የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
5 066
Subscribers
-25624 hours
-1 8217 days
-3 02830 days
Posts Archive
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማደስ እና ሀገሪቱን ለማገዝ መወሰኑን ኢትዮጵያ በበጎ እደምታየው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ኢትዮጵያ በፕሪቶሪያ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ትልቅ እምርታ ማስመዝገቧን እ.ኤ.አ ሚያዚያ 24 ቀን 2023 መግለጫ ማውጣቱን ጠቅሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ኢትዮጵያ ከህብረቱ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ብዙ ጥረት ስታደርግ መቆየቷን እና ይህ የህብረቱ ውሳኔም ወደላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርገው ሚኒስቴሩ ጠቅሷል፡፡
ህብረቱ መደበኛውን የባለብዙ- አመላካች አመታዊ ፕሮግራምን እንደገና ለማንቀሳቀስ መወሰኑ፣ አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ የማረጋጋት ጥረት እንዲደግፉ ማበረታታቱን እና አበዳሪ ተቋማትም የእዳ አከፋፈል ሽግሽግ እንዲያደርጉ ጥሪ ማድረጉን ኢትዮጵያ በበጎ እንደምትቀበለው አስታውቋል፡፡
ኢትዮጵያ ሰላሟን በማጠናከር፣ በጦርነቱ የተጎዳውን የህብረተሰብ ክፍል መልሶ በተማቋቋም፣ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያዎችን እና የአየር ንብረት ለውጥን ሊቋቋም የሚችል እድገትን ለማሳካት ጥረት በምታደርግበት ወቅት ወዳጅ አገሮች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ መሆናቸውንም መግለጫው ያመለክታል፡፡ የአውሮፓ ህብርት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ፣ በቀይ ባህር እና አካባቢው ቁልፍ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን እና አገሪቱ ወደ ዘላቂ ሰላም የምታደርገውን ጉዞ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አመላክቷል።
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
⚽ 📰 የረቡዕ ምሽት የዝውውር ወሬዎች፡ ፊሊፕስ፣ ሉካኩ፣ ፖቸቲኖ፣ ፓልሂንሃ፣ ኦናና፣ ኬፓ፣ ግራቨንበርች |የቢቢሲ ስፖርት ወሬዎች
🆕➥ ሊቨርፑሎች የማንቸስተር ሲቲውን አማካይ ካልቪን ፊሊፕስን በክረምቱ ማስፈረም ይፈልጋሉ። ለየ27 አመቱ እንግሊዛዊ ኢንተርናሽናል ዝውውር እስከ 35 ሚሊዮን ፓውንድ ለማቅረብ ፍቃደኞች ናቸው። (Star)
🆕➥ ቼልሲዎች በኢንተር ሚላን በውሰት ሰጥተውት የሚገኘውን ቤልጄማዊው አጥቂ ሮሜሉ ሉካኩ ጋር ሲዝኑ ሲጠናቀቅ ይወያያሉ። የ29 አመቱ ተጫዋች በአዲሱ አሰልጣኝ ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ ስር የሰማያዊውን ህይወቱን ማደስ ይፈልግ እንደሆነ ከአሰልጣኙ ጋር እንዲነጋገርና በወደፊት ቆይታው እንዲወስን ይደረጋል። (ቴሌግራፍ - የደንበኝነት ምዝገባ ያስፈልጋል)
🆕➥ ጊዜያዊ የቼልሲ አለቃ ፍራንክ ላምፓርድ ስራውን ለተጠባቂው አርጀንቲናዊ አሰልጣኝ ፖቸቲኖ የሚጠበቀው ሽግግር በተቻለ መጠን ለስላሳ እንዲሆን ለመርዳት ሲል ስለ ሰማያዊዎቹ ቡድን አሁናዊ ሁኔታ ከፖቸቲኖ ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል። (ኢቭኒንግ ስታንዳርድ)
🆕➥ እንግሊዛዊው አማካኝ ሜሰን ማውንት ኮንትራቱ ሊጠናቀቅ አንድ አመት ብቻ የቀረው ቢሆንም፣ እስካሁን በቼልሲ የሚያቆየውን አዲስ ኮንትራት ሊፈራረም አልቻለም። ሊቨርፑል፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ኒውካስል የ24 አመቱን ተጫዋች ማስፈረም ይፈልጋሉ። ቼልሲዎች ለዝውውሩ እስከ 70 ሚሊዮን ፓውንድ ይጠይቃሉ። (ሜል ስፖርት)
🆕➥ ቶተንሃም ፣ቼልሲ እና ማንቸስተር ዩናይትድ የፉልሃሙን ፖርቹጋላዊ አማካይ ጆአዎ ፓልሂንሃ በክረምቱ ለማስፈረም ተዘጋጅተዋል። (ፉትቦል ኢንሳይደር)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ !
🆕➥ ቼልሲዎች የካሜሮኑን ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናናን ከኢንተር ሚላን የማስፈረም ፍላጎት አላቸው። ለዚህም የ28 አመቱን ስፔናዊ ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋን እንደ የስምምነቱ አካል ሊጠቀሙበት ይችላሉ። (ጋዜታ ዴሎ ስፖርት - በጣሊያንኛ)
🆕➥ ከሊቨርፑል ጋር ስሙ ሲነሳ የነበረው ሆላንዳዊው አማካኝ ሪያን ግራቨንበርች በሚቀጥለው የውድድር አመት በባየር ሙኒክ ያለውን ቆይታ ተጠይቆ ማረጋገጥ ያልቻለ ሲሆን፣ በክለቡ ለተጨማሪ አመት ለመቀጠል የመጫወት ዕድል እንዲሰጠው እንደሚፈልግ ተናግሯል። የ20 አመቱ ወጣት አማካይ በጀርመኑ ክለብ ያለው ቆይታ ላይ በሲዝኑ መጨረሻ ምላሽ ይጠብቃል። (ቮትባል ኢንተርናሽናል - በሆላንድኛ)
🆕➥ የኒውካስል ዩናይትዱ አለቃ ኤዲ ሃዌ በክረምቱ የአርሰናሉን ስኮትላንዳዊው የግራ መስመር ተከላካይ ኪይራን ቲየርኒን ለማስፈረም ከክረምቱ የ150 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር በጀታቸው ውስጥ እስከ 25 ሚ. በመክፈል ከአርሰናል ሊያስፈርሙት ይፈልጋሉ። (ስታር)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ !
🆕➥ በተጨማሪም ኒውካስሎች የ24 አመቱ የሮማውን ብራዚላዊ የመሀል ተከላካይ ሮጀር ኢባኔዝ እየተከታተሉ ነው። (ኒኮሎ ሺራ)
🆕➥ በሌላ የኒውካስል ዜና የ26 አመቱን ፈረንሳዊ የክንፍ መስመር ተጫዋች አለን ሴንት-ማክሲሚንን በዚህ ክረምት ለመሸጥ አስበዋል። (ፉትቦል ኢንሳይደር)
🆕➥ የሪሴ ጀምስ የጉዳት ሪከርድ ሪያል ማድሪዶች የቼልሲውን እንግሊዛዊ የቀኝ ተከላካይ ላይ ፍላጎታቸው እንዲቀዘቅዝ ያደርጋቸዋል። ተጭዋቹ የሲዝኑን ቀሪ ጨዋታዎች በጉዳት እንደሚያመልጡት መነገቱን ተከትሎ፣ የ23 አመቱን ተጫዋች ለማስፈረም ሙከራ እንዳያደርጉ ሊያደርጋቸው ይችላል ተብሏል። (AS - በስፓኒሽ)
🆕➥ ባርሴሎና የ35 አመቱን አርጀንቲናዊ የፊት መስመር ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲን ከፓሪስ ሴንት ዠርሜይን ለማስፈረም በሚያደርጉት ጥረት ላይ ዝውውሩ እንዲሳካ 'የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም'። ነገር ግን ስምምነቱን ለማጠናቀቅ ቀላል አይሆንም። (90 ደቂቃ)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ !
🆕➥ የብሬንትፎርዱ አለቃ ቶማስ ፍራንክ የ20 አመቱ ስኮትላንዳዊ ተከላካይ አሮን ሂኪ በክረምቱ ወደ ማንቸስተር ሲቲ ሊያቀና ይችላል የሚለውን ወሬ አጣጥለውታል። (ስካይ ስፖርት)
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትዶች የስፔናዊውን ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴሂያ ጋር በክለቡ የሚያቆየውን አዲስ የረዥም አመት ኮንትራት ሊስማሙ ተቃርበዋል። ግብ ጠባቂው ቀደም ሲል ይከፈለው የነበረውን 375ሺ ሳምንታዊ ደሞዝ ለመቀነስ የተስማማ ሲሆን፣ አሁንም ዩናይትዶች በእግሩ መጫወት የሚችል ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ወደ ገበያው እንደሚወጡ ይጠበቃል። ( ኤክስፕረስ )
🆕➥ ሬንጀርሶች የውድድር ዘመኑን ከክሪስታል ፓላስ በውሰት በማንቸስተር ዩናይትድ ያሳለፈውን የ30 አመቱን የቀድሞ የእንግሊዝ ግብ ጠባቂ ጃክ በትላንድን ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል። (ስኮትላንድ ስታር)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ !
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትዶች የ28 አመቱን የዲናሞ ዛግሬብ ተጫዋች ክሮሺያውን ግብ ጠባቂ ዶሚኒክ ሊቫኮቪች ለማስፈረም የውል ማፍረሻውን 10 ሚሊየን ዩሮ (£8.8m) ለመክፈል ተዘጋጅተዋል። (ስፖርትስኬ ኖቮስቲ - በክሮሺያኛ)
🆕➥ አርቢ ላይፕዚግ ለስፔናዊው አጥቂ ዳኒ ኦልሞ የመጨረሻ የኮንትራት ማራዘሚያ አቅርበዋል ፣የአሁኑ ስምምነቱ በ2024 ክረምት ያበቃል ፣ነገር ግን ተጭዋቹ የጀርመኑ ክለብ የቀረበለትን አዲስ ኮንትራት ላለመፈረም ከመረጠ የ24 አመቱን ተጭዋች በዚህ ክረምት መሸጥ ይፈልጋሉ። (ስካይ ስፖርት ጀርመን)
🆕➥ የሬክስሃም የጋራ ባለቤት ሮብ ማክኤልሄኒ የ33 አመቱ የቀድሞ የዌልስ አጥቂ ጋሬዝ ቤል ከጡረታ ወጥቶ በሊግ ሁለት ለቀይ ድራጎኖች እንዲጫወት ለማሳመን ሙከራ በማድረግ ላይ ናቸው። (ዌልስ ኦንላይን)
🆕➥ የቀድሞ የአርሰናብ ሌዠንድ ሬይ ፓርሎር ስለ ዲክላን ራይስ ቀጣይ ክለብ: “በቀጣይ ሲዝን በእርግጠኝነት የአርሰናል ተጭዋች ይሆናል። ይህ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለኝም”
🆕➥ ኤርሊንግ ሃላንድ፡ ፔፕ ጋርዲዮላ፡ ሚኬል አርቴታ፡ ቡካዮ ሳካ፣ ከአስር አመታት ታላላቅ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች አንዱ፣ በዛሬ እሮብ ምሽቱ ጫወታ የሻምፒዮንሺፕ ተቀናቃኞቹ ማን ሲቲ እና አርሰናል መካከል በሚደረገው ጨዋታ ምን ይጠበቃሉ? አስተያየትዎን ያካፍሉን?
