የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
5 066
Subscribers
-25624 hours
-1 8217 days
-3 02830 days
Posts Archive
የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 4 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሯ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የሁለት ቀን ቆይታ ከመንግስት እና ከአፍሪካ ሕብረት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።
ጉብኝቱ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት ለማጠናከር ያለመ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ጣሊያን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ሰብዓዊ እና የልማት ድጋፍ ማጠናከር ዋነኛ የቆይታቸው አጀንዳ ይሆናል ተብሏል።
ሀገራቱ በሚጋሯቸው ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሯ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
"ግብፅ የአባይን ውሃ እና ግድቡን የፖለቲካ መልክ ለማሰጠት እየሄደች ያለችበት መንገድ የትኛውን አካል የሚጠቅም አይደለም" ፦ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህመት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል በውይይታቸውም ስለ ዓባይ ግድብ የተለያዩ ነጥቦችን አንስተዋል።
አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ ምን አሉ?
አምባሳደሩ ግብፅ የአባይን ውሃ እና ግድቡን የፖለቲካ መልክ ለማሰጠት እየሄደች ያለችበት መንገድ የትኛውንም አካል የሚጠቅም አይደለም በማለት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው የታላቁ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት የኢትዮጵያን አቋም ለሊቀመንበሩ ሲያስረዱ÷ "የሶስትዮሽ ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስራ መከናወኑ መቀጠል እንዳለበት ኢትዮጵያ የፀና አቋም አላት" ሲሉ ተደምጠዋል።
አምባሳደሩ አክለው ይህ እንቅስቃሴ ተገቶ መሬት ላይ ያለውን እውነት መነሻ ያደረገ ወይይትና ድርድር እንዲቀጥል ህብረቱ በጎ ሚናውን ይወጣል በማለት ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
የህብረቱ ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህመት ምን አሉ?
ሊቀመንበሩ አባይ አፍሪካዊ ወንዝ በመሆኑ አጀንዳው አህጉራዊ መሆን እንዳለበት ህብረቱ እንደሚያምን ገልፀዋል።
ድርድሩም በአፍሪካ ማዕቀፍ እልባት እንዲያገኝ ህብረቱ የማያይቋረጥ ድጋፍ እንደሚያደርግ አንስተዋል፡፡
ህብረቱ በሚያከናውነው ተቋማዊ ሪፎርምም የሰራተኞችን መብትና ጥቅም ባከበረ መልኩ እንደሆነ ማረጋገጣቸውን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ቀጥሎ እየተካሄደ ሲሆን የውሃ ሙሌት በቀጣዩ ክረምት የሚይዘው የውሃ መጠን ከ22 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ወደ 42 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ከፍ እንደሚልና ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ ከ50 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሏል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ እብደታ የነበሩ ሁኔታዎች ዕዙን ጠንካራ እንዲሆን አሥቸለውታል ሲሉ ተናገሩ፡፡
