የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
5 344
Subscribers
-22624 hours
-2 2007 days
-2 65830 days
Posts Archive
ሰበር ዳጉ ....💙 💚
እንደ ሶማሊላንድ ሁሉ ራስ ገዟ ፑንትላንድ ኢትዮጵያ የባህር ዳርቻዎቼን አልምታ መጠቀም ትችላለች እኛ በየትኛውም ኢትዮጵያ ወጪ ገቢ ላይ ምንም አይነት ቀረጥ አንጥልም ብላለች።
ፑንትላንድ በምታሳያቸው እንቅስቃሴ ክፉኛ ያናደዳቸው የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ለፑንትላንድ መንግስት የማስጠንቀቂያ መልዕክት መላካቸው ተገልጿል።
ሰሞኑን ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ የምታሳየው ፍቅር፦ እኛም እንደ ሶማሊላንድ ሀገር የመሆን እውቅና እንፈልጋለን ይመስላል። የፑንትላንድ ፕሬዝደንት ቀጣይ ሳምንት በሚያከብሩት በዓላሲመት ላይ እንዲገኙ ጠ/ሚ አብይ መጋበዛቸው ይታወቃል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኞ ጥር 13 ቀን 2016 ዓ.ም
በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የብላቴ ማሰልጠኛ ማዕከል የአየር ወለድ ትምርት ቤት በራሪ ነብር የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዝላይ ላይ ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቅዳሜ ጥር 11 ቀን 2016 ዓ.ም
"የማንንም ፍቃድ አንጠይቅም!"
አምሳባደር ሬድዋን ሁሴን
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ የባህር በር ለማግኘት እና ወደብ ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ከፈፀመችበት ዕለት አንስቶ ከሶማሊያ የህዝብ እንደራሴዎች ተነስተው ከተስተጋቡ ውጥረት ጫሪ ሀሳቦች በኋላ ኢትዮጵያ ያላትን የሰላም እና አብሮ የማደግ አቋም በማስገንዘብ ቀጥላለች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጥር 09-2016 ዓ.ም በመከላከያ ውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ተቀማጭነታቸውን በኢትዮጵያ ላደረጉ የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች የአህጉራዊና የዓለም አቀፍ ተቋማት ባለድርሻ አካላት በአገራዊና ቀጠናዊ ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ በመስጠት የመንግስትን አቋም አሳውቀዋል።
በኢትዮጵያና በሶማሊላንድ መካከል የተካሄደው የወደብ ማልማት ስምምነት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ሆና የቆየችውን አገራችንን በሊዝ የወደብ ባለቤት የሚያደርጋት እንደሆነ እና ይህንኑ ለመተግበርም ኢትዮጵያ የማንንም ፍቃድ እንደማትጠይቅ በአፅንኦት አስምረዋል።
ሀያላኑ አገራት በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎሜትሮችን አቋርጠው የጦርሰፈር ለመገንባት በሚቀራመቱበት የቀይ ባህር ቀጠና በመቶ ኪሎሜትሮች ርቀት ላይ የምትገኘዋ ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነውም ብለዋል።
'ኢትዮጵያ ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በጅቡቲ ወደብ በኩል የገቢ እና ወጪ ንግዷን እያከናወነች ዘልቃለች።'' ያሉት የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚንስትሩ በአለም ላይ እየተስተዋለ ያለውን ተለዋዋጭ የኢኮኖሚ ሚዛን በሚያመጣጥን መልኩ የራስን ወደብ መገንባትን ዓላማ ያደረገ እንጂ ማንንም ወገን ለመጉዳት ያለመ አለመሆኑን በማሳያዎች አብራርተዋል።