📌 ከተመቻችሁ LIKE
📌 ወሳኝ ሆኖ ካገኙት SHARE
📌 አስተያየት ካላችሁም INBOX አድርጉልን!
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ለዘላቂ ሠላም የሠራዊት ግንባታ ሂደትን በተመለከተ ከመከታ መፅሄት ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ የመጨረሻ ክፍል እነሆ ፦
ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ የኢትዮጵያ ሕዝብም መረጃን አጣርቶ መቀበል እንዳለበት የእኩያን ዱካ ተከትሎ መንጎድ ለውድቀት እንደሚያደርገው መገንዘብ እንደሚኖርበት ያሳስባሉ፣ አስከትለውም የጠላቶቻችን ፍላጎት እኛን መከፋፈልና ማፋጀት ነው። መከፋፈልና መፋጀት ደግሞ ሁሉንም ተሸናፊ ያደርጋል።
ኢትዮጵያውያን ከሊቢያዊን መማር አለብን"ሲሉም ይመክራሉ:ስለ ሁኔታው ሲያብራሩም ‹‹የሊቢያው መሪ ኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊ ምድረ በዳ የነበችውን ሊቢያን ምድራዊ ገነት አደርገዋት ነበር፡፡ የዜጎቿንም ሕይወት በእጅጉ ለውጠዋል፤ በአንድ ወቅት ያች ሀገር ብዙዎች ለእርዳታ ደጇን የሚጠኑ ሆና ነበረ።
ለአፍሪካ ህብረት በጀት የምትመድብ፣ ቤትና መኪና ለዜጎቿ በነፃ የምታበረክት፤ የበለፀጉ ዜጎች መኖሪያ የሆነችውን ሊቢያን ዛሬ ምድራዊ ሲኦል ያደረጋት የጠላቶቿ ሴራ ነው። ለሌላ ይተርፉ የነበሩ ዜጎቿ ለስደት ተደርገዋል።ሃብታቸው በውጪ ሐይሎችና በወሮበሎች ተዘርፏል፤ አሊያም ወድሟል፡፡ ሐገረ መንግስታቸውን መልሰው መገንባት ተስኗቸው እርስ በርስ እየተላለቁ ነው፤ ጠላቶቻቸው ወዳጅ መስለው ኘሬዚዱንቱን ጭራቅ አድርገው ለሊቢያዊያን ነገሯቸው። ስልጣን ፈላጊ ዜጎችም ከውጪ ጠላት ጋር ተባብረው በሐገራቸው ላይ ዘመቱ።
ከዚያም መሪያቸውን ገደለው ወይም አስገደለው ሀገሪቱን ወደማትወጣው አዘቅት ውስጥ ከተቷት። ኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊ በውጪ ሐይሎቸ በጠላትነት የተፈረጁበት ዋነኛው ችግር ግን እንደ ሊቢያዊ መሪ ለሊቢያ ብሔራዊ ጥቅምና ለዜጎቿ ዕድገት ማሰባቸው ነበር።
የእኛም ሕዝብ ከሊቢያ ውድቀት ተምሮ ከጠላቶቹ ሴራ ራሱን ሊጠብቅ ይገባል›› በማለት የሚያሳስቡት ፊልድ ማርሻል ብርሐኑ ጁላ ለኢትዮጵያ ወጣቶች ባስተላለፉት መልዕክት "ወጣቱ ሰራዊቱን ቢቀላቀል ሐገሩንም የሚያገለግልበት፤ እራሱንና ቤተሰቡንም የሚጠቅምበት ዕድል ይገጥመዋል፤ውትድርና በዲሲፕሊን ለመታነፅና በጠንካራ ሰብዕና ለመንባት ዕድል ይሰጣል፡፡
በውትድርና ውስጥ ያለፉ ሰዎች ለችግር በቀላሉ የማይበገሩ ስለሆነ ፈተናን ተቋቁመው ለስኬት መብቃት ይቻላቸዋል:: የቀድሞ ሠራዊት አባላትን እንደ ምሳሌ ብንወስድ ከተበተኑ በሗላ አብዛኞቹ ተጣጥረው ለተሻለ ሕይወትና ስኬት በቅተዋል::