አዛዡ ይህንኑ ያሉት በዕዙ ስር ከሚገኙ የኮማንዶና አየር ወለድ ክፍለጦሮች ጋር ስለ ሀገራዊ የፀጥታ እና የሰላም ጉዳዮች ዙሪያ በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ የሠራዊት አባላት ከባዱን ውጣ ውረድ በማለፍና ለህይወታቸው ሳይሳሱ አስፈላጊውን መስዋዕትነት በመክፈል ሀገርን ከብተና የታደጉ ጀግኖች ናቸውም ብለዋል፡፡
ሀገር ከየትኛውም የፖለቲካ ቡድን በላይ ነው ሠራዊት ደግሞ የሀገርን ሠላም የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት እናም ይህንኑ ሃላፊነቱን በተገቢው መንገድ እየተወጣ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በዚህ አሰተሳሰብ ሠራዊቱ ሀገራችንን ከየትኛውም ጥቃት ለመከላከል የተደራጀ ኃይል ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ክፍሉ ቀጣይ የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ግዳጅ ከዚህ በፊት ከነበረው በላቀ አግባብ ለመፈፀም እና ጥንካሬውን ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
👉 ግብፅ በድብቅ ሮኬቶችን ለሩሲያ ለማቅረብ ማቀዷ ተሰማ‼
ግብፅ በድብቅ ሮኬቶችን ለሩሲያ ለማቅረብ ማቀዷን ሾልኮ የወጣ ሰነድ አመለከተ።
የግብፅ ፕሬዝዳንት አብደልፋታህ ኤል ሲሲ ለሩሲያ የሚቀርቡ 40 ሺህ ሮኬቶችን ለማዘጋጀት አቅደው የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እና የጦር መሪዎች በሚስጥር እንዲይዙ አሳስበው እንደነበር ነው ሰነዱ የጠቆመው፡፡
ድርጊቱም ከምዕራባዊያን የሚመጣባቸውን ችግር ለማስወገድ ያለመ እንደነበር ዋሽንግተን ፖስት አገኘሁት ያለውን ሰነድ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡
ሚስጥራዊ ሰነዱ ከቅርብ ወራት ወዲህ በተለያዩ ማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ ሾልከው ከወጡ ሰነዶች መካከል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣን በእቅዱ ዙሪያ ምንም አይነት መረጃ የለንም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ሰነዱ እውነት ከሆነ ግብፅ ከሞስኮ ጋር ጠንካራ ግንኙነት መመስረት የምትችል ቢሆንም ከአሜሪካ ጋር የሚኖራት የወደፊት ግንኙነት ግን ምን ሊመስል እንደሚችል መገመት ከባድ ይሆናል፡፡
ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 01 ቀን 2015 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰዱ ዋና ዋና ሀሳቦች፡-
• የአንድ ሀገር ሠራዊት ጥንካሬ የሚወሰነው በዋናነት በማዕከላዊነቱና በጠንካራ የዕዝ ሰንሰለቱ ነው
• በመከላከያ ሠራዊት አደረጃጀት የቁጥር ብልጫ የሚጫወተው የራሱ ሚና እንዳለ ይታመናል፤ በጠንካራ ዕዝ ሰንሰለት፣ በጥብቅ ዲሲፕሊን፣ በተደራጀ ስትራቴጂ፣ በረቀቁ መሳሪያዎችና ሥልጠናዎች እስካልታገዘ ድረስ አስተማማኝ አይሆንም
• ከሥልጠናው፣ ከትጥቁና ከዕዝ ሰንሰለቱ የሚመነጭ፤ ወታደራዊ ማዕከላዊነት ለመከላከያ ሠራዊት “ጥራት” ወሳኝ ነው
• ሀገራት አጣዳፊ የጸጥታና የደህንነት ሥጋቶች ውስጥ በሚገቡበት ጊዜ አነስተኛና መካከለኛ የጸጥታ ኃይሎችን አደራጅተው ለመንቀሳቀስ ይገደዳሉ፤ እነዚህ ኃይሎች በጥድፊያ ውስጥ በጊዜያዊነት እንደመቋቋማቸው መጠን የሚሰጡትም ጊዜያዊ መፍትሔ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ እንዳልሆነ ይታወቃል
• የመከላከያ ሠራዊት ማዕከላዊ በሆነ መልኩ ማጠናከርና ለሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲበቃ ማድረግ ተገቢና ወቅታዊነቱ አያጠያይቅም
• በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ልዩ ኃይሎች ወደ መከላከያ ሠራዊት ለመቀላቀል ያልፈለጉ ወደ ፌደራል ፖሊስ ወይም ወደ ክልሎች ፖሊስ እንዲገቡ ምርጫ ተቀምጦላቸዋል፣
• የክልሉ ልዩ ኃይሎች ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ፈተና በገጠማት ጊዜ ሕይወታቸውን ሠውተዋል
