en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 537 subscribers, ranking 8 329 in the Technologies & Applications category and 2 179 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 537 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 31 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.36%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 097 views. Within the first day, a publication typically gains 2 520 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 537
Subscribers
-124 hours
-167 days
+3130 days
Posts Archive
ተቋሙ በአማራ ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረገ ........////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአማራ ክልል አሸባሪው ህወኃት በፈፀመው ወረራ ለተፈናቀ
ተቋሙ በአማራ ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረገ ........////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአማራ ክልል አሸባሪው ህወኃት በፈፀመው ወረራ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉን ለአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ዛሬ ያስረከቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ናቸው። በርክክብ ሥነስርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጦርነቱ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከመጠገን በተጓዳኝ 4 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ደግሞ የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። ተቋሙ ሠራተኞቹን በማስተባበር ያደረገው የዓይነት ድጋፍ የህፃናት አልሚ ምግብ፣ የምግብ ዘይት፣መኮረኒ፣ ዱቄት፣ አልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሶችን ያካተተ ነው። የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘላለም ልጃለም በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ እንደገለፁት የሽብር ቡድኑ ወረራ ፈፅሞባቸው በነበሩ አካባቢዎች በርካታ ዜጎች የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2014 ዓ/ም

የሐረር ከተማና አካባቢውን የኃይል እጥረት የሚቀርፍ ስራ ተጀመረ ........///........ በሐረር ከተማና አካባቢው የነበረውን የኃይል እጥረት ሙሉ በሙሉ የሚቀርፍ ስራ መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን የምስራቅ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳስታወቁት ያለፉት ሁለት ዓመታት የሐረር ከተማና አካባቢው ከፍተኛ የኃይል እጥረት አጋጥሞት ነበረ። ችግሩንም ለመቅረፍ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ጊዜያዊና ቋሚ መፍትሄዎች እየተነደፉ ሲተገበሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ የኃይል እጥረቱ ብቸኛ መንስኤ የፓወር ትራንስፎርመሮች ከአቅም በላይ የኃይል ጭነት በመሸከማቸው ነው። ይህንንም ለመቅረፍ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል በከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር የሆነ ትራንስፎርመር ግዢ ተፈፅሞ ትራንስፎርመሩ ሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ያለምንም ችግር እንዲቀመጥ ተደርጓል ብለዋል። የፓወር ትራንስፎርመሩን ተከላ በቀጣዮቹ ሀገራት ሦስት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን የገለፁት አቶ ጋሻው ተከላው ሲጠናቀቅ የሐረሪ ብሔራዊ ክልል ከተሞችንና እንደ አወዳይ እና ኮምቦልቻ ያሉ የምስራቅ ሐረርጌ ከተሞችን የኃይል እጥረት ሙሉ በሙሉ እንደሚቀርፍ አስታውቀዋል። የትራንስፎርመሩን ተከላ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላትና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 19 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