ነጋዴዎች:ኢንቨስተሮች፣ኢንጀነሮች፣የግብርና ባለሙያዎች የሆኑትን ብዙዎችን እናውቃለን::
ብዙዎቹ መልካም ስነምግባር ያላቸው፣ ዕውቀትን የተላበሱ በማሕበራዊ ሕይወታቸውና በተሠማሩበት የሥራ መስክ ምስጉኖች የሆኑ ናቸው:: ይሕን ባሕሪ የተጎናፀፉት በውትድርና ቆይታቸው ከተላበሱት ስብዕና ነው::
የዚሕ ዘመን መከላከያ ደግሞ በብዙ ረገድ በዕድገት ጉዞ ላይ የሚገኝና በርካታ ተጓዳኝ የሙያ ክሕሎትን መቅሰም የሚቻልበት ተቋም ሆኖ የተገነባ ነው::
በዛሬው መከላከያ የተለያዩ የትምሕርት ተቋማትና የሙያ ማሰልጠኛዎች አሉ:: በሲቪሉ ዓለም እንዳለው ተምረህ ሥራ አጥ የምትሆንበት (ስራ የምትፈልግበት) ሳይሆን ተምረሕ ወደ ሥራ ላይ የምትመደብበት ነው:: በተቋሙ ግብርና አለ፣ ኢንጀነሪንግ በመማር በኮንስትራክሽን ሥራ መሰማራት ይቻላል፣ የሕክምና ባለሙያ፣ ፓይለት፣ አስተዳደርና ወዘተ መሆን ይቻላል::
በመሠረታዊ ውትድርናና በዕጩ መኮንንነት በመሰልጠንም እያደጉ ሄዶ ለአመራርነት መብቃት ይቻላል:: ሰልጥኖ ሐገርን በማገልገልና ሰብዕናን ሞርዶ በመውጣት የግል ሕይወትን በተሻለ ሁኔታ መምራትም ዕድል ነው:: ውትድርና ለተወሰኑ ዓመታት ለማገልገል ውል የሚገባበት መስክ ነው:የበታች ሹም ሰባት ዓመት: መኮንን አስር ዓመት አገልግሎ መቀጠል ከፈለገ ውሉን ያራዝማል:መውጣት ከፈለገም የአገልግሎት ካሳ ተሰጥቶት በክብር ይሰናበታል::
ከዚያ መከላከያ ውስጥ ባገኘው ስልጠናና ትምሕርት በገነባው አቅምና የሥራ ልምድ ተጠቅሞ ሕይወቱን በመልካም ሁኔታ መምራት ይቻለዋል፤ በርካታ ሥራ አጦች ባሉበት አገር መከላከያ አሰልጥኛችሁና አስተምሬያቸው ሥራ ልስጣችሁ ሲል ዕድሉን አለመጠቀም ሞኝነት ነው::
በእርግጥ ባለፉት ጊዜያት ውትድርናን እንደ ዝቅተኛ ሥራ የመመልከትና ሠራዊቱንም በሕብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ካልነበረው ወይም ተቀባይነት ካጣው ፓርቲ (ኢህአዴግ) አገለጋይነት ጋር አስተሳስሮ የመመልከቱ የቆየ አመለካከት የፈጠረው አሉታዊ አስተሳሰብ አለ::አሁን ያለው መከላከያ ግን እንደዛ አይደለም:: ሁሉም በዕኩልነት የሚታይበትና በብቃቱ የሚመዘንበት፣ ውጪ አገር ሔዶ እስከመማር የደረሰ ዕድል የሚገኝበት በመሆኑ ወጣቶች መከላከያን አንዲቀላቀሉ እመክራለሁ"ብለዋል ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፡፡
ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክትም "ህብረተሰቡ የህልውናው ዘብ የሆነውን የመከላከያ ሠራዊት ማጠናከር እንዳለበትና ሰለሙን ከሚያደፈርሱ ድርጊቶች አራሱን እንዲጠብቅ አሳስበዋል:: አክለውም "ህብረተሰቡ መገንዘብ ያለበት በሀገራችንም ሆነ በሠራዊታችን ግንባታ ያለውን የመረጃ ክፍተት በመጠቀም ጠላቶቻችን የሐሰት ወሬ ያሰራጫሉ።
