ መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ከማቋረጡ በፊት የገጠሙትን ችግሮች በወቅቱ ለማስተካከል እንደሚያግዙ አቶ ሙሉብርሃን አንስተዋል፡፡ የኢትዮ - ኬንያ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር 1 ሺ 66 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይሸፍናል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2