#News update እስከ ጋሸና ያሉት ከተሞች ኤሌክትሪክ አግኝተዋል።

በሲል መበላት ምክንያት ተከስቶ ለነበረው የፖውር ኖዝል ችግርን ለማስተካከል የተከናወነውም ተግባር ፓወር ኖዝሎች ማውረድና መፍታት ነው፡፡ በዚህም መሰረት በዩኒት አንድ ላይ ብቻ ስድስት (6) ፓወር ኖዝሎች (needle valves) ያሉ ሲሆን እያንዳንዳቸውም 6000 ኪ.ግ የመመዘን ክብደት ያላቸው ናቸው፡፡ ስለሆነም ስድስቱንም ፓወር ኖዝሎች (needle valves) በሠው ኃይልና በአንዳንድ ማሽነሪዎች አማካኝነት በማውረድ፣ የመፈታታት፣ የማፅዳት እና የመቀየር እንዲሁም የመግጠም ስራ እንደተሰራ የጥገና ቡድኑ አባላት በአንድነት ያወሳሉ፡፡ ከፖወር ኖዝል ጥገና ጎን ለጎን Main inlet valve (MIV servomotor) መሳሪያዎች ጥገና ተከናወኗል፡፡ MIV servomotor ማለት ወደ ተርባይን የሚገባውን ውሃ ለመቆጣጠር የሚያገለግሉ መሳሪያዎች ናቸው፡፡ ይህም መሳሪያ በመዝጊያው በኩል የዘይት መፍሰስ ችግር መኖሩን በመረጋገጡ በዩኒት አንድ ላይ ሁለት እንዲሁም በዩኒት ሦስት ላይ አንድ በድምሩ ሦስት (MIV servomotor) የጥገና ስራዎች በመከናወናቸው ዜሮ የነበረውን የዩኒት አንድ የመጫን አቅም ወደ 105 ሜ.ዋ እንዲሁም 25 ሜ.ዋ ብቻ ይጭን የነበረውን ዩኒት ሦስት ወደ 100 ሜ.ዋ ኃይል እንዲያመነጭ በመደረጉ ጣቢያው 180 ተጨማሪ ኃይል እንዲያገኝ ማስቻሉንና በቀጣይም ይህን መሠል ስራዎች በዩኒት ሁለትና አራት ላይ የሚሰራ መሆኑን ለመረዳት ችለናል፡፡ ጣቢያውን ለማዘመን እየተሰሩ ካሉ ስራዎች ውስጥ አንዱ የኃይል ጭነትን ለማስተካከል የሚረዳውን የርቀት መቆጣጠሪያ ነው፡፡ ይህም ሲባል በፖወር ትራንሲደርሱ ላይ printed circuit board (PCB) የሞስፌት ብልሽት በማጋጠሙ ለረጅም ጊዜ በማኑዋል ይሰራ የነበረውን የኃይል ጭነትን በመስተካከሉ በቀላሉ ከፖወር ሀውስ ሆኖ መቆጣጠር በመቻሉ ከባድ የነበረውን ሥራ ቀላል እንዲሆን አስችሏል፡፡ በተጨማሪም ማሽኑ ያለበትን ችግር በድምፅ ለመለየት የሚያስችል የድምፅ መቅጃ (sound recorderr) ተገጥሞ በመሰራት ላይ እንደሆነም አጫውተውናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በምስራቅ አፍሪካ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት (Voith) አማካኝነት በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች የጥገና ማኔጀመንት ስርዓት (maintenance management system) ስራዎች እየተሰራ መሆኑን የጥገና ቡድኑ አባላት አጫውተውናል፡፡ እንግዲህ እኛም በነበረን ቆይታ እንዲህ ዓይነቱን ተስፋ ሰጭ የወገን እጆች ሥራን ስልንመለከት የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ተቋሙ ለውጭ ሙያተኞችና ኩባንያዎች በሚሊየን ሊያወጣ የሚችለውን ውጭ ማስቀረት ከማስቻሉ በተጨማሪ ቅንጅታዊ አሰራር እና የእውቀት ሽግግር የተገኘበት መሆኑ፣ በተለይም የሙያተኞች የራስ መተማመን ስሜት እንዲጨምር የተደረገበት የበላይ አመራር አዎንታዊ ድጋፍና ክትትል እየተጠናከረ መምጣቱ፣ ተቋማችን በረጅም ጊዜ እደርስበታለሁ ብሎ ከሚያስበው ራዕይ በቶሎ ለመድረስ ከማስቻሉም በተጨማሪ ሀገሪቷ ለምታከናወነው ሁለንተናዊ ልማት መምጣት በየተቋማቱ እነዚህን መሰል እጆች መኖራቸውን አመላካች መሆንን ያስገነዝበናል፡፡ ወድ የገፃችን ተከታታዮች ሁላችንም በየተሰማራንበት የሙያ ዘርፍ በአቅማችን ልክ ከሠራን የማናስመዘግበው ውጤት የለምና በርቱ እንበርታ በማለት ለሀገራዊ ዕድገት የበኩላቸውን ጠጠር ሲወረውሩ የተመለከትናቸው እጆች በጊቤ ሁለት ኃይል ማንጫ ጣቢያ ያከናወኑትን ተስፋ ሰጪ ስራዎች በሁለት ክፍል ያስቃኘናችሁን ፅሁፍ በዚሁ አጠናቀቅን በሌላ ጽሁፍ እስከምንገናኝ ቸር እንሰንብት!!