ትውልዱን ተጠራጣሪ ለማድረግ ስስ ብልቶችን እየለዩ ያወናብዳሉ። አሁን ባለንበት ዘመን ምቹ ሁኔታ እና ስስ ብልቶች ብሔርና ሐይማኖት ሆነዋል። ብሔርህ ተጠቃ! ሐይማኖትህ ተነካ! እያሉ መቀስቀስ የመከፋፈያ ዘዴያቸው ሆኗል፡፡ ሕዝቡ ዕውነተኛ መረጃዎችን ከሐሰተኛ መረጃዎች መለየትና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አቋም መያዝ ይኖርበታል:: ከከፋፋይ ፕሮፖጋንዳ ተጠብቀን ልማት ላይ በማተኩር ሐገራችንን ማሳደግና ከድሕነት መላቀቅ እንችላለን::
እኛ በአንድነት ከቆምን የሀገራችንን ታላቅነት የሚመጥን ሠራዊት ስለተገነባ የሚያሰጋን የውጪ ሐይል አይኖርም"ብለዋል የኢፌዲሪ ጦር ሐይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻ ብርሃኑ ጁላ፡፡
በጦር ሐይሎች ጠቅላይ መምሪያ በየሦስት ወሩ የሚታተመው መከታ መፅሔት ቁጥር 1 ዕትም የተወሰደ፡፡
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
⚽📰 የማክሰኞ ምሽት የዝውውር ወሬዎች - ኬን ፣ ራሽፎርድ ፣ ዛሃ ፣ ኔይማር ፣ ኦባሚያንግ ፣ ፊርሚኖ ፣ ማክ አሊስተር ፣ ጋቪ ፣ ላፖርቴ እና ሌሎችም ...
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትዶች የቶተንሃሙን አጥቂ ሃሪ ኬንን በክረምቱ ለማስፈረም ጥረታቸውን እያጠናከሩ ሲሆን የ29 አመቱ እንግሊዛዊ ካፒቴን ከልጅነቱ ክለብ ጋር አዲስ ኮንትራት እንደማይፈርም ይጠበቃል። (ምንጭ: ዘ ቴሌግራፍ)
🆕➥ ዩናይትዶች ኬን በክረምቱ ወደ ኦልድትራፎርድ የሚሄድ ከሆነ በስፐርስ ያለውን ወቅታዊ £200,000 ሳምንታዊ ኮንትራት ወደ £300,000 ያሳድጉለታል። (ምንጭ: ሚረር)
🆕➥ የክሪስታል ፓላስ እና አይቮሪኮስት የፊት መስመር አጥቂ ዊልፍሬድ ዛሃ በሳምንት 200,000 ፓውንድ የሚያወጣ አዲስ ኮንትራት ቀርቦለታል። የ30 አመቱ ተጨዋች በውድድር አመቱ መጨረሻ ኮንትራቱን የሚያጠናቅቅ ሲሆን የአርሰናል፣ ቼልሲ እና ፓሪስ ሴንት ዠርሜይን የዝውውር ኢላማ ነው። (ምንጭ: ጋርዲያን)
🆕➥ ኢንተር ሚላን ለካሜሩን ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና የ£35m ዋጋ አስቀምጧል። ቼልሲዎች የ27 አመቱን ተጫዋች ኢላማቸው አድርገውታል ተብሏል። (ምንጭ: ጎል)
