የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
4 550
Subscribers
-22324 hours
-1 7327 days
-3 48930 days
Posts Archive
ዩክሬንና ብሪታንያ በጋራ በመሆን የሩሲያ አብራሪዎችን ለማስኮብለል ያዘጋጁት ሚስጥራዊ እቅድ ተጋለጠ
ዩክሬን Su-24M፣ Su-34 እና Tu-22M3 የሚባሉ የሩሲያ የጦር ጄቶች ላይ ከፍተኛ ፍላጎት ነበራት
ሩሲያ የብሪታንያ እና የዩክሬን አብራሪዎቿን ለማስኮብለል እና የሚያበሩትን ጄት ካስረከቡ በነፍስ ወከፍ 2 ሚሊዮን ዶላር ለመክፈል ያዘጋጁትን ሚስጥራዊ እቅድ አጋለጠች።
የሩሲያ የፌደራል የደህንነት አገልግሎት በብሪታኒያ የሚደገፍ እና ለእያንዳንዳቸው የሩሲያ የጦር አውሮፕላን አብራሪዎች 2 ሚሊየን ዶላር ለመክፈል እና በአውሮፓ ሀገራት ውስጥ የመኖሪያ ፈቃድ እንዲያገኙ የተዘጋጀ እቅድ ላይ መድረሱን አስታውቋል።
በተጋለጠው ሚኒስጥራዊ እቅድ መሰረትም የሩሲያ አብራሪዎች በዩክሬን የጦር አውሮፕላኖች የተጠለፉ በማስመሰል ዝቅ ብለው በመብረር የያዙትን የጦር ጄት በዩክሬን እጅ ወደ ሚገኝ የአውሮፕላን ማረፊያ አንዲያሳርፉ ለማድረግ ነበር።
ኪቭ Su-24M፣ Su-34 እና Tu-22M3 የሚባሉ የሩሲያ የጦር ጄቶች ላይ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት የደህንት ባለስልጣኑ ያስታወቁ ቢሆንም፤ ሆኖም ግን እቅዱ የሩሲያ አብራሪዎች ለሀገራቸው የፌደራል የደህንነት ተቋም በሰጡት ጥቆማ ሊደረስበት ችሏል።
ሮሲያ 24 የተባለው የሀገሪቱ ብሄራዊ ጣቢያ ባወጣው መረጃ ሞሶኮ ከሪስቶ ግሮሴቭ ተባለ የምርመራ ጋዜጠኛ የማስኮብለያ ቅድመ ክፍያዎችን ለአብራሪዎች የመክፈል ሂደት ውስጥ ከብሪታኒየ የስለላ ተቋም ጋር ሲሰራ ነበረ በሚል መክሰሷ ጠቅሷል።
ለአብራሪዎች ከገንዘብ በተጨማሪም በፈረንሳይ እና በጀርመን ጭምር መኖሪያ እየተመቻቸላቸው አንደሆነም የምርመራ ጋዜጠናው አረጋግጧል።
የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ አዲስ አበባ ገቡ!
የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል። ሰርጌይ ላቭሮቭ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሚኖራቸው ቆይታ በሩሲያ እና ኢትዮጵያ መካከል ስላለው የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
“የሶማሌ ክልል ህዝብ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ልዩ የሆነ አንድነትና ህብረት ከአርበኞቹና ጀግኖቹ ጎን በመቆም ላበረከተው እጅግ በጣም ከፍ ያለ የሞራል ስንቅ እና ከልብ የሆነ ድጋፍ አመሰግናለሁ!
"የክልሉን ፀጥታና የነዋሪዎች ደህንነት መቼም ቢሆን በአልሸባብ አሸባሪነት ሊታወክ እንደማይችል ሙሉ እምነት አለኝ !
"አሸባሪው አልሸባብ በራሱም ይሁን ከጀርባው የጥፋት ተልዕኮ በሚሰጠው ቀጣሪ ኃይል ግፊት ፣ ይህ ሊረግጠው የሚሻው የሶማሌ ክልል ምድር ፣ የእግር እሳቱና የመጥፍያው መሬት እንጂ እንዳሻው ገብቶ በቀላሉ የሚወጣበት ቦታ እንዳልሆነ ማሳወቅ ይገባል! ደጋግሞ ማሰብም ግድ ይለዋል!"