• በየአካባቢው የተሰጣቸው ግዳጆችን በመወጣት ሕግና ሥርዓት ለማስከበር ታግለዋል
• አሁን ባለችው ኢትዮጵያ የልዩ ኃይል አደረጃጀት አስፈላጊ አይደለም ማለት የልዩ ኃይል አባላት አያስፈልጉም አይደለም
• የልዩ ኃይል አባላትን ወደ መከላከያ ወይም ወደ ፖሊስ እንዲገቡ የማድረግ አጀንዳ ለረጅም ጊዜ ተመክሮበታል፤ አጀንዳው በተለያዩ ጊዜያት በአመራርም በሕዝብ መድረኮችም ተነሥቶ ነበር
• አንድ የልዩ ኃይል አባላትን ጥቅማ ጥቅም፣ ዕድገትና ማዕረግ፤ ሁለት አደረጃጀቱን ምክንያት በማድረግ በተደጋጋሚ ያጋጠሙንን ፈተናዎች የተመለከተ ነው
• የልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ በተገቢው መንገድ መስተናገድ እንዳለባቸው ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ጉዳይ አይደለም
• በሀገር ውስጥና በውጭ የሚሰጡ ወታደራዊ ትምህርቶችንና ሥልጠናዎች ሊደርሷቸው ያስፈልጋል
• ወታደራዊ ማዕረጎች በቆይታቸውና በጀብዷቸው ሊቀዳጁ ይገባል፤ የላቁ ወታደራዊ መሣሪያዎችን ሊታጠቁ ይገባል፤ ይህ መሆን የሚችለው ወደ መደበኛ የጸጥታና ደህንነት ተቋማት ማለትም በሀገር መከላከያ ሠራዊት አልያም በፌደራል ፖሊስ ሠራዊትና በክልሎች ፖሊስ ሠራዊት ውስጥ መካተት ሲችሉ ብቻ ነው
• በውጊያ የተፈተኑ ኃይሎች በጊዜያዊ የልዩ ኃይል አደረጃጀት ወስኖ ማስቀረት ሀገርንም አባላቱንም መጉዳት ነው
• የተጣለባቸውን ኃላፊነት በዐቅማቸው የተወጡ፤ ለወደፊትም በተሻለ ኢትዮጵያን ማገልገል በሚያስችላቸው ቦታዎች ላይ እንደየፍላጎታቸው ተመድበው ያገለግላሉ
👉 ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን የሠላማችን ዋስትና ነው‼️
እናንተ ባህር ማዶ ሆናችሁና በሠላም እየኖራችሁ፣ እዚህ ሀገር ውስጥ ካሉ ጥቂት ያበዱ አክራሪ ብሔርተኞች ጋር ተቀናጅታችሁ በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ላይ የአሉቧልታ ድንጋይ የምትወረውሩ አጥንት ቆጣሪዎች አደብ ልትገዙ ይገባል‼️አይበገሬው መከላከያ ሠራዊታችንና ልዩ ኃይሎቻችን በአንድ ምሽግ አብረው የከረሙ፣ የአንዱን ከበባ አንዱ የሰበረ፣ መስዋዕትነት ሲከፍልም አብረው በአንድ ጉድጓድ የተቀበሩ፣ የማይነጣጠሉና የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው። ልዩ ኃይሉ ነገም ቢሆን የጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አካል መሆኑ አይቀርም። እናም አብረው ዋጋ የከፈሉና ነገም በጋራ ተሰልፈው ለአንዲቷ ሀገራቸው የሚዋደቁ የፀጥታ አካላትን እርስ በእርስ ለማጋጨት የውዥንብር መረጃዎችን ከማሰራጨት ልትቆጠቡ ይገባል። እንዲህ ዓይነቱ አካሄድ፤ ለአማራ ሕዝብም ይሁን ለልዩ ኃይሉ የሚፈይደው አንዳችም ነገር የለም‼️
ጀግናውና አይበገሬው መከላከያ ሠራዊታችን ከዘረኝነት አስተሳሰብ የፀዳ፣ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ሁሉ መመኪያና አለኝታ ነው። የሕዝቦች የሠላም ዋስትናም ነው። የሉዓላዊነታችን ጠባቂና ባለአደራም ነው። በየትኛውም አቅጣጫ በመከላከያ ሠራዊታችን የሚቃጡ ማናቸውም ዓይነት ትንኮሳዎች፤ በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ የሚቃጡ ናቸው። እንዲህ ዓይነቱ መረን የለቀቀና ሕግን ያልተከተለ ድርጊት ማንም ሊታገሰው እንደማይችል ማወቅ ብልህነት ነው‼️
ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇
የኢፌዴሪ መከላከያ መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
"መርከብ ያለ ባህር ሀገር ያለ ወታደር ብቃቱን ሊያረጋግጥ አይችልም" ፦ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሁርሶ የእጩ መኮንን ማሠልጠኛ በ23ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን የጉባ ኮርስ እና የድህረ ምረቃ ዕጩ መኮንኖችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር አብይ አህመድ ባስተላለፉት መልዕክት በጉባ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ የአለምን ጫና ለብሔራዊ ጥቅማችን ስንል ተቋቁመን የውሃውን ሙሌት ብቻ ሳይሆን ውሃው ከላይ መፍሰስ እንዲችል አድርገን የጨረሰንበት ታሪካዊ ቦታ ነው።