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትዶች ብራዚላዊውን አጥቂ ኔይማርን ለማስፈረም በሚደረገው ፉክክር ቼልሲን ተቀላቅለዋል። የ31 አመቱ ተጫዋች በክረምቱ ፓሪስ ሴንት ዠርሜንን እንደሚለቅ ይጠበቃል። (ምንጭ: ፉትመርካቶ - በፈረንሳይኛ)
🆕➥ የ33 አመቱ የቼልሲ አጥቂ ፒየር ኤምሪክ ኦባሚያንግ የፖላንዳዊውን ሮበርት ሌዋንዶውስኪን ድጋፍ ለመስጠት በዚህ ክረምት በኑካምፕ የተመለሰው የባርሴሎና ከፍተኛ ኢላማ ነው። (ምንጭ: ስካይ ስፖርት)
🆕➥ የ31 አመቱ የሊቨርፑል አጥቂ ሮቤርቶ ፊርሚኖ ኮንትራቱ ሲጠናቀቅ ባርሴሎናን የመቀላቀል ፍላጎት አለው። ነገር ግን የስፔኑ ክለብ ብራዚላዊውን ኢንተርናሽናል የማስፈረም ፍላጎት የለውም። (ምንጭ: ማርካ)
🆕➥ የ24 አመቱ የብራይተን አማካኝ አሌክሲስ ማክ አሊስተር ብራይተንን በዚህ ክረምት ይለቃል። ነገር ግን እዛው በፕሪምየር ሊግ ለመቆየት አቅዷል። ሊቨርፑል የአርጀንቲናውን የአለም ዋንጫ አሸናፊ ለማስፈረም ቀዳሚ ቢሆንም ቶተንሃም፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ፣ቼልሲ እና ኒውካስልም ፍላጎት አስመዝግበዋል። (ምንጭ: 90 ደቂቃ)
🆕➥ ቦርሺያ ዶርትሙንድ በ50ሚ ዩሮ (£44m) የሚገመተውን የ23 አመቱ የቼልሲ እና እንግሊዛዊ አማካኝ ኮኖር ጋላገርን በመከታተል ላይ ናቸው። (ምንጭ: ስካይ ስፖርት ጀርመን)
🆕➥ የ18 አመቱ ስፔናዊ አማካኝ ጋቪ በባርሴሎናን አዲስ ኮንትራት ባይቀርብለትም እና ቼልሲን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ክለቦች እየተከታተሉት ቢሆንም፣ በዚህ ክረምት ኑካምፕን የመልቀቅ እቅድ እንደሌለው አረጋግጧል። (ምንጭ: ስፖርት)
🆕➥ ማንቸስተር ሲቲ ከማንቸስተር ዩናይትድ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ጋር የደቡብ ኮሪያውን የመሀል ተከላካይ ኪም ሚን-ጄን ከናፖሊ በ£40m ለማስፈረም ለመፎካከር ተዘጋጅተዋል። (ምንጭ: ሚረር)
🆕➥ የ28 አመቱ ስፔናዊ ተከላካይ አይሜሪክ ላፖርቴ በማንቸስተር ሲቲ ደስተኛ ባለመሆኑ በቋሚነት የመጫወት እድል ለማግኘት ሲል፣ ማን ሲቲን ለቆ ባርሴሎናን መቀላቀል ይፈልጋል። (ምንጭ: ሬሌቮ - በስፓኒሽ)"
🆕➥ ኒውካስል ዩናይትድ የባርሴሎናውን የቀድሞ የሊድስ ዩናይትድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ራፊንሀን ወደ ፕሪምየር ሊግ ሊመልሱት አቅደዋል። የ27 አመቱ ብራዚላዊ ኢንተርናሽናል በሴንት ጀምስ ፓርክ፣ የቱርኩ ተከላካይ አርዳ ጉለር እና የ23 አመቱ የፌነርባህቼ የአማካይ ክፍል ባልደረባው ፌርዲ ካዲዮግሉ ሊቀላቀሉት ይችላሉ። (ምንጭ: ሚረር)
🆕➥ አስቶንቪላዎች ከቶተንሃም በውሰት በቪላሪያል እየተጫወተ የሚገኘውን እና በስፔኑ ክለብ ባሁኑ በቪላ አለቃ ኡናይ ኤምሪ ስር የተጫወተውን የ27 አመቱን አርጀንቲናዊ አማካይ ጆቫኒ ሎ ሴልሶን ማስፈረም ይፈልጋሉ። (ምንጭ: ዴይሊ ሜይል)
🆕➥ ብራይተኖች አስቶንቪላ የ22 አመቱን የቫሌንሺያ ፖርቹጋላዊ አማካኝ አንድሬ አልሜዳ ለማስፈረም የሚደረገውን ፉክክር ተቀላቅለዋል። (ምንጭ: ዴይሊ ሜይል)
🆕➥ ኒውካስል ዩናይትድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ የ21 አመቱ የሊድስ ሆላንዳዊ የክንፍ ተጫዋች ክሪሴንሲዮ ሰመርቪል ሁኔታን ከሚከታተሉ ክለቦች መካከል ይጠቀሳሉ። (ምንጭ: የእግር ኳስ ኢንሳይደር)
🆕➥ ቼልሲዎች የ18 አመቱን ፖርቹጋላዊ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያጎ ሞሬራ ከቤኔፊካ ለማስፈረም ተቃርበዋል። (ምንጭ: 90 ደቂቃ)
🆕➥ የኒውካስል እና የማንቸስተር ዩናይትድ ስካውቶች የ19 አመቱ የስሎቬኒያ አጥቂ ቤንጃሚን ሴስኮ በሳምንቱ መጨረሻ ለሬድ ቡል ሳልዝበርግ ሲጫወት ገምጋሚዎቻቸውን ልከው እንቅስቃሴውን ተመልክተውታል። (ምንጭ: 90 ደቂቃ)
🆕➥ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የ16 አመቱን ክሮሺያዊ የመሀል ተከላካይ ሉካ ቩስኮቪችን ከሀጅዱክ ስፕሊት ለማስፈረም በሚደረገው ፉክክር ማንቸስተር ሲቲን ተቀላቅለዋል። (ምንጭ: ዴይሊ ሜይል)
🆕➥ አርሰናል የ23 አመቱ የዎልቭሱን ፖርቱጋላዊ አጥቂ ፔድሮ ኔቶን ለማስፈረም ፍላጎታቸውን ለማደስ ተዘጋጅተዋል። (ምንጭ: TeamTalk)
📌 ከተመቻችሁ LIKE
📌 ወሳኝ ሆኖ ካገኙት SHARE
📌 አስተያየት ካላችሁም INBOX አድርጉልን
ማክሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 17/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች
1፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ የተሻሻለውን የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ በስድስት ድምጸ ተዓቅቦ አጽድቋል። መንግሥት አዘጋጅቶ ያቀረበው የተሻሻለ ረቂቅ አዋጅ፣ ኅብረ ብሄራዊ ተዋጽዖውን የጠበቀ ዘመናዊ የአገር መከላከያ ሠራዊት ለመገንባት ማነቆ ኾነዋል የተባሉ የሕግ ማዕቀፎችን ለማሻሻል ያስችላል ተብሏል። ተሻሽሎ የጸደቀው አዋጅ፣ የሠራዊቱ አባላት የጡረታ መውጫ የእድሜ ጣሪያን አወሳሰን፣ የ12ኛ ክፍል ወይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በፍቃዳቸው ለኹለት ዓመት ብሄራዊ አገልግሎት የሚሰጡበትን አግባብ፣ የአገር ሕልውና ከባድ አደጋ ላይ በሚወድቅበት ጊዜ ከሠራዊቱ የተገለሉ የቀድሞ