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ዑመር
#የአሜሪካና_ቻይና_ፍጥጫ
ቻይና ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ ወታደራዊ ጨምሮ ማንኛውንም አይነት እርምጃ ልወስድ እችላለሁ ስትል አስጠንቅቃለች
አፈጉባኤዋ ናንሴ ፔሎሲ የፊታችን ነሀሴ ወር ላይ ታይዋንን እንደሚጎበኙ ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ በሁለቱ ሀገራት መካከል አዲስ አለመግባባት ተከስቷል፡፡
የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዛኦ ሊጃን ለፋይናንሺያን ታየምስ እንዳሉት “ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ቻይና ወታደራዊ እርምጃዎችን ጨምሮ ማንኛውንን አይነት እርምጃ ለመውሰድ በሚገባ ተዘጋጅታለች” ብለዋል፡፡
"አሜሪካ አሁን በያዘችው እቅድ የምትመራ ከሆነም ቻይና ጠንካራ እርምጃ መውሰዷን ትቀጥላለች ፣ለሚፈጠረው ክስተትም አሜሪካ ሃላፊነቱን ትወስዳለች” ሱሉም ቃል አቀባዩ አክለዋል፡፡
የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት እስካሁን ቻይና ስለሰጠችው ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ምንም ያላለ ሲሆን በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው ራሳቸውን ያገለሉት ፕሬዝዳንት ባይደን በያዝነው ሳምንት ውስጥ ከቻይና አቻቸው ሺ ሺፒንግ ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል ሲሉ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ቻይና ታይዋን የግዛቴ አንድ አካል እንጂ ሀገር አይደለችም በሚል ጠንካራ አቋም ያላት ሲሆን ታይዋን ይሄንን እንድትቀበል የተለያዩ ጫናዎችን በማድረስ ላይ እንደሆነች ይጠቀሳል፡፡
የታይዋን መንግስት በበኩሉ ጉዳዩ የ23 ሚሊዮን ዜጎች ውሳኔ እንጂ የቻይና ማዕከላዊ መንግስት አይደለም በሀይል ከተጠቃንም ሁላችንም ለሉዓላዊነታችን እንዋጋለን በማለት ላይ ትገኛለች፡፡
በምስራቅ ኢትዮጵያ በኩል ሰርጎ ለመግባት የሞከረውን አልሸባብ በመደምሰስ ተቆርጠው የቀሩ የሽብር ቡድኑን አባላት የማጽዳት እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የሀገር መከላከያ ሃይል ስምሪት ሃላፊና ጊዜያዊ የፀጥታ ኮማንድፖስት አስተባባሪ ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ተናገሩ።
የኢትዮጵያ ጠላቶች በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍልና በምዕራብ ኢትዮጵያ የተወሰደውን የህግ ማስከበር እርምጃ ተከትሎ ሰላም የሰፈነ ሲመስላቸው ሰሞኑን በምስራቅ ኢትዮጵያ የማጥቃት ሙከራ ማድርጋቸውን ገልጸዋል።
የአልሽባብ አሸባሪ ቡድን በሶማሌ ክልል በአምስት ትናንሽ የጠረፍ አካባቢዎች ማለትም በየድ፣ አቶ፣ ኤልብርዴ፣ ዋቃሾና ፈርፈር ለማጥቃት ቢሞክርም በጸጥታ ሃይሉ ሙሉ በሙሉ መክሸፉን ጠቅሰዋል።
የሶማሌ ልዩ ሃይልና አመራርም የሽብር ቡድኑን በመደምሰስ የነበረው ሚና የላቀ መሆኑን መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የአልሽባብ ታጣቂዎች በአንድ አካባቢ ብቻ ሰርገው ገብተው የነበረ ቢሆንም የጸጥታ ሃይሉ ከበባ በማድረግ ከ100 በላይ የሽብር ቡድን አባላት ደምስሷል ብለዋል።
ቡድኑ ለሽብር አላማው ሲጠቀምባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ ጠቅሰው፤ ተቆርጠው የቀሩ የሽብር ቡድኑ አባላትን የማጽዳት እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸዋል።
በሽብር ቡድኑ ላይ በተወሰደው ርምጃ፣ መትረየስ፣ አር ፒ ጂ እና ሌሎች ከባድ የቡድን መሳሪያዎች እንዲሁም የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች ተማርከዋል።
በአካባቢው የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት የሀገሩን ዳር ድንበር እያስከበረ መሆኑን የጠቀሱት ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ፤ የሶማሌ ክልል ህዝብ ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለክልሉ ልዩ ሃይል ከፍተኛ የሞራልና የስንቅ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ጥምር የፀጥታ ሃይሉ ሙሉ በሙሉ በቀጣናው መግባቱን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለመድፈር የሚሞክሩ ሃይሎች ላይ ሙሉ ርምጃ ለመውሰድ የሀገር መከላከያ ሰራዊትና የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይልን ጨምሮ የፀጥታ ኮማንድ ፖስቱ በተጠንቀቅ ላይ መሆኑን መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የአርጀንቲናው ፕሬዚዳንት አልቤርቶ ፈርናንደዝ BRICS ን ለመቀላቀል ይፋዊ ጥያቄ አቅርበዋል ። ከአርጀንቲና በተጨማሪ አረባዊቷ ግብፅ ብሪክስን ለመቀላቀል መወሰኗን በመሪዋ አብዱልፈታህ አልሲሲ በኩል አሳውቃለች ።
የአርዶጋኗ ቱርክ ፣ ኢራን ፣ ሳኡዲ አረቢያ እና ሜክሲኮ ብሪክስን ይቀላቀላሉ ተብሎ የሚጠበቁ ሀገራት ናቸው ። እንደዚያ ከሆነ ብሪክስ ከየትኛው የምእራባውያን ህብረት በኢኮኖሚም በወታደራዊ አቅምም የጠጠረ የምእራባውያንን የዘመናት የሀያልነትና የመሪነት ፀሀይን የሚያጠልቅ ለአለም አድስ ሚዛን ፈጥሮ አለምን በምስሉ የሚቀርፅ ህብረት ያደርገዋል ።
ብሪክስን የመሰረቱት ብራዚል ፣ ሩሲያ ፣ ህንድ እና ቻይና የነበሩ ቢሆንም በሗላ ላይ የአፍሪካዋ ሀብታም ሀገር ደቡብ አፍሪካ ግንባሩን ተቀላቅላለች ። በዚህም ብሪክስ ተፅእኖው በአለም ላይ ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ ፈርጣማ ድርጅት ለመሆን ችሏል ።
አሁን ላይ BRICS ከአለም ከ 1 - 10 የያዙ የኢኮኖሚ ባለፀጋ ሀገራት ውስጥ ቢያንስ 3 ቱን ይዟል ። እነ ቱርክና ሜክሲኮን እንድሁም ሀብታሟን ሳኡዲ አረቢያን ሲያጠቃልል ደግሞ ድርጅቱ ከአለም ከ 1 - 20 ያሉ ባለጠንካራ የጦርና የኢኮኖሚ ባለቤቶችን የሚያካትት ግዙፍ ድርጅት ይሆናል ።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ይህንን በአለም ተፅእኖው እየገዘፈ ያለና በልእለሀያላኖቹ ቻይና እና ሩሲያ የሚመራውን ድርጅት ብትቀላቀል የምታገኘው ኢኮኖሚያዊ ወታደራዊና ድፕሎማሲያዊ ትርፍ የትየለሌ ነውና ቢታሰብበት እንላለን !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ዳንቶ🎵🎶💚💛❤️
የምስራቅ አንበሶቹ የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል አባላት ዛሬ በኢትዮጵያና ሶማሊያ ድንበር አከባቢ አልሸባብን ከገረፉ በኋላ በሶማሌ ተወዳጅ በሆነው ዳንቶ በተሰኘ የሙዚቃ ምት እንዲህ ወዝ…ወዝ ሲሉ ታይተዋል።
#የምስራቅ_አንበሶች!
#የዳር_ድንበር_አጥሮች!
#ኢትዮጵያ 💪
መረጃዎች‼️
1፤ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት የተፈጸሙ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እንዲመረምር ባለፈው ታኅሳስ ያቋቋመው መርማሪ ኮሚሲዮን ኮሚሽነሮች ከዛሬ እስከ ቅዳሜ በኢትዮጵያ ጉብኝት ላይ መሆናቸውን ምክር ቤቱ በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ሦስቱ ኮሚሽነሮች በመጭው ቅዳሜ የጉብኝታቸውን ውጤት አስመልክተው ከተለያዩ አካላት ጋር ይወያያሉ። ሦስት ኮሚሽነሮች ያሉት ኮሚሲዮን ምርመራውን በቅርበት እንዲያከናውን ካምፓላ ላይ ጽሕፈት ቤት ተቋቁሞለታል።
2፤ መከላከያ ሠራዊት የሱማሊያውን አልሸባብ ለመፋለም ወደ ኢትዮ-ሱማሊያ ድንበር መሠማራቱን የሱማሌ ክልል ኮምንኬሽን ቢሮ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ኡመር ባካባቢው ከክልሉ ልዩ ኃይል ጋር የተቀላቀሉትን የሠራዊቱ አባላት ጎብኝተዋል። ባለፉት ቀናት የክልሉ ልዩ ኃይል በአፍዴር ዞን በኩል ወደ ሱማሌ ክልል በገቡት የአልሸባብ ተዋጊዎች ላይ ልዩ ስሙ ሁልሁል በተባለ ቦታ ላይ፣ በርካታ የቡድኑን ታጣቂዎች መግደላቸውና ጦር መሳሪያዎችን መማረካቸውን የክልሉ መንግሥት መግለጡ ይታወሳል።
3፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በመጭው ዓመት 30 ሚሊዮን ብር በጀት ያስፈልገኛል ሲል ዛሬ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ መግለጡን ኢትዮጵያ ኡንሳይደር ዘግቧል። ምክር ቤቱ በጀቱን የፈለገው፣ የአባል ፖለቲካ ፓርቲዎችን አቅም ለመገንባት እና በአገራዊ ምክክሩና በአካባቢያዊ ምርጫዎች ዓይነተኛ ተሳትፎ ለማድረግ እንዲችል መሆኑን ተናግሯል። ምክር ቤቱ አብዛኛውን ገንዘብ ለማግኘት ያቀደው ከዓለማቀፍ ለጋሾች ነው።
4፤ ሳፋሪኮም ኩባንያ በኢትዮጵያ ቴሌኮም ዘርፍ ለመሠማራት ከአሜሪካው ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ላገኘው አገልግሎት 4 ሚሊዮን ዶላር እንደከፈለ ቢዝነስ ደይሊ ዘግቧል። ኮርፖሬሽኑ ምን አገልግሎት እንደሰጠ ኩባንያው ባይገልጽም፣ በኢትዮጵያው የቴሌኮም ጨረታ የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም ዓለማቀፍ ብድሮችን ማስገኘት ሊሆን እንደሚችል ዘገባው ጠቁሟል። የናይሮቢው ስታንዳርድ ቻርተርድ ባንክ ብቻ ለኩባንያው 400 ሚሊዮን ዶላር አበድሯል። ሳፋሪኮም በነሐሴ በድሬዳዋ ሥራውን ይጀምራል።
5፤ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ዛሬ ከግብጹ አቻቸው አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ቤተ መንግሥታቸው በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ሁለቱ መሪዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ፣ በሁለትዮሽ እና የቀይ ባሕር አካባቢ ደኅንነትን ጨምሮ በቀጠናዊ ጸጥታና ልማት ዙሪያ መወያየታቸውን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ሥልጣን ከያዙ ወዲህ፣ ከግብጽ ቀደም ብሎ በኤርትራ፣ ጅቡቲና ኬንያ ኦፊሴላዊ ጉብኝት አድርገዋል።
6፤ የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የግብጽ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ዛሬ ኮንጎ ብራዛቪል እንደገቡ ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። አገራቸው ከዩክሬን ጋር በገባችበት ጦርነት ሳቢያ ምዕራባዊያን ማዕቀብ ከጣሉባት ወዲህ፣ ላቭሮቭ በአፍሪካ ተከታታይ ጉብኝቶችን ሲያደርጉ የመጀመሪያቸው ነው። ላቭሮቭ ከኮንጎ ብራዛቪል ቀጥሎ ኡጋንዳንና ኢትዮጵያን የሚጎበኙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአፍሪካ ኅብረት ባለሥልጣናት ጋር ጭምር እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል። ከወር በፊት የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ሩሲያን መጎብኘታቸው ይታወሳል።
7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ1166 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ1589 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 59 ብር ከ4718 ሳንቲም፣ መሸጫው 60 ብር ከ6612 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ52 ብር ከ9661 ሳንቲም ሲገዛ እና በ54 ብር ከ0254 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።
ልዩ መረጃ #BBC
#Ethiopia : በሶማሊያ ሂራን ዞን በኩል ወደ ፌርፌር ወረዳ ዘልቆ ለመግባት ኤል ቁዱን በምትባል በሶማሊያና ኢትዮጲያ ድንበር ላይ በምትገኝ ንኡስ በዝግጅት ላይ የነበረ የአልሸባብ ታጣቂ ቡድን ተደመሰሰ።
በቡድኑ ላይ የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል ድንገተኛ እና የተጠና የማጥቃት እርምጃ በመውስድ የአሸባሪ ቡድኑ አበላትን በመደምሰስ አከባቢውን መቆጣጠሩን የ BBC ሶማሊኛ ዘግቧል።
#ኢትዮጵያ #አሜሪካ #ሩስያ
በመጪዎቹ ቀናት ኢትዮጵያ የሩስያ እና የአሜሪካ ባለስልጣናትን ታስተናግድለች።
ነገ ማክሰኞ የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ሰርጌ ላቭሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ።
ለቭሮቭ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ነው ነገ አዲስ አበባ የሚገቡት።
በአዲስ አበባ ቆይታቸው ፦
- በኢትዮጵያ እና ሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ፤
- ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ እና ሩስያ መካከል የተፈረሙ ስምምነቶች ላይ ይመክራሉ፤
- ከአፍሪካ ህብረት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ላቭሮቭ ኢትዮጵያ ሲመጡ የመጀመሪያቸው አይደለም። እ.ኤ.አ 2018 ላይ ኢትዮጵያን ጎብኝተው ነበር።
(ሰርጌ ላቭሮቭ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው ቀደም ብሎ #በግብፅ የስራ ጉብኝት አድርገዋል)
#US የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ከሐምሌ 17- ሐምሌ 25 2014 ዓ.ም ኢትዮጵያን ጨምሮ በግብፅ፣ በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ጉብኝት ያደርጋሉ።
በኢትዮጵያ ግብኝታቸው የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላም ለመቋጨት ሊደረግ የታሰበው የሰላም ድርድር ላይ ይወያያሉ።
በተጨማሪ ፦
- የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ያለበትን ሁኔታ ይገመግማሉ።
- በጦርነቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ ማድረግን በተመለከተ ይመክራሉ።
ሐመር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ከተሾሙ በኃላ ወደኢትዮጵያ ሲመጡ ሁለተኛቸው ይሆናል ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ መጥተው ከምክትል ጠ/ሚ እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር መወያየታቸው አይዘነጋም።
(ማይክ ሐመር ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት #በግብፅ ጉብኝት ያደርጋሉ)
መዓዛ ግደይን የዛሬ 11 አመት ነው ፌስቡክ ላይ የማውቃት አስታውሳለሁ በቴዲ አፍሮ የተነሳ በውስጥ መስመር አውርተን ተከራክረን እናውቃለን መቼም በጥላቻ የታወረች ልጅ መሆኗን ቀድሜ ባውቅም ስለሷ ለማወቅ ባደረኩት ጥረት አብረዋት የተማሩ ልጆች በቂ ነገር ስለሷ ነግረውኛል ከኢትዮጵያ አወጣጥዋ ጭምር አንዳን ጉዳዮችን አብረዋት የተማሩትን ልጆች የነገሩኝን በሌላ ግዜ ይዤ እመለሳለሁ ለአሁኑ ግን መዓዛ ስለ ደራርት ቱሉ በጻፈችው ነገር ላይ አንድ ነገር ልበል
ወያኔ የሚከስሳትን ደራርቱን ኢትዮጵያ ከፍ ታደርጋታለች!
ጀግናዋ ደራርቱ ለኢትዮጵያ ክብር የሆኑትን የትግራይ ልጆችን ከዚህ ውጤት እንዲደርሱ ብዙ ለፍታለች። ወያኔ የትግራይ ልጆች ባመጡት ውጤት ደስተኛ ቢመስልም ለውጤቱ መምጣት ዋነኛዋን ደራርቱን ጀኖሳይድ ፈፃሚ አድርጎ ስሟን እያጠፋ ነው። ከዚህ አገር አጥፊ ቡድን ከዚህ ያነሰ አንጠብቅም። ድሮም ኢትዮጵያዊነት ከፍ ሲል አይናቸው ይቀላል። ደራርቱ በአትሌቲክሱ ውጤት እንዲመጣ አድርጋ ኢትዮጵያውያን ስለ አገር አንድ ስለሆኑ ወያኔ አላመው ፉርሽ ሆኖበት ተናድዷል። ሌሎቹ ውስጣቸው እየደማ ኢትዮጵያን ያኮሩትን የትግራይ ልጆች ውጤት ቢያደንቅም ማዕዛ ግደይ የተባለችው የወያኔ ዋነኛ አክቲቪስት ግን የሚያስቡትን አልደበቀችም።
ወያኔ ኢትዮጵያዊነትን ይጠላል። ኢትዮጵያዊነትን ጠልቶ ደራርቱን ሊወዳት አይችልም። ደራርቱን የሚያከብራት ኢትዮጵያን የሚያከብር እንጅ ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ ብሎ የተነሳው ወያኔ አይደለም። በአትሌቲክሱ ውጤት የወያኔን ያህል ኬንያም አልተናደደችብንም። ወያኔ ግን ገና ይበሽቃል። ኢትዮጵያዊነት ከፍ ይላል።
©ናትናኤል_መኮንን
የሱማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስጠፋ መሀመድ ኡመር ዛሬ የኢትዮጲያን ድንበር ከአሸባሪው አልሸባብ የሚጠብቁ የሃገር መከላከያ ሠራዊት በማበረታታት ላይ ናቸው።
የሃገር መከላከያ ሠራዊትና የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል የሃገራችንን ድንበር በመጠበቅ በአሸባሪው አልሸባብ ቀሪቶች ላይ የተቀናጀ እርምጃ በመውስድ የሃገራቸውን ድንበር ጠብቀው የህዝባችንን ሠላም እንደሚያሰጠብቁ ሙሉ እምነት እንደለው የሶማሌ ክልል ርዕስ መሰተዳደር ለመከላከያ ሠራዊቱ ገልጽዋል።
⬆️
#MondayMessage የሰኞ መልዕክት
የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን፣ አካውንቶችን እንዲሁም ቻናሎችን እንዴት ቬሪፋይ ማስደረግ ይቻላል?
የማህበራዊ ሚዲያ ማረጋገጫ (verification) ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ ሲደረግ ለታዋቂ ግለሰቦች እና ድርጅቶች እንዲሁም ከፍተኛ ተከታዮች ላሏቸው ሰዎች ብቻ ተጠብቆ ነበር። ከጊዜ በኋላ ግን በርከት ያሉ ኩባንያዎችን፣ ጋዜጠኞችን፣ አክቲቪስቶችን፣ የመንግስታት ሀላፊዎችን እና ተጽዕኖ ፈጣሪዎችን ለማካተት ጥረት ተደርጓል፡፡
በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ይህንን ማረጋገጫ (verification) ማግኘት ብዙ ጥቅሞች አሉት። ከእነዚህም መሀል:
• ከተከታታዮች ጋር መተማመንን ለመገንባት
• ማህበራዊ ማስረጃን (social proof) ለማግኘት
• ተመሳስለው የሚከፈቱ አካውንቶችን፣ ገፆችን እና ቻናሎችን በቀላሉ ለመለየት፣ እንዲሁም
• የተከታታዮችን እድገት ለማግኘት ወዘተ ሊጠቀሱ ይችላሉ
በትዊተር ላይ ማረጋገጫን (verification) ማግኘት: በትዊተር ላይ ማረጋገጫን ለማግኘት በሚከተሉት ምድቦች ውስጥ መገኘት ያስፈልጋል:
• የመንግስት አካል
• የምርት ድርጅቶች፣ ኩባንያዎች እና ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች
• ጋዜጠኞች እና የዜና ድርጅቶች ባልደረባ
• የስፖርት ድርጅቶች እና ስፖርተኞች
• መዝናኛ ኢንደስትሪ ውስጥ ያሉ መሆን
• አክቲቪስቶች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች መሆን
የትዊተርን ሰማያዊ ባጅ ለመቀበል ገጹ ትክክለኛ (authentic)፣ ታዋቂ (notable) እና ንቁ (active) መሆን አለበት።
ትክክለኛ(authentic): የትዊተርን ማረጋገጫ ለማግኘት ትዊተር ማንነትዎን ማረጋገጥ ይፈልጋል። ማንነትዎን ለማረጋገጥ ከሶስቱ ዘዴዎች ውስጥ አንዱን መምረጥ ይቻላል። እነሱም: የተረጋገጠ ድረ-ገፅ፣ መታወቂያ ወይም የኢሜል አድራሻን መጠቀም ይቻላል።
ታዋቂ (notable): አካውንቱ ከታወቀ ግለሰብ ወይም ድርጅት ጋር በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ የተያያዘ መሆን አለበት። ይህንንም ትስስር ትዊተር በራሱ ወይም አብረው በሚሰሩ ድርጅቶች ይረጋገጣል።
ንቁ (active): የትዊተር አካውንቱ የትዊተር ህጎችን ባከበረ መልኩ ንቁ መሆን አለበት። ይኼ ማለት የመገለጫ ስም እና የመገለጫ ምስል ሊኖረው ይገባል። ንቁ አጠቃቀም ማለት ባለፉት 6 ወራት ውስጥ አካውንቱን መጠቀም አለብዎት። ከዚህም በተጨማሪ አካውንቱ የተረጋገጠ የኢሜል አድራሻ ወይም የስልክ ቁጥር ሊኖረው ይገባል።
አንዴ የትዊተር ማረጋገጫ ከተሰጠ በኋላ የተጠቃሚ ስምዎን (username) ከቀየሩ፣ አካውንቱ እንቅስቃሴ አልባ ከሆነ፣ ወይም መጀመሪያ መረጋገጫው በተሰጠበት ቦታ ላይ ካልሆኑ የተሰጠው ማረጋገጫ ሊወርድ ይችላል። Note: ትዊተር ከቀናት በፊት የማረጋገጫ ጥያቄዎችን ለግዜው መቀበል እንዳቆመ አስታውቋል።
በፌስቡክ እንዴት ማረጋገጫ ይሰጣል?
• በመጀመርያ ወደ ፌስቡክ ሰማያዊ ማረጋገጫ ባጅ መጠየቂያ ገጽ (Blue Verification Badge Page) ይሂዱ። ሊንክ: https://www.facebook.com/business/learn/lessons/verify-facebook-instagram-account
• የማረጋገጫ ዓይነትዎን (ገጽ ወይም አካውንት) ይምረጡ
• ምድብ ይምረጡ፣ አገርዎን ይምረጡ፣ መታወቂያ ያስቀምጡ፣ የእርስዎ መለያ/አካውንት ለምን መረጋገጥ እንዳለበት ያብራሩ፣ ከዛም 'ላክ' የሚለውን ይጫኑ።
ለግለሰቦች የመንጃ ፈቃድ ወይም ሌላ በመንግስት የተሰጠ የመታወቂያ ካርድ ይበቃል። ለንግድ ገጽ ደግሞ የምስረታ የምስክር ወረቀትን፣ የኩባንያዎን ስልክ ወይም የፍጆታ ሂሳብ ወይም የግብር ሰነዶችን ማቅረብ ይችላሉ። ጥያቄዎን ከላኩ በኋላ የፌስቡክ ማረጋገጫ ቡድን መረጃዎን ይገመግምና እና ውሳኔ ይሰጣል።
ፌስቡክ ጥያቄውን ከተቀበለው በአካውንቱ ላይ ሰማያዊ ባጅ ይታያል። ሆኖም ጥያቄዎ ውድቅ ከተደረገ ከ30 ቀናት በኋላ እንደገና ማመልከት ይችላሉ። የፌስቡክ ማረጋገጫ የብቁነት መስፈርቶች ከኢንስታግራም (Instagram) ጋር ተመሳሳይ ናቸው።
እንዲሁ በዩትዩብ (YouTube) ላይ ማረጋገጫ ማግኘት ይቻላል። የዩትዩብ ቻናሉ ለማረጋገጫ ባጅ ብቁ ከሆነ ግራጫ አመልካች ምልክቱን ለማግኘት በማረጋገጫ ባጅ ገጹ ላይ ማመልከት ይችላሉ።
ዩትዩብ መስፈርቶቹን የሚያሟላ መሆኑን ለማየት ቻናሉን ይገመግማል። የማረጋገጫ ባጅ ለመቀበል የዩትዩብ ቻናሉ ቢያንስ 100,000 ተመዝጋቢዎች ሊኖረው እና መስፈርቶችን ማሟላት አለበት።
ማስታወሻ: ሁሉም የማህበራዊ ሚድያ ድርጅቶች ማረጋገጫ ለመስጠት ገንዘብ አያስከፍሉም፣ ስለዚህ "ማረጋገጫ እንዲሰጥዎት እናደርጋለን" ብለው ገንዘብ ከሚጠይቁ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ራስዎን ይጠብቁ።
©EthiopiaCheck
#ሰላም #Peace
የጎተይቶም የሰላም ምኞት !
ጎተይቶም ገብረስላሰ የሴቶች ማራቶን #የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ፦
" ... ምኞቴ ሰላም ነው። ሰላም በምንም ነገር አይገኝም።
እኛ በጣም ነው ሰላምን የምንፈልገው። ዓመት ከስምንት ወር ሆኖብናል የወላጅ ናፍቆት ቀላል አይደለም።
እናቴ እንዳለችው እኔ ናፍቆት አልችልም። ማይቻል ነገር ግን የለም። ችለን እዚህ ደረስን እንጂ እኔ ናፍቆት አልችም ነበር።
አንድ ቀን ሳልደውልላት አልተኛም። አባት፣ እናቴን በጣም እወዳለሁ፤ አባቴን በጣም ነው የምወደው በዛ የተነሳ ስልክ ሳልደውልላቸው አልተኛም ነበር።
ማይቻል ነገር የለም ብላዋለች እናቴ ናፍቆትን አትችልም እሷ ይሄን ሁሉ ተቋቁማ እዚህ መድረሷ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ነው ያለችው ትክልል ነው ማይቻል ነገር የለም ችዬዋለሁ።
እግዚአብሔር ሰላም አምጥቶ እንዲያገናኘን ነው ምኞቴ። "
ጎተይቶም ገብረስላሰ የኢትዮጵያን ህዝብ ስሜት በተመለከተ፦
" .. እያየሁ ነበር የነበረውን ድባብ፣ የነበረውን ደስታ እንደዚህ ስንሆን ነው የሚያምርብን ፤ ሁሉን ነገር ትተን #ለሰላም ስንቆም ነው።
ለካ ይሄንን ያህል በህዝቡ ልብ ውስጥ አለን ብዬ ነበር ለራሴ ፤ ደጋግሜ እያየሁ ነበር።
እርግጥ ውድድሩ አጓጊና እልህ አስጨራሽ ነበር በጣም ፤ በዛ የተነሳ ሰው ስሜታዊ ሆኖ ነበር በጣም ነው የማመሰግነው። በፀሎትም፣ በሞራልም የደገፉኝ ሰዎች በጣም ነው የማመሰግነው።
ሁለተኛ ትልቅ ደስታ ነው የፈጠረብኝ። ይሄን ያህል ህዝብ ነበር ለካ የሚከታተለው ብዬ ለራሴ ውስጤን እንድጠይቅ ነው ያደረገኝ "
(አትሌት ጎተይቶም ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጠችው ቃለምልልስ)
©tikvahethiopia
ለኢትዮጵያ ክብር እና አንድነት የሚከፈል መስዋእትነት!
የሱማሌ ክልል ልዩ ሀይል ፖሊስ።
ክብር ይገባቸዋል።💚💛❤️
" ደራርቱ ቱሉ ፍቅር የሆነች ልጅ ነች " ሲፋን ሀሰን
ባለፉት ጥቂት አመታት ከኢትዮጵያዊያን ጋር በምታደርገው እልህ አስጨራሽ ፉክክር በአትሌቲክስ አፍቃሪው ዘንድ ትውልደ ኢትጵያዊቷን አትሌት ሲፋን ሀሰን የማያውቃት የለም ።
ሲፋን ሀሰን አለም ሻምፒዮናውን እንዲሁም ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ በሰጠችው አስተያየት ለደራርቱ ቱሉ ልዩ ፍቅር እንዳላት ገልፃለች ።
" ኢትዮጵያኖች በአለም ሻምፒዮናው ባስመዘገቡት ድል በጣም ነው ደስ ያለኝ ፣ በፓሪስ 2024 የኦሎምፒክ ውድድር ጥሩ ውጤት ቢያስመዘግቡ ደስ ይለኛል ።
" ደራርቱ ከመጣች በኋላ ነው ይሄ ሁሉ ለውጥ እና የአትሌቶች ፍቅር ልናይ የቻልነው " ያለችው ሲፋን ሀሰን ለተሰንበት ወጣት እና በጣም የማደንቃት አትሌት ነች ፣ ደራርቱን በጣም ነው የምወዳት ፍቅር የሆነች ልጅ ነች ።
ለኢትዮጵያዊያን የማስተላልፈው መልዕክት አንድ ሁኑ በዘር አትከፋፈሉ ነው ፣ ለተመዘገበው ውጤት ኢትዮጵያዊያኖች እንኳን ደስ አላችሁ " ስትል ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፋን ሀሰን መልዕክቷን አስተላልፋለች ።
ምንጭ :- ጋዜጠኛ ይሳቅ በላይ
ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም
✍ እያደር ይጠራል!
ሠላም ለሀገር ደም ስር ነው። ሠላም የመኖር ዋስትና ነው። ሠላም የእድገት መሠረት ነው። ለዚህም ነው "ዋናው ነገር ሠላም" የሚባለው።
እኛ ኢትዮጵያዊያኖች የነፃነትንና የሠላም ዋጋን ጠንቅቀን እናውቃለን። ሀገራችን ሰላም ባጣችበት ወቅት የህይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደልና የንብረት መውደም አደጋ አጋጥሞናል። ጀግኖች አባቶቻችን ይህ እንዳይሆን አሁን ላለነው ትውልድ ለነፃነታችን እና ሠላማችን ሲሉ አጥንታቸውን ከስክሰዋል። ህይወታቸውንም ከፍለውልናል።
ወድ ህይወት የተከፈለላት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ለመበተን የተነሱ የውጭ ኃይሎች እንዳሉ ሁሉ ከውስጥም ሆነው ለተግባራዊነቱ ታጥቀው እና አድፍጠው የሚንቀሳቀሡ አሸባሪ ኃይሎች አሉ።
ሀገር የህፃናት እቃቃ መጫወቻ የመሠለው አሸባሪው ህወሃት የላኪዎቹን ትዕዛዝ ተቀብሎ ሀገር አፈርሳለሁ ቢል አይደንቅም። ምክንያቱም ህወሃት ከፅንስሡ ጀምሮ ለይስሙላ ለህዝብ የቆመ በማስመሠል የማፍረስ እና የማሸበር ተግባሩን በስልጣን ቆይታው ጭምር በተግባር አሳይቷል።
ይህን የማስመሠል አባዜውን ቀድመው የተረዱ አያሌ ኢትዮጵያውያኖች በቡድንም ሆነ በተናጠል ታግለዋል። ጫናው የበረታበት የኢትዮጵያ ህዝብም የአሸባሪው መንግስት አገዛዛ ሲያንገሸግሸው ከአራት ኪሎ ቤተመንግስት አሽቀንጥሮ በመቀሌ ዋሻ ከቶታል። ይህ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።
አሸባሪው በስልጣን እያለ ሲዘርፍ የነበረውን ጥቅም ሲያጣ መቀሌ መሽጎ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር መኖር የለባትም። አፍርሰናትም ሲኦል እንገባለን በማለት በገሀድ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ ወረራና ጭፍጨፋ ፈፀመ።
ይህ አልበቃቸውም በወረራ በገቡበት አካባቢዎች ዘረፉ፣ ከህፃን እስከ አሮጊት እና መነኩሴ ደፈሩ። የጥላቻ ጥጋቸውን በግፍ ገለፁ።
ተከበሀል፤ ልትጨፈለቅ ነው የሚሉ ቃላቶች የዘወትር መዝሙራቸው አደረጉ። ወጣቱን በጥላቻ ሞልተው የእኩይ ድርጊት ማስፈፀሚያቸው አደረጉት። በሐሽሸ አናውዘው እራሡን ስቶ የፍላጎታቸው ማስፈፀሚያ እንዲሆንም ያደርጉታል። እምቢ ካለም ከኋላው መሣሪያ ደግነው የሚፈልጉትን ሳይፈልገው ያስፈፅሙታል።
ከኢትዮጵያዊነት ጋር የተጣሉ አሸባሪዎች በተለያዩ የማደናገሪ ፕሮፖጋንዳ የሚኖሩበትን ህዝብ አደናግረውታል። የጥላቻ ጉም በመሆን ህዝቡን ከእውነታው ጋርደውታል።
ከደመና በላይ ሰማይ አለ ደመናውን አይቶ ሠማይ የለም የሚል አይጠፋም። ነገር ግን እያደር ሲጠራ ደመናውም ገፎ ሠማዩ ጥርት ብሎ ይታያል። ህውሃት በተለያዩ የማጨበርበሪያ ፕሮፖጋንዳዎች በትግራይ ሰማይ ላይ ያጠላው የጥላቻ ዳማና መግፈፉ አይቀርም። ይዋል ይደር እንጂ እያደር ይጠራል!
የጥላቻው ደመና የሠራዊታችንን ስም አጉድፏል። የሀገርን ክብር አዋርዷል። ፍላጎታቸው እና ግባቸው ኢትዮጵያን ማፍረስ ያደረጉ ህወሃታውያን የሠበቁትን የጥፋት ጦርነት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጀግናው መከላከያ ሰራዊቱ ጋር ሆኖ አምክኖታል።
ሠራዊታችን ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በትግራይ ምድር ያልሠራው ልማት፤ ያላገዘው አቅመ ደካማ የለም። አሸባሪው ህወሃት የነዛው ጉም ይህን እውነታ ጋርዶታል። ጉሙ ጥላቻን ወልዶ ሠሜን ዕዝ በተኛበት እንዲታረድ አድርጓል።
መግፈፉ የማይቀረው የጥላቻ ጉም የትግራይን ህዝብ ለችግር አጋልጦታል። ከወንድም ህዝቦች ሊነጥለውም ጋርዶታል። ጉሙ እየዋለ ሲያድር ህወሃትን እራቁቱን ያስቀረዋል። ህወሃት ጉሙ እንዳይገፍበት የጦርነት ጉሠማ ለማድረግ መፍጨርጨሩ ግድ ነው።
ጥላቻ፣ ሽብር እና ውጊያ ህወሃት የሚፈልገው መደበቂያ ጉሙ ነው። ሠላም ደግሞ የተደበቀበትን ጉም የሚገላልጥ ነው። ለዚህም ነው ህወሃት ሠላም ይስፈን ሲባል አሻፈረኝ የሚለው።
ኢትዮጵያውያን ሰላምንም ሆነ ጦርነትን በሚገባ ጠንቅቀው ያውቁታል። ሰላማቸውን የሚያውክ የውጭ ወራሪንም ይሁን የውስጥ አሸባሪ ኃይልን ለማስታገስ የተካኑ ናቸው።
ከህዝብ አብራክ የወጣው ጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ጠላትን አጥፍቶ ሠላምን ለማስፈን አቅሙም ብቃቱም አለው። ይህንንም በአሸባሪው ኃይል ላይ በወሠደው እርምጃ ማየት ይቻላል። ኢትዮጵያ እንደ አሸባሪው ህወሃት ፍላጎት ቢሆን ኖሮ እስካሁን የለችም። ፈርሳለች። ተበትናለች።
ለመከላከያ ሠራዊታችን ክብር ይግባውና ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሆና እንድትቀጥል የተወጣው ግዳጅ ዘመን የማይረሳው ታሪክ ሆኖ ተከትቧል። ህዝባችን ዘላቂ ሠላምን እንዲያገኝ ሠራዊታችን የኢትዮጵያ ጠላቶችን ለመደምስ ሁልጊዜ በተጠንቀቅ ቆሟል።
ክብር ለመከላከያ ሰራዊታችን!!
ብስራት ፀልይ