ጠጠር ወርዋሪ እጆች ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት መፋጠን ከፍተኛ ሚና ከሚጫወቱ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ የኃይል ልማት ዘርፍ አንዱ ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ለኃይል ልማቱ አመቺ የሆኑ ባለ ብዙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶች ባለቤት እንደሆነች ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም ቀደም ሲል ከውኃ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ከንፋስና ከተርማል ኃይልን በማመንጨትና በማቅረብ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ ሲወጣ የቆየ መንግስታዊ የልማት ተቋም ነው፡፡ ሀገሪቱ ለተለመቻቸውን በርካታ የልማት ግቦች እውን መሆን በቂና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የሚጠበቅበትን ሀገራዊ አደራ በብቃት ለመወጣት ተቋሙ ከተለያዩ ታዳሽ ኃይሎች ማለትም ከጆኦተርማልና ከፀኃይ ኃይል ማመንጨት የሚያስችሉ የተለያዩ የአሰራር ስርዓቶችን ዘርግቶ የኃይል ስብጥሩን ለማስፋት ከመቼውም በተሻለ በመትጋት ላይ ይገኛል፡፡ ተቋሙ ከአዳዲስ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች በተጨማሪ በስራ ላይ ያሉ ነባር ኃይል ማመንጫዎችን በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው፡፡ ከእነዚህም ስራዎች መካከል በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ቆመው የነበሩ ዩኒቶችን በራስ አቅም ጠግኖ ወደ ሥራ ማስገባትና በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚጠበቀውን የኃይል አቅርቦት በቂና አስተማማኝ ማድረግ አንዱ ነው፡፡ ለዚህም መሰል ዓላማ እውን ለማድረግ ደግሞ የውጭ ሀገር ሙያተኞችን መተካት የሚያስችሉ የራስ አቅም የጥገና ሙያተኞችን ማፍራት ቀዳሚው ተግባር ነው፡፡ ይህን ዓላማ መነሻ በማድረግ ከተቋማችን የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ ሙያተኞች በተለይም የክላስተር ቢሮዎች፣ የቴክኒክ ሰፖርት እና የኃይል ማመንጫዎች ጣቢያ ሠራተኞች በጊቤ ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ያከናወኑትን አኩሪና ተስፋ ሰጭ ስራዎችን ማከናወን ችለዋል፡፡ ውድ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ገፅ ተከታታዮች በዛሬው ፅሁፋችን ከላይ ባነሳነው ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ በወርሃ ነሐሴ በዘመነ ማርቆስ 2013 ዓመተ ምህረት ወደ ስፍራው ተጉዘን በጊቤ ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለሀገራዊ ዕድገት ስኬት የበኩላቸውን ጠጠር ሲወረውሩ የተመለከትናቸው የጥገና እጆች ያከናወኑትን እና በምስራቅ አፍሪካ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት (Voith hydro Addis Ababa) አማካኝነት ጣቢያውን ማዘመን እንዲያስችል በመከናወን ላይ ስላሉት የጥገና ማኔጀመንት ስርዓት (maintenance management system) ስራዎች ዙሪያ እንሚከተለው ልናስቀኛችሁ ወደድን፡፡ መልካም ንባብ!!!! የጊቤ ሁለት ኃይል ማንጫ ጣቢያ ከአዲስ አበባ በ250 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሠቦች እና ህዝቦች ክልል በየም ልዩ ወረዳ የሚገኝ ሲሆን 420 ሜጋዋት የማመንጨት አቅም ያለው የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው፡፡ ተቋሙ ካሉት 14 የውኃ ኃይል ማመንጫዎች ውስጥ የጊቤ ሁለት የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች አንዱ ነው፡፡ የጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃይል እንዲያመነጭ የሚያስችለውን ውሃ የሚያገኘው 180 ሜ.ዋ አመንጭቶ የሚወጣውን የጊቤ አንድ ውኃ ነው፡፡ ይህም ከጊቤ አንድ ኃይል አመንጭቶ ከወጣ በኋላ በቅርብ ርቀት በተሰራው መለስተኛ ግድብ (Weir) ውኃው እንዲያዝ ከተደረገ በኋላ ወደ ጊቤ 2 በመሬት ውስጥ በሚያልፍ ዋሻ (under groun tunnel) አማካኝነት ነው፡፡ ይህ ዋሻ በኮንክሪት እና በብረት (concrete & steel) የተሰራ ሲሆን 26 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና 3.6 ዲያሜትር ስፋት አለው፡፡ ዋሻው ከመሬት ከወጣ በኋላም ከብረት በተሰሩ 1.3 ኪ.