የተደረሰው ስምምነት ለሶማሊላንድ የአገርነት እውቅናን ከመስጠት ጀምሮ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በሁለትዮሽ መግባባት መመለስን መሰረት ያደረገ ቢሆንም ከዚህ ተፃራሪ በሆነ መልኩ በሶማሊያ መንግስትና በአንዳንድ የግጭት ጠንሳሽ አካላት የተሳሳቱ መረጃዎች በመሰራጨት ላይ መሆናቸውንና በኢኮኖሚያውና ገበያ መርህ ስምምነትም ኢትዮጵያ አገራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ከቀጠናው አገራት ጋር ያላትን ውህደት የሚቃረን በመሆኑ መስተካከል እንዳለበትም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መለያና አርማ የሆነው የመከላከያ ሰራዊታችን ለሶማሊያ ሰላምና ለህዝቦቿ አንድነት በምንም የማይተመን ከፍተኛ የመስዋዕትነት ዋጋ እንደከፈለና አሁንም በተልዕኮው ተግቶ እንደሚገኝ ያብራሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ልክ እንደከዚህ በፊቱ ሁሉ ከሶማሊያም ሆነ ከቀጠናው አገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነትና በአብሮነታዊ አንድነት መርህ ላይ የተመሰረተ ትብብር እንደምታደርግ አስታውቀዋል።
''በወደቡ ላይ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ አለኝታ የሆነ ባህር ሃይል ይገነባል ፤ የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ትንሳኤም በቀይባህር ላይ በሚገነባው የባህርሀይል ጦርሰፈር ይበሰራል።'' ብለዋል።
አምባሳደር ሬድዋን የሽብርተኞች መተላለፊያ በሆነው የቀይባህር ሰርጥ የአልሸባብንና የሃውቲ አማፂያንን ህልውና ለማክሰም በበብ ኤልመንደብና ዙሪያ ገባዎቹ የሚያንዣብበውን ተገማች ውጥረት ለማርገብ የአፍሪካ ቀንድ መገለጫ የሆኑትን የሽብርተኝነት አደጋ የባህር ላይ ውንብድና ህገወጥ የሰዎችና የጦርመሳሪያ ዝውውርን ለመግታት ብሎም በቀጠናው ሰላምና መረጋጋት በመፍጠር ሂደት የኢትዮጵያ ባህርሀይል ሚናውን በተገቢው እንዲወጣ የሚያደርግ እንደሆነም በኩራት ገልፀዋል።
በመጨረሻም አሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚንስትሩ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በአፍሪካ ቀንድም ይሁን በአህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ኢትዮጵያ ያላትን ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል እና አገራዊ ፣ ክፍለ አህጉራዊና አህጉራዊ ተጠቃሚነቶችን ለማስፈን የማንንም መልካም ፍቃድ እንደማትጠይቅና ለዚህም በማንም እንደማትገደድ ይህንን ለማስጠበቅም የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በመላክ በቃሉ
ኢትዮጵያ ከታጠቀችው ዘመናዊ ድሮዎኖች ውስጥ አንዱ ቱርክ ሰራሹ እረጅም እርቀት የሚጏዘውና 24 ሰአት በአየር ላይ ቅኝት በማድረግ ኢላማውን የሚመታው Bayraktar long distance Akinci UAV
የ5ኛ ትውልድ ትጥቆችን በጀግንነት ተደምረን ታጥቀናል። ለጠላቶቻችን ድንጋጤን ለህዝባችን ደግሞ መመኪያ ጋሻ መሆኑን የኢፌዴሪ አየር ሃይል አስመስክሯል።
" ክብር ለሰማያዊ ንስሮች "
የኢትዮጵያ አየር ሀይል “su-30” ተዋጊ ጀቶችን መታጠቁን አስታወቀ!
ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ su-30 ተዋጊ ጀቱን በማብረር የተለያዩ የአየር ላይ ትእይንቶችን አሳይተዋል
የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዘመናዊ የሆነውን የsu-30 ተዋጊ ጀቶችን እና የስትራቴጂክ ሰው አልባ ተዋጊ አውሮፕላኖችን መታጠቁን አስታወቀ።
የsu-30 ተዋጊ ጀቶች እና የስትራቴጂክ ሰው አልባ ተዋጊ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) የመጀመሪያ ዙር ርክክብ በዛሬው እለት መከናወኑን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል
ርክክቡ ላይ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፣ “በአለማችን ላይ ተመራጭ የሆኑትን የsu-30 እና የስትራቴጂክ ሰው አልባ አውሮፕላን ባለቤት መሆናችን በሀገራችን ላይ ሊቃጡ የሚሞከሩ ጥቃቶችን ለማክሸፍ ወሳኝ ናቸው” ብለዋል።