የጉባ ኮርስ እጩ መኮንን ተመራቂዎችም እንደስማችሁ የኢትዮጵያን የታሪክ እጥፋት የምታመጡ፣ ፈተና የሚያበረታችሁ፣ የተሠጣችሁን ሃላፊነት በብቃት የምትወጡ የሀገር ኩራት መኮንኖች ናችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያ የማትበገር የፀናች ለልጆቿ ዕዳ የምታሸጋግር ሳይሆን በትውልድ የበለፀገች እና ያማረች በታሪኳም በአሁናዊ ቁመናዋም የምታስደስት ሀገር ስለመሆና የእናንተ ተመራቂ መኮንኖች ገፅታ ማሳያ ነው።
የሃሣብያን ሀገር ሃሳብ ታፈልቃለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ኢትዮጵያ እናንተን መሠል ጀግኖች ስላሏት የምትፀና፣ የምተኮራ፣ ትውልድ እንኳን ተወለድኩባት የሚላት እና የሚመካባት ሀገር እንድትሆን ሚናችሁ እጅጉን ከፍተኛ ነው ብለዋል።
መርከብ ያለ ባህር ሀገር ያለ ወታደር በወጉ በስፍራው ካልታየ ብቃቱን ሊያረጋግጥ አይችልም መርከብ በአስፓልት ላይ ቢቆም የቆመ ግዙፍ እቃ ከመሆን አልፎ በባህር ላይ የሚያሳየውን ብቃት አያሳይም ጠንካራ ሀገርም ካለ ወታደር የፀናች መሆን አትችልም ብለዋል።
ተመራቂ መኮንኖች አንድ ውድ ህይወት አላችሁ እሡም ህይወታችሁ ኢትዮጵያ ሀገራችሁን መጠበቅ ነው። ለሀገራችሁን ዋጋ የምትከፍሉላት የምትሠውላት ትልቁ አላማ ኢትዮጵያን ለማፅናት እና ለማስቀጠል ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ለምንሳሳላት ሀገር የሚከፈልላት ማንኛውንም ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ሆነን ኢትዮጵያን በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በአለም እንደ ታሪኳ ገናና ሆና እንድትቀጥል ተመራቂ መኮንኖች የበኩላችሁን ድርሻ ልትወጡ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።
መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም
#በዛሬዋ_ዕለት
ከ 77 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመሪያ ዓለም አቀፍ በረራውን ከአዲስ አበባ ተነሥቶ በአስመራ በኩል ወደ ካይሮ (ግብፅ) በረራ ያደረገበት ዕለት ነበር።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታህሳስ 21 ቀን 1938 ዓ.ም ተመሠረተ። ዋና መሥሪያ ቤቱም በመዲናዋ አዲስ አበባ ላይ የነበረው ይህ አንጋፋ ተቋም ከቀድሞው ትራንስ ወርልድ ኤይርዌይስ/ Transworld Airways (TWA) ጋር በጋራ የተመሠረተ ሲሆን አስተዳደሩ በአሜሪካኖች እጅ ነበር።
ድርጅቱ ታኅሣሥ 21 ቀን 1938 ዓ/ም ተመሥርቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ከ አዲስ አበባ ተነሥቶ ካይሮ ድረስ አከናወነ። አየር መንገዱ ሲመሠረት ከአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል የተገዙና በሁለተኛው ዓለም ጦርነት ያገለገሉ አምስት ዲ.ሲ. ፫ ( DC 3-C47 ) አውሮፕላኖች ነበሩት።
#ታሪክን_ወደኋላ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር አብይ አህመድ በሁርሶ ሰላም ማስከበር ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተገኝተው የጉባ ኮርስ እና የድህረ ምረቃ ዕጩ መኮንኖችን በማስመረቅ ላይ ናቸው።
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሁርሶ ማሰልጠኛ ያሰለጠናቸው እጩ መኮንኖች ዘመኑ የሚጠይቀውን ወታደራዊ ሳይንስ እና የአመራር ጥበብ የተካኑ መሆናቸው ተገልጿል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ ጀነራል መኮንኖች፣ የቀድሞ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