ሜ ርዝመትና 2.1 ዲያሜትር ስፋት ባላቸው ሁለት አሸንዳ (Penstock) ከተጓዘ በኋላ እያንዳንዱ አሸንዳ እንደገና ለሁለት በመከፈል ለአራቱም ዩኒቶች ውኃ እንዲደርስ የሚያደርግ የኃይል ማመንጫ ነው፡፡ ይህ ጣቢያ በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ኃይል የማመንጨት ሥራውን በስኬት ሲወጣ እንደነበርና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳድ ችግሮች ምክንያት አንደኛው ዩኒት ሙሉ ለሙሉ ሲያቆም ሌላኛው ኃይል ማምረት ከሚጠበቀቅበት 1/4ኛውን ብቻ በማምረቱ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ እንዳያመርት እንቅፋት ፈጥሮበት ቆይቷል፡፡ በዚህም መነሻነት ወደ ስፍራው ተጉዘን በነበረበት ወቅት በጣቢያው እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ሲመለከቱ ከፍተኛ ኩራትን ከማላበሱ በላይ እነዚህ አስገራሚና አስደማሚ አገር በቀል እጆች የነገይቱን ኢትዮጵያ በብሩህ ተስፋ መነፅር እንድንመለከት የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እነዚህ የነገይቱን ኢትዮጵያ የሚያመለክቱ እጆች ላሳዩን አስደማሚ ስራ የጣቢያው ኃላፊ የሆኑትን አቶ ሀብታሙ ገረመው እና የጥገና ቡድኑ አባላቱ የስራውን መነሻና መድረሻ ምን ይመስል እንደነበር? እንዲያወጉልን በጠየቅናቸው መሠረት ያጫወቱንን ጨዋታ እንደሚከተለው ሰንደን አቅርበንዋል፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚጠበቅባቸውን ኃይል የማምረት ተግባር በአግባቡ ማከናወን ካልተቻሉ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ በኩል የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዳይወጣ የሚያደርገው ነው፡፡ ስለሆነም ይህንና መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ እንዲያስችል ለምን ሥራውን ቅድሚያ እኛ አንጀምረውም? ለምንስ ሁሌም በውጭ ሀገር ሙያተኞች እንዲሰራ እናደርጋለልን? ለምን በራስ አቅም ችግሩን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት ለምን አንሞክርም? በሚል ሃሳብ ላይ ውይይት ከተደረገ በኋላ በጉዳዩ ተግባብተንበት እና ከፍተኛ ተነሳሽነትን ይዘን ሥራውን ለማከናወን ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን ነግረውናል፡፡ በተለይም ዩኒቶቹ አገልግሎት እንዳይሰጡ ያደረጋቸው ችግር ምን ሊሆን ይችላል? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ የመጀመሪያው ስራ የነበረው በሁሉንም ዓይነቶች ማለትም በሃይድሮሊክ፣ ሜካኒካልና ኤሌክትሪካከል ሥራዎች ችግሮቻቸውን የመለየት (Trouble-shooting) ስራን እንደነበርና ችግሩም በሃይድሮሊክ በኩል በዩኒት አንድና ሦስት ላይ በሲል መበላት ምክንያት የተከሰተ የፖወር ኖዝል ብልሽት ነበር፡፡ ፓወር ኖዝል (needle valve) ሲባል ዩኒቶቹ እንደመጫን አቅማቸው ውሀን ለመመጠን የሚያገለግል የውሃ መቆጣጠሪያ አካል ነው፡፡ የችግሮቹን ዓይነትና ስፋት በጥልቀት ከተለዩ በኋላ ጉዳዩን ለተቋሙ የበላይ ኃላፊዎች ማሳወቃቸውን እና ጥገናውን በራስ አቅም ማከናወን እንዲቻል ከበላይ ኃላፊች ፈቃድ እንዲሰጣቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን እና የተቋሙ የበላይ አመራርም የቀረበውን ጥያቄ በመቀበልና በማበረታታት ለሚፈልጓቸው ሌሎች የድጋፍ ጥያቄዎች በሙሉ ትብብር እንደሚደርጉላቸው በማሳወቃቸው የጥገና ቡድኑ በልዩ ተነሳሽነት ወደ ጥገና ሥራ እንዲገባ አስችሎታል ይላሉ፡፡ ወደ ጥገና ሥራም ከመገባቱ በፊት በቅድሚያ ለጥገና ሥራው የሚስፈልጉ የተለያዩ ሰነዶችን፣ ከሌሎች ሥራ ክፍሎችና ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሙያተኞችንና ማቴሪያሎችን የማሰባሰብ ስራዎችን የማከናወን ስራ ሠራን ሲሉ መሰራቱን ያወሳሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ የተቋሙን ማኔጀመንት አባላት እና የጄነሬሽን ኦፕሬሽን ጽ/ቤት አመራሮች በእኛ ላይ ከፍተኛ እምነት አሳድሮ ጥገናውን እንድናከናውን ፈቃድ በመስጠቱ እና በየጊዜው አስፈላጊ ድጋፎችን በማድረጋቸው ከልብ የሆነ ምስጋናችን ይድረሳቸው ሲሉ በእኛ በኩል አቅርበዋል፤ እኛም ምስጋናቸው ይድረሳችሁ ብለናል፡፡

ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና 95 በመቶ ተጠናቋል …..///…… ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለው መስመር ጥገና 95 በመቶ ሲጠናቀቅ የሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ደግሞ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሜሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት ከገረገራ እስከ ጋሸና ሲካሄድ የቆየው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና እየተገባደደ ነው፡፡ በመሆኑም ቀሪ የጥገና ሥራዎችና የመስመር ፍተሻ ሥራ እንደተጠናቀቀ ለሥርጭት መስመሮች ኃይል እንዲደርስ በማድረግ አካባቢዎቹ ኃይል የሚያገኙ ይሆናል ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር ጥገና የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ ገልፀዋል፡፡ ኃላፊው አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንዳስታወቁት ከዚህ ቀደም በአስቸኳይ ጥገና እስከ ደሴ ያሉት ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ የተደረገው ባለ132 ኪሎ ቮልት መስመርን በመጠገን ብቻ ነበር፡፡ ከተሞቹ ኤሌክትሪክ ካገኙ በኋላ በሁለተኛ ዙር ጥገና ከሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሲከናወን መቆየቱን ገልፀዋል፡፡ አሁን ላይ ጥገናው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም ነው ያስታወቁት፡፡ ይህም በትልልቅ ከተሞች የኃይል እጥረት እንዳይኖር ያደርጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 18 ቀን 2014 ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ብቻ!! በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል አሸባሪው የህወኃት ቡድን የፈፀመውን ወረራ ተከትሎ የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳትና የመከላከያ ሠራዊታችን አጋር ለመሆን የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች ከዚህ ቀደም ከደመወዛቸው 50 ሚሊየን ብር የሚጠጋ እንዲሁም ከተቋሙ 25 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ ከህዳር 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ በደም ልገሳ፣ በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ አስተዋጽኦ እያደረጉ ሲሆን በጥሬ ገንዘብ ብቻ የተሰባሰበው ከ1 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ሆኗል፡፡ በዓይነት እየተሰባሰበ ያለው ድጋፍም ለወገን ደራሽነታችንን በሚያስመሰክርና ተቋማችንን በሚመጥን መልኩ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ነው፡፡ በመሆኑም አስተዋጽኦውን የምታደርጉና በዓይነት የተሰባሰበውን ድጋፍ ለማስገባት እስከ ታህሳስ 19 ቀን 2014 ዓ.ም 11፡00 ሰዓት ድረስ ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡ ለተጨማሪ ድጋፍ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000444528129 ይጠቀሙ፡፡ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴው!

የማዕከላዊ ሪጅን አመራሮችና ሠራተኞች ደም ለግሰዋል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች የህልውና ዘመቻውን ለመደ
+7
የማዕከላዊ ሪጅን አመራሮችና ሠራተኞች ደም ለግሰዋል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች የህልውና ዘመቻውን ለመደገፍ ትናንት የደም ልገሳ አከናውነዋል፡፡ የደም ልገሳው የሪጅኑ አመራሮችና ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው በተጓዳኝ ሀገር በምትፈልጋቸው ሁሉ ለማገልገልና መስዋዕት ለመሆን ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ የሪጅኑ አመራሮችና ሠራተኞች በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የአልባሳትና የገንዘብ ማሰባሰብ የበጎ አድራጎት ሥራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በደም ልገሳው 22 ዩኒት ደም ተሰብስቧል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ በቀጣዮቹ አራት ቀናት ይጠናቀቃል .......///....... ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና በቀጣዮቹ አራት ቀናት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም ጉዳት ደርሶባቸው ከነበሩ የማስተላለፊያ መስመሮች በተጨማሪ አምስት ቦታዎች ላይ ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን ሦስቱ ከባድ የመበጣጠስ ጉዳት የደረሰባቸው ነው፡፡ የደረሱትን ጉዳቶች የመጠገን ሥራ በርብርብ እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በቀጣዮቹ አራት ቀናት ውስጥ ሥራው ሊጠናቀቅ ይችላል ብለዋል፡፡ በመስመሮቹ ላይ በተካሄደ የፍተሻ ሥራ በቅርቡ የደረሱትን ተጨማሪ ጉዳቶች ሳይጨምር ሠላሳ አራት በሚሆኑ በምሰሶቾች መካከል በሚገኙ ቦታዎች ላይ 50 የመስመሮች መበጣጠስ፣ 7 የድምፅና ዳታ ማስተላለፊያ የኦፕቲካል ፋይበር መቆረጥ እና 13 ቦታዎች ላይ መስመር ሳይበጠስ ጉዳት መድረሱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