የ5ኛ ትውልድ አካል የሆኑት ዘመናዊ ተዋጊ አውሮፕላኖችና የስትራቴጂክ ስው አልባ አውሮፕላኖች አየር ሀይሉን የማዘመን አንዱ አካል መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ “አንጋፋው የኢትዮጵያ አየር ሀይል በአፍሪካ በውጊያ አቅሙ፣ በጀግንነቱና በትጥቁ የነበረውን ዝና ዘመኑ በሚጠይቀው መልኩ ለማዘመን እየተሰሩት ያሉት ስራዎች ውጤታማ እየሆኑ ነው” ብለዋል።
የኢፌዴሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ “ተቋሙ የተረከባቸው ዘመናዊ የጦር ጀቶች በተመሳሳይ ጊዜ በአየርና በምድር ላይ ያለ የጠላት ታርጌትን ማውደም የሚችል ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በተጨማሪም “ኢትዮጵያ የተረከበቻቸው ዘመናዊ የስትራቴጂክ ሰው አልባ ተዋጊ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) የጠላትን ዒላማ የማይስቱ ናቸው” ሲሉ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር ሀይል “su-30” ተዋጊ ጀቶችን መታጠቁን አስታወቀ
ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ “የsu-30 ጄትና የስትራቴጂክ ሰው አልባ አውሮፕላን ባለቤት ሆነናል” ብለዋል። ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ su-30 ተዋጊ ጀቱን በማብረር የተለያዩ የአየር ላይ ትእይንቶችን አሳይተዋል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://bit.ly/4aQpRD8
ዛሬ የሚደረጉ ተጠባቂ ጨዋታዎች ጨዋታዎች
🏴በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ
04:30 | ዌስተሀም ከ አርሰናል
04:45 | በርንማውዝ ከ ሊቨርፑል
04:45 | ቼልሲ ከ ብላክበርን
04:45 | ኤቨርተን ከ በርንሌይ
04:45 | ኢፕስዊች ከ ፉልሀም
05:15 | ማንቸስተር ዩናይትድ ከ ኒውካስትል ዩናይትድ
🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
09:00 | አዳማ ከተማ ከ ድሬደዋ ከተማ
12:00 | መቻል ከ ሀምባሪቾ ዱራሜ
🇮🇹በጣልያን ኮፓ ኢታሊያ
11:00 | ጅሮና ከ ሬጂያና
02:00 | ሊቼ ከ ፓርማ
05:00 | ዩድንዜ ከ ካግላሪ
🇪🇸በስፔን ኮፓ ዴላ ሬ
08:00 | አትሌቲክ ዴ ሉጎኔስ ከ ራዮ ቫልካኖ
08:00 | ባዳሎና ፉቱር ከ ካዲዝ
08:00 | ሳን ሮክ ከ ጅሮና
02:00 | ታርዲንት ከ ሄታፈ
04:30 | ሄርናን ኮርቴስ ከ ሪያል ቤቲስ
05:30 | UE ሩቢ ከ አትሌቲክ ቢልባዎ
🇩🇪በጀርመን DFB ፖካል
02:00 | ዶርትሙንድ ከ ሆፈናየም
02:00 | ፍራይበርግ ከ ፓደርቦርን
02:00 | ሳንድሃውሰን ከ ባየር ሌቨርኩሰን
04:45 | ሄርታ በርሊን ከ ሜንዝ
04:45 | ቪክቶሪያ ኮለን ከ ፍራንክፈርት
04:45 | ሳርብሩከን ከ ባየር ሙኒክ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም
በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ከክፍለ ጦሮች ለመጡ ሴት የሠራዊት አባላት በስርዓተ-ፆታ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በስልጠናው የተገኙት የመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ሴቶች በተሰማሩበት የስራ መስክ ሁሉ ውጤታማ እና ጀግና መሆናቸውን በመግለፅ ሴት የሠራዊት አባላት በውትድርናው ሙያ ለሀገራቸው ተሰልፈው ተላላቅ ድሎችን እያስመዘገቡ የሚገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል።
በኮማዶና አየር ወለድ ዕዝ ውስጥ የምትገኙ ሴት የሠራዊት አባላትም ከሁሉ ፈታኝ የሆነውን የኮማንዶ፤ የአየር ወለድና እና የፀረ-ሽብር ልዩ ኃይል ስልጠናን በብቃት ተወጥታችሁ ሀገራዊ ግዳጆቻችሁን የፈፀማችሁ ጀግኖች ናችሁ ያሉት ዳይሬክተሯ ሴቶች ራሳችሁን በትምህርት መገንባት እና የአመራር ብቃታችሁን ማሳደግ አለባችሁ ሲሉ ጠቁመዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው ሰይድ በበኩላቸው የተሰጠውን ስልጠና አስፈላጊነት ገልፀው ሴቶች እንደ ጀግንነታቸው ራሳቸውን በማብቃት አዋጊ አመራር ሆነው መውጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ስልጠናውን የሰጡት በመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት የትምህርትና ስልጠና ቡድን መሪ ወይዘሮ አስተዋይ ዳንኤል ስልጠናው በስርዓተ-ፆታ ጉዳዩች በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር እና የአይችሉምን መንፈስ ለመሥበር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት እሁድ ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
"ወደኃላም ተመልከት ወደፊትም ተልም ዛሬን
ግን የሚያበላሽ አይሁን"
ዛሬ ቱርክ /ቱርክዬ/ የሪፐብሊክ ይፋዊ ምስረታ 100ኛ ዓመቷን በድምቀት እያከበረች ነው።
ይህ ማለት ግን የቱርካዊያን ታሪክ በመቶ ዓመት የተገደበ እንዳልሆነ ይታወቃል።
በዓለም በበረቱ ጦረኞቾ ተንሰራፍቶ የነበረው የኦቶማን ቱርክ ኢምፓየር ስንቱን ያካልል እንደነበር የዓለምን ታሪክ በጥቂቱ ማገላበጥ ይበቃል።
ታዲያ ከእዚህም ከዚያም በግድ የተጠቃለሉ ሀገራት ህዝቦች ነጻነትን መሻት የወለደው ትግል የኦቶማን ቱርክን ኢምፓየር ሲያንኮታኩተው የአሁን ቅርጿን ይዛ ህልውናዋን ማስጠበቅና መዝለቅ እንድትችል አንድ ልበ - ብርሃን መሪ ተፈጠረላት።
አታ ቱርክ/የቱርክ አባት ብለው ቱርካዊያኑ በበዛ ፍቅር የሚያንቆለጳጵሱት ያኔው መሪያቸው "ያረጀን ታሪክ እያላዘኑ ተስፋ መቁረጥ ያለንን ያሳጣናልና ዛሬ የቆምበት ላይ አዲስ ታሪክ በአዲስ መንፈስ እንስራ" ብሎ ሃገሬውን አነቃነቀው።
በአውሮፓ ውስጥ ሆና በብዙ ነገሮች ከአውሮፓዊያን ሀገራት የምትለየው ቱርክ በአታ ቱርክ አስተምህሮ ተግዳሮቶችን ሁሉ በጣጥሳ በማለፍ ዛሬ ላይ በእሷነቷ ቀለም የምታንጸባርቅ ታላቅ ሀገርነቷን አስመስክራ ይኸው ዛሬ የመቶኛ ዓመት ክብረ-በዓሏን እየዘከረች ትገኛለች።
ዛሬ ላይ ቱርክ ከራሷ አልፋ ስለሌሎች መብትና ጥቅም መሞገት የሚያበቃትን ሁለንተናዊ አቅም የፈጠረችና ይህንን አቅሟን በየጊዜው እያሳደገች የምትገኝ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሀገር የመሆን ወግ ማዕረግ ተጎናጽፋ ትገኛለች።
ከዚህች ታሪከ-ብዙ ሀገር በብዙ መማር ይቻላል።
ትላንት ሆኖ ያለፈን ታሪክ መመልከት ጠቃሚ ነገሮችን ለመውሰድና የማይጠቅምን ለመጣል እንጂ፤የትላንት እስረኛ በመሆን ዛሬን ለማበላሸት መሆን የለበትም።
እኛ የኢትዮጵያ ወታደሮች በየራስ ትርክት የሀገር ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅምን የሚጎዳ ቀውስ ጠማቂዎችን አንታገስም።
ለሀገርና ህዝብ ቆመን በቃል-ኪዳናችን ጸንተን ስለ ሰላም መስዋዕት የምንከፍለው፤ የኢትዮጵያንና ዜጎቿን ዛሬ ለማበላሸት ያሰፈሰፉ የሀገር ጠንቆችን አደብ ለማስገዛት ነው።
የኢትዮጵያን ህልውና ከሚገዳደር ፣ የህዝብን ሰላም ከሚያደፈርስ የትኛውን ሃይል ሀገርን መከላከል ወሳኝ ተልዕኳችን ነው።
ተልዕኳችንንም በህግና በህግ ብቻ ተመስርተን እየተወጣን የጀመርነውን ሁሉ በድል እየየቋጨን እንቀጥላለን።
የመስዋዕትነታችን ድምር ውጤትም ሀገራዊ ችግሮቻችን እየተወገዱ የዛሬያችንን ንጋት እያቀረበ ሰላማዊት በዕድገት መም በፍጥነት የምትሮጥ ታላቋን ኢትዮጵያ እንደሚያዋላድልን በልበ - ሙሉነት የምናምንበት እውነታችን ነው።
ወደኃላ መመልከት ክፋት የለውም። ወደፊትን መተንበይም ትክክል ነው።
ነገር ግን የኃላው ትውስታም ሆነ የወደፊቱ ትንቢት የኢትዮጵያችንን ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም ማሳካት የሚያስችል ጠቃሚ የታሪክ እውነተኛ ውል ጫፍ ለማግኘት እንጂ ዛሬያችንን የሚያበላሽ መሆን እንደሌለበትም እናስባለን።
በአስቻለው ሌንጫ
