የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
5 576
Subscribers
-40724 hours
-2 4147 days
-2 42630 days
Posts Archive
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የአየር ወለድ ስልጠናን አስጀመሩ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በቢሾፍቱ አየር ወለድ ትምህርት ቤት ተገኝተው የአየር ወለድ ሥልጠናን አሥጀምረዋል።
የአየር ወለድ ሠራዊት አባላት በኢትዮጵያ ሠራዊት ታሪክ ውስጥ ለሀገራቸው ሉአላዊነትና ለህዝባቸው ክብር አስፈላጊውን መስዋዕትነት በመክፈል ከፍተኛ ገድል በመፈፀም ታሪካቸውን በወርቃማ ቀለም የፃፉ የሀገር በለውለታዎች መሆናቸውን ለሰልጣኙ አብራርተዋል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አየር ወለድ ማለት ወደር በሌለው ጀግንነት ለላቀ ግዳጅና ድል መዘጋጀት ማለት መሆኑን በመግለፅ ሰልጣኞችም ከዚህ አኳያ ብዙ እንደሚጠበቅባቸው አውቀው ስልጠናቸውን በትጋት በመወጣት ለተጣለባቸው ታላቅ ሀገራዊ አደራ ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
አየር ወለድ በምንም ሳይታገድ በየትኛውም ቦታ እና ወቅት ድንበር ተሸጋሪ ግዳጆችን ጭምር መፈፀም የሚችል የሰራዊት ክፍል በመሆኑ እየተዘጋጀ ያለውም በዚህ ደረጃ መሆኑን ጄኔራል መኮንኑ አብራርተዋል፡፡
አየር ወለድ ከተመሰረተበት 1953 ዓ.ም ጀምሮ ታላላቅ ጀግና የሠራዊት መሪዎችን እያፈራ መቆየቱንና አሁንም እያፈራ መሆኑን በማስታወስ የአሁኑ ትውልድም ይህንን ታሪክ በመውረስ ለሀገሩ የላቀ ጀግና መሪ የመሆን ራዕይ ሊኖራው እንደሚገባም እስገንዝበዋል፡፡
ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሰን
ቀይ ለባሽ ኮማንዶ 🙏🇪🇹🙏
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
ቀይ ለባሽ ኮማንዶ 🙏🇪🇹🙏
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
Update‼
ከኢትዮጵያ በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ሊያመልጡ ሲሉ ተያዙ
የባለሀብቱን ገዳይ እና አስገዳይን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
አቶ ቢረሳው ምናለ ፈንታ የተባሉት ግለሰብ ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው አትሌቶች መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ ታህሳስ 21 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ከስራ መልስ ወደ ቤታቸው በማምራት በራቸው ላይ ቆመው የመኪና ጥሩምባ እያሰሙ በር እስኪከፈትላቸው እየጠበቁ በነበረበት ወቅት ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ በተተኮሰባቸው ሦስት ጥይት ህይወታቸው አልፏል፡፡
ፖሊስ የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት ከደረሰው ሰዓት ጀምሮ በወንጀሉ ስፍራ ፈጥኖ በመድረስ የወንጀል ፈፃሚውን ማንነት ለማወቅና በቁጥጥር ስር ለማዋል ቀን ከሌት ያልተቋረጠ እና እልህ አስጨራሽ ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል፡፡
ከወንጀሉ ጀርባ ያሉ ግለሰቦችን ማንነትና ምንነት ለመለየትም ከአዲስ አበባ ሐዋሳ እስከ ሞያሌ ጫፍ የደረሰ መረጃና ማስረጃዎችን የማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል። በፖሊሳዊ ጥበብ እና ስልት በተሰራው በዚህ ስራ ወንጀሉን በመፈፀም የተጠረጠረውን መኮንን ይዋል ይፍሩ የተባለውን ግለሰብ እና አብዩ አይተነው ፈንታ ጨምሮ ለወንጀሉ መፈፀም አካባቢውን በመቆጣጠር ተሳትፎ የነበረውን አቶ ወርቁ መለሰ ካሴ የተባሉትን ሦስቱንም ተጠርጣሪዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጌዴዎን ዞን ይርጋ ጨፌ ከተማ ላይ በቁጥጥር ሥር በማዋል ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ከወንጀሉ መፈፀም በፊት በተቀነባባረ ሴራ በቂ ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን የግድያ ወንጀሉን የፈፀመው መኮንን ይዋል ይፍሩ የተባለው ግለሰብ በህገ-ወጥ መንገድ በታጠቀው ማካሮቭ ሽጉጥ የአቶ አብዩ አይተነው ፈንታ የግል ጠባቂ ሆኖ ሲያገለግል እንደቆየ ተጠቁሟል።
ሁለቱ ግለሰቦች ከአቶ አብዩ አይተነው ፈንታ በተሰጣቸው ትዕዛዝ መሰረት አንዱ የአካባቢውን እንቅስቃሴ በመቆጣጠር ለወንጀል ፈፃሚው ሁኔታውን ሲያመቻች መኮንን ይዋል ይፍሩ የተባለው ደግሞ የግድያ ወንጀሉን መፈፀሙን ለፖሊስና ለፍርድ ቤት ከሰጡት የእምነት ቃል የተረጋገጠ ከመሆኑም ባሻገር በወንጀሉ ስፍራ የመርማሪዎችንና አቃቤ ህግ ቡድን እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት የወንጀሉን አፈፃፀም መልሶ ማቋቋም (Re-construct) በተግባር አሳይተዋል፡፡ በዕለቱም የወንጀሉ ፍሬ የሆነው ንብረትነቱ የአቶ አብዪ አይተነው ፈንታ የውግ ቁጥር የሌለው ማካሮቭ ሽጉጥ እና ለማምለጥ የሞከሩበት እንዲሁም ሽጉጡን የደበቁበት ላንድክሩዘር ተሽከርካሪ በኤግዚቢትነት ተይዟል ፡፡ ምንም እንኳን ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመቀየር ከወንጀሉ ተጠያቂነት ለማምለጥ በሐሰተኛ ስም ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት ከኢትዮጵያ በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ለመጥፋት ቢያስቡም በተሰራው እረፍት አልባ ፖሊሳዊ ጥበብ በታከለበት የክትትልና የምርመራ ስራ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በቅንጅት ሰርተዋል፡፡ የሲዳማ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን በዚህ የክትትል ስራ ውስጥ የጎላ ተሳትፎ እና ትብብር ማድረጉም ተጠቅሷል፡፡
የተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋል ወንጀል ፈፅሞ ከህግ ተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይቻል የሚያረጋግጥ ተግባር መሆኑን የጠቀሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ የህብረተሰቡን አቅም በመጠቀም ውጤት መገኘቱን አመላክቷል፡፡ በቀጣይም በተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚደረጉ የፍትህ ሂደቶች ውሳኔውን ተከታትሎ ለህዝብ እንደሚያቀርብ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያንና ለመላው ለኢፌዲሪ ለአገር መከላከያ ሰራዊታችን በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ ። መልካም በዓል ይሁንላችሁ ።
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
በ2025 ጠንካራ ጦር ያላቸው ሀገራት
የአለማችን የደህንነት ስጋት በየጊዜው እየጨመረ መሄድ ሀገራት ወታደራዊ አቅማቸውን ይበልጥ እንዲያሳድጉ አስገድዷል።
ባለፈው አመት (2024) ሀገራት ለወታደራዊ ተግባራት የያዙት የ2.34 ቢሊየን ዶላር በጀት ከ2023ቱ በ6 ነጥብ 8 በመቶ ማደጉም የሰጡት ትኩረት ማሳያ ነው።
በየአመቱ የሀገራትን ወታደራዊ አቅም ደረጃ የሚያወጣው "ግሎባል ፋየርፓወር" የ2025 ደረጃ ይፋ አድርጓል።
የወታደሮችና ጦር መሳሪያዎች ብዛትና ጥራት፣ አመታዊ የጦር በጀት፣ የጦር መሳሪያ ልማት እና ሌሎች ከ60 በላይ መመዘኛዎችን መሰረት አድርጎ የሚወጣው የወታደራዊ አቅም ደረጃ አሜሪካን ቀዳሚ አድርጓል።
ከፈረንጆቹ 2005 ጀምሮ ደረጃውን የምትመራው አሜሪካ 900 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ወታደራዊ በጀት ይዛለች።
በዩክሬን ጦርነት ከጀመረች ሶስት አመት ለመያዝ የተቃረበችው ሩሲያ በ2025 ፈርጣማ ጦር ካላቸው ሀገራት በሁለተኝነት ተቀምጣለች።
ከአሜሪካ በሶስት እጅ ዝቅ ያለ ወታደራዊ በጀት የምትይዘው ቻይና፣ ህንድ፣ ደቡብ ኮሪያ እና ብሪታንያ የባለፈውን አመት ደረጃቸውን አስጠብቀዋል።
ፈረንሳይ፣ ጃፓን፣ ቱርክ እና ጣሊያን እስከ 10ኛ ያለውን ደረጃ ሲይዙ ፓኪስታን ከባለፈው አመት ሶስት ደረጃዎችን ዝቅ ብላ 12ኛ ስትሆን፤ ጀርመን ደረጃዋን ከ19ኛ ወደ 14ኛ ማሻሻል ችላለች።
እስራኤል 15ኛ ላይ የተቀመጠች ሲሆን፥ ኢራን ከባለፈው አመት አንድ ደረጃ ዝቅ ብላ እስራኤልን ትከተላለች።
ግብጽ ከአፍሪካ አንደኛ ከአለም ደግሞ 19ኛ ደረጃን ስትይዝ ኢትዮጵያ ደግሞ ከአፍሪካ አምስተኛ ከአለም ደግሞ 52ኛ ላይ ተቀምጣለች።
ሰሜን ኮሪያ እና ሩሲያ በወታደሮች ብዛት አራተኛ እና አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
#Ethiopia #Somalia #Peace
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
#ሶማሊያ #ኢትዮጵያን #በአውሶም ወታደሮች ኮታ ውስጥ ለማካተት እየሰራች መሆኑን ገለጸች
ሶማሊያ ከዲፕሎማሲያዊ መሻሻል በኋላ ኢትዮጵያን በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ወታደሮች ኮታ ውስጥ ለማካተት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ መሃመድ ኦማር አስታወቁ።
ሚኒስትር ዴኤታው የተወሰኑ መሻሻሎች ቢደረጉም፣ ቀደም ሲል በተመደበው ኮታ ምክንያት የኢትዮጵያን ተሳትፎ በማረጋገጥ ረገድ ተግዳሮቶች መኖራቸውን አጽንኦት ሰጥተዋል።
"ዋነኛው እንቅፋት ከመግባቢያ ስምምነቱ ጋር የተያያዘ ነበር፤ ይህ ጉዳይ ተፈትቷል" ብለዋል። ይሁን እንጂ "አሁን ያለው ተግዳሮች አብዛኛው የወታደሮች ኮታ ቀደም ሲል የተመደበ መሆኑ ነው እናም ለማሰረማራት የቀረው በጣም ጥቂት ነው። መፍትሄ ለመፈለግ በንቃት እየሰራን ነው" ሲሉ አሊ መሃመድ ገልጸዋል።
ይህ የሆነው በቅርቡ በሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ እና በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መካከል በአዲስ አበባ በተደረገው ውይይት ሙሉ የዲፕሎማሲ ትስስርን ለመመለስ ስምምነት ላይ መደረሱን ተከትሎ ነው። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የባህር በር መግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ ከሶማሊያ ጋር የነበራት ግንኙነት መሻከሩ ይታወቃል።
የሶማሊያ ልዑካን ቡድን የጦር ሰራዊት ቁጥርን ጨምሮ የቴክኒክ ዝርዝሮችን ለማጠናቀቅ እና ከሶማሊያ ብሔራዊ ጥቅሞች ጋር የተጣጣመ መሆኑን ለማረጋገጥ ወደ ኢትዮጵያ ለማምራት ቀጠሮ ተይዟል።
በተጨማሪም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ መሃመድ፤ ኢትዮጵያ በሶማሊያ አምባሳደሯን ትሾማለች ተብሎ እንደሚጠበቅ እና የሶማሊያም አምባሳደር በቅርቡ በይፋ ሥራውን እንደሚጀምር አረጋግጠዋል። ይህም የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ሰፊ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ያሳያል ሲል ሂራን ዘግቧል።
የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ያጋሩ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇☝️☝️☝️
https://youtube.com/shorts/kQmhCYuYQeg?feature=shared
በህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተከሰሱት የቀድሞው አሜሪካዊው ሴናተር ላይ የ15 ዓመት እስራት ቅጣት እንዲጣልባቸው ተጠየቀ
በህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተከሰሱት የቀድሞው አሜሪካዊው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ ላይ የ15 ዓመት እስራት ቅጣት እንዲጣልባቸው የአሜሪካ ፌደራል ዓቃቤ ሕጎች ጠይቀዋል።
የአሜሪካ ፌደራል ዓቃቤ ሕጎች፣ ከግብጽ መንግሥት ከፍተኛ መጠን ያለው የገንዘብና የወርቅ ሥጦታ በመቀበል የግብጽን ጥቅም ለማስጠበቅ በሞከር ጥፋተኛ በተባሉት የቀድሞው የአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ቦብ ሜኔንዴዝ ላይ የ15 ዓመት እስራት ቅጣት እንዲጣልባቸው ጠይቀዋል።
ሜኔንዴዝ ጥፋተኛ ከተባሉባቸው ክሶች መካከል፣ የኢትዮጵያና ግብጽ የሕዳሴ ግድብ ውዝግብን ለመፍታት በሚደረገው ድርድር የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ሚና እንዲጫወት በመጠየቅ ያልተገባ ተጽዕኖ ለመፍጠር ሞክረዋል የሚል ይገኝበታል።
ክሱን ተከትሎ ሜኔንዴዝ የምክር ቤቱን መቀመጫቸውን መልቀቃቸው አስታውሶ ሲኤንኤን ዘግቧል። የፌደራሉ ፍርድ ቤት በሜኔንዴዝ ላይ የእስር ብይኑን ጥር 21 ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የቀድሞው የኒው ጀርሲው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የውጭ መንግሥት ፍላጎትን ለመፈጸም ሥልጣናቸውን መጠቀም፣ ጉቦ መቀበል፣ ማጭበርበር፣ ፍትሕን ማደናቀፍን ጨምሮ በ16 የወንጀል ድርጊቶች ተከሰው በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ መባላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
+2
የመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ እና የመሃል ሜዳ ከተማ አስተዳደር ያሰለጠኗቸውን ሚሊሺያ እና ሰላም አስከባሪ አባላት አስመርቀዋል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 04 ቀን 2017 ዓ.ም
በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የኮማንዶ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል ሳድቅ አህመድን ጨምሮ የሁለቱም ወረዳ አመራሮች እና የመንግስት ሰራተኞች ፣ የከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
የኮማንዶ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል ሳድቅ አህመድ ተመራቂ የሚሊሺያ እና ሰላም አስከባሪ አባላት በስልጠና ያገኙትን እውቀት ፣ክህሎት እና ልምድ ተጠቅመው የወረዳውን ሰላም የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አሁን ላይ በወረዳው ውስጥ አንፃራዊ ሰላም አለ ያሉት ኮሎኔል ሳዲቅ ይኸንን ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ እና ልማትን ለማሳደግ ካለው የፀጥታ ሃይል ተሞክሮ ወስዶ ለተሻለ ተልእኮ ራስን ማዘጋጀት ከተመራቂዎች ይጠበቃል ብለዋል።
የስልጠናውን ቆይታ እና ሂደት አስመልክቶ ሪፖርት ያቀረቡት ሻለቃ ዋሲሁን ስልጠናው የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ እጅግ ወሳኝ መሆኑን አንስተው ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ያሳዩት የስልጠና ብቃት እና ሞራል የሚበረታታ ነው ብለዋል።
ተመራቂ የሚሊሺያ አባላት በበኩላቸው ከስልጠናው በቂ እውቀትና ልምድ እንዳገኙ ገልፀው ስልጠናው የአካባቢን ሰላም ለማስፈን ፣ የሀሳብ እና የተግባር አንድነት ሊያመጣ የሚችል ወሳኝ ስልጠና በመሆኑ ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጁ ነን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በምን ጉዳዮች ላይ መከሩ ፤ ምንስ ተስማሙ ?
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል።
ከውይይቱ በኃላ የጋራ መግለጫ ወጥቷል።
ምን ተባለ ?
- በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
- በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና ግንኙነት በማጠናከር ላይ ገንቢ ውይይት አድርገዋል።
- የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እና በየመዲኖቻቸው ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ውክል እንዲኖር ለማድረግ ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ ለቀጣናው መረጋጋት የሁለቱ ሀገራት የጋራ የእርስ በርስ እምነት ፣ መተማመን እና መከባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትብብር እንደሚያስፈልግ አረጋግጠዋል።
- ቀጠናዊ ግንኙነቶችን ለማሻሻል፣ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እና የጋራ እድገትን ለማስቀጠል በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ የጸጥታ ትብብር ማስቀጠልና ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል። በቀጠናው ፅንፈኛ ታጣቂ ሃይሎች እየፈጠሩ ያሉትን አሳሳቢና እየጨመሩ ያሉ ስጋቶችን በመገምገም መሪዎቹ በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ትብብር ለማጠናከር ለጸጥታ ተቋሞቻቸው መመሪያ ለመስጠት ተስማምተዋል።
- በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ማጠናከር ያለውን ጠቀሜታ ላይ ተወያይተዋል ፤ አጽንኦትም ሰጥተዋል። የበለጠ ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትብብር በማድረግ የንግድ ልውውጥን ለማሳለጥ እና የጋራ ብልጽግናን ለመፍጠር የመሰረተ ልማት ትስስሮችን ለማስፋት ተስማምተዋል።
- ለአንካራው ስምምነት በጓደኝነት እና በአብሮነት መንፈስ ቁርጠኝነታቸውን ዳግም ያረጋገጡ ሲሆን በስምምነቱ ላይ የታቀዱትን የቴክኒክ ድርድሮችን ለማፋጠንም ተስማምተዋል።
#Ethiopia #Somalia #Peace
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
የብሽሽቅ ፖለቲካ😳😳
የሶማሊያው ኘሬዝዳንት አዲስ አበባ ሲገቡ የግብጽ የኤርትራና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች በግብጽ የሶማሊያን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ እንሰራለን ሲሉ መግለጫ ሰጥተዋል።ሶሚሊያ በመሪዋ አዲስ አበባ ኤርትራና የሶማሌ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር በካይሮ ተሰይመዋል። ግን ቀመሩን ያወቀ ጨዋታውን ያሸንፋል። ድል ለታለቋ ኢትዮጵያና ህዝቦቿ ተመኘሁ ሰላም🙏🇪🇹🙏