የተቋሙ ሠራተኞች የዘማቾች ቤተሰብ ሰብል ሰበሰቡ …….////…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደጀን - ደብረማርቆስ ማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ኘሮጀክት ሠራተኞች “ስንተጋገዝ እና ስንተባበር ከባዱ ቀላል ይሆናል!” በሚል መሪ ሀሳብ የዘማቾች ቤተሰብ ሰብል ሰበሰቡ። ሠራተኞቹ ትናንት ታህሳስ 13 ቀን 2014 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ከተማ ዙሪያ ባሉ ቀበሌዎች ለሀገር ህልዉና እየተዋደቁ ለሚገኙ የዘማቾች ቤተሰብ ሰብላቸውን በመሰብሰብ አጋርነታቸውን አሳይተዋል። የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለጹት ፕሮግራሙ ከኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታ ጎን ለጎን ቤተሰብና ሰብላቸውን ጥለው ለሀገር ሉዓላዊነት ዋጋ እየከፈሉ የሚገኙ ዘማቾችን ለማሰብና ቤተሰባቸውንም ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። የሰብል መሰብሰብ ኘሮግራሙ ተቋሙ በሚገነባቸው የተለያዩ ኘሮጀክቶች አካባቢ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ መልካም እሴቶችን ለማጎልበት ትልቅ ማሳያ መሆኑን አቶ ዋለ ተናግረዋል ። በቀጣይም በሌሎች የተቋሙ ኘሮጀክቶችና ጣቢያዎች ከመደበኛ ሥራዎች በተጓዳኝ ለህብረተሰብ ለውጥ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ሌሎች ሥራዎችን ለማከናወን ተቋሙ ትኩረት አድርጎ በመንቀሳቀስ የተቋሙን እሴት ለመገንባት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል። ሰብላቸው ከተሰበሰበላቸው የዘማች ቤተሰቦች መካከል ወ/ሮ አስረስ መብሬ እንደተናገሩት ባለቤታቸው አቶ አያሌው ደጉ ከዚህ ቀደም በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ለሀገራዊ ጥሪ ዘምተው በክብር የተሰናበቱ እንደነበር አስታውሰዋል። ባለቤታቸው በሰላም ጊዜ ጎበዝ አርሶ አደር በሀገራቸው ጉዳይ ደግሞ የማይደራደሩ ግንባር ቀደም ዘማች መሆናቸውን ወ/ሮ አስረስ ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች "ባለቤቴን ተክተዉ የዓመት አዝመራየን በመሰብሰብ ላሳዩኝ አጋርነት ከልብ አመሰግናለሁ" ብለዋል። ሌላዋ የዘማች ባለቤት ወ/ሮ አቻምየለሽ ካሳ በበኩላቸው ባለቤታቸው አቶ ጌታየ አስራደ ከነሐሴ ወር 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለሀገር ህልውና እየተዋደቁ እንደሚገኙ ገልፀው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች በችግር ጊዜ ደርሰው ሰብላቸውን ስለሰበሰቡ መደሰታቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሚያከናውናቸው የኤሌክትሪክ ማመንጨት፣ ማስተላለፍ፣ ማከፋፈልና ሌሎች የተቋሙ ሥራዎች ጎን ለጎን በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ፈጣን ምላሽ እየሰጠ ይገኛል። በቅርቡ ከወራሪው የህወኃት የሽብር ቡድን ነፃ የወጡ የአፋርና የአማራ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ከፍተኛ ርብርብ ማድረጉ አይዘነጋም፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+9

photo content
+1

ለወልዲያ ከተማና አካባቢው አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በጁንታው ተነቅሎ ተወስዷል …..///…… ዶሮ ግብር በተባለው ቦታ ለወልዲያ ከተማና አካባቢው አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በጁንታው ተነቅሎ ተወስዷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የባለሙያዎች ቡድን በስፍራው ተገኝቶ እንዳረጋገጠው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያው ለስም የቀረ ነገር ሳይኖር በአሸባሪው የህወኃት ቡድን ተነቃቅሎ ተወስዷል። ማከፋፈያ ጣቢያው ከወልዲያ ነባር ባለ 66 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር በመሆን ለወልዲያ ከተማ፣ ለወልዲያ ዪኒቨርሲቲ፣ ጭፍራ፣ ሲሪንቃ፣ ሳንቃ፣ ኡርጌሳ፣ ውጫሌ፣ ጉባላፍቶ፣ቃሊም፣ ጉብዬ፣ ሀራ፣ሮቢት ቆቦ ጊራና ከተሞችና አካባቢያቸው የሚሄዱ መስመሮች ነበሩት። የሽብር ቡድኑ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያውን ጨምሮ ከነባሩ የወልዲያ ማከፋፈያ ጣቢያ የሥርጭት ትራንስፎርመሮችን ነቅሎ መውሰዱን እና የትራንስፎርመር ዘይት ገልብጦ መውሰዱን ማረጋገጥ ተችሏል። የዓይን እማኞቸ እንደገለፁት የሽብርተኛው የህወኃት የዘረፋ ቡድን ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የተዋቀረና ትራንስፎርመሩ ችግር አለበት ወይስ የለውም የሚለው እየተፈተሸ ነው የወሰደው። በባለሙያዎች ቡድኑ የሚቀርበውን መነሻ መሰረት አድርጎ የጥገና ቡድኑ ከነሐሴ 2 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ የተቋረጠውን የወልዲያና አካባቢው ኤሌክትሪክ ለማገናኘት በፍጥነት የጥገና ሥራውን እንደሚጀምር ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 11 ቀን 2014 ዓ/ም

በአፋር ክልል ለኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ ኃይል ይቋረጣል …..///…… የኮምቦልቻ ሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ትናንት ቢጠናቀቅም የኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ባለመጠናቀቁ በአፋር ክልል ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ ኃይል እንደሚቋረጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያስታውቃል። ኃይል ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች ትናንት የተጠናቀቁ ቢሆንም የኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ቀሪ ስራዎችን ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ በመስራት ሙሉ በሙሉ ጥገናውን ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ ነው። የኦፕቲካል ፋይበር ጥገናው ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ለግማሽ ቀን የሚካሄድ ይሆናል። ስራዎቹ እንደተጠናቀቁ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመነጋገር የአፋር ከተሞች ኃይል የሚያገኙ ይሆናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

ወደአፋር ክልል የሚገባው የኤሌክትሪክ መስመር ተጠግኖ በመጠናቀቁ ክልሉ ምስጋና አቀረበ ..........////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮምቦልቻ ሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ጠግኖ ለአገልግሎት በማብቃቱ የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስጋና አቀረበ። የክልሉ የውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አህመድ ሻም ክልሉን በመወከል ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ጁንታው በአፋር ክልል ያደረሰውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ውድመት በአጭር ጊዜ በመጠገን ለአገልግሎት በማብቃቱ ክልሉ እውቅና ሰጥቷል። በአጭር ጊዜ የተሰራው ስራ ለአፋር ህዝብ ትርጉም ያለው ሲሆን ለጁንታው ደግሞ ራስ ምታት እንደሚሆንበት አንስተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው በተቋሙ ባለሙያዎች በአጭር ጊዜ ሊሳካ የማይችል የሚመስል ሥራ መሰራቱ ተቋማችን ለህዝብ የቆመ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ የክልሉ ህዝብና የፀጥታ ኃይል ድጋፍ ባያደርግ ኖሮ ስራው በፍጥነት ሊጠናቀቅ አይችልም ነበር። ለዚህም የክልሉ ህዝብና መንግስት እንዲሁም በጥገና ስራው ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች በሙሉ አመስግነዋል። የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኃላፊ አቶ ያሲን ኡስማን ደግሞ ጁንታው ለአፋር ክልል ህዝብ እንደ ኦክስጂን አስፈላጊ የሆነውን መብራት እንዲቋረጥ በማድረግ የክልሉን ህዝብ ለማንበርከክ ያደረገው ጥረት በአፋር ህዝብ ጀግንነት አልተሳካለትም ብለዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በርብርብ እንዲስተካከል የተደረገውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ነገ ለሁሉም አካባቢ እንዲደርስ እናደርጋለን ሲሉ ቃል ገብተዋል። የምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንቢሮ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ እንደገለፁት መስመሩን ጠግኖ ለአገልግሎት ለማብቃት የተደረገው ጥረት ከባድ መስዋዕትነት የጠየቀ ቢሆንም በትልቅ ሀገራዊ ስሜት ተከናውኗል። በሥራውም ላይ በየቀኑ በርካታ ሰው በቅንጅት ሲንቀሳቀስ እንደነበርም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 09 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5

በየቀኑ በአማካይ 200 ሰዎች ሲሳተፉበት የቆየው የኮምቦልቻ ሠመራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቀቀ …..///…… የኮምቦልቻ ሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ የሙከራና የፍተሻ ሥራ እየተከናወነ ነው። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት በቡርቃና ካሳጊታ አካባቢ በሽብርተኛው የህወሓት ቡድን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሙሉ በሙሉ ተጠግነዋል። ድምፅና ዳታ ለማስተላለፍ ከተዘረጋው የኦፕቲካል ፋይበር ውጪ የጥገና ሥራው በመጠናቀቁ ከኮምቦልቻ ሠመራ በተዘረጋው መስመር ኃይል ሲያገኙ የነበሩ የአፋር ከተሞች በሙሉ ኃይል እንዲያገኙ መስመሮችን ዝግጁ ለማድረግ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል የፍተሻ ሥራ ተከናውኗል ብለዋል። በዛሬው ዕለት የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል እንዲያገኝም ተደርጓል። ይህን ተከትሎ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ያሉት የሥርጭት መስመሮች ዝግጁ ሲሆን ሚሌ፣ ዲቼቶ፣ ሎጊያና ሰመራን ጨምሮ በርካታ የአፋር አካባቢዎች ኃይል የሚያገኙ ይሆናል። በኮምቦልቻ ሠመራ መስመር በጥገና ሥራ ላይ በየቀኑ በአማካይ ከ2 መቶ ያላነሱ የቴክኒክ ባለሙያዎችና የጉልበት ሠራተኞች ሲሳተፉ ቆይተዋል። የቀኑን ሐሩርና ውሃ ጥም ተቋቁመው እስከ ሁለት ወር ሊወስድ የሚችለውን ሥራ በሁለይ ሳምንት ውስጥ እንዲጠናቀቅ ላደረጉ የማከፋፈያ ጣቢያና የማስተላለፊያ መስመር የጥገና ባለሙያዎች እንዲሁም የራስ አቅም የጥገና ሰራተኞች አቶ ሀብታሙ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 09 ቀን 2014 ዓ/ም

“ደም በመለገስ ህይወት እናትርፍ፤ማህበራዊ ኃላፊነታችን እንወጣ” በሚል መሪ ሐሳብ የደም ልገሳ ተካሄደ ………////………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች “ደም በመለገስ ህይወት እናትርፍ፤ ማህበራዊ ኃላፊነታችን እንወጣ” በሚል መሪ ሐሳብ በዋና መሥሪያ ቤት ዛሬ የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሃግብሩ ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖቻችን እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን በየሦስት ወሩ በቋሚነት የሚከናወነው የደም ልገሳ አካል ነው፡፡ ዛሬ ለግማሽ ቀን በተካሄደው የደም ልገሳ 35 ዩኒት ደም ተለግሷል፡፡ ከዚህ ቀደም በሪጅኖችና በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ደም የተለገሰ ሲሆን በትናንትናው ዕለትም የጅግጅጋ ንዑስ ሪጅን ሠራተኞችና አመራሮችም ትናንት 12 ዩኒት ደም ለግሰዋል፡፡ የማዕከላዊ ሪጅን ሰራተኞችና አመራሮች ደግሞ በቀጣይ ሳምንት ሐሙስ በኮተቤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግቢ ደም ለመለገስ ቀጠሮ ይዘዋል፡፡ ከአሁን በፊት ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ደም ከመለገስና ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ በጦርነቱ ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ አመራሩና ሠራተኛው በትኩረት ሲንቀሳቀሰ ቆይቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሚያከናውናቸው የተቋሙ መደበኛ ሥራዎች በተጨማሪ በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡ ተቋሙ በአሸባሪው የህወሓት ቡድን የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመጠገን ወደ ሥራ ለማስገባት ሰፊ ርብርብ እያደረገ ይገኛል፡፡ በተከናወነው የመልሶ ጥገና ሥራ ኮምቦልቻና ደሴን ጨምሮ በርካታ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 08 ቀን 2014 ዓ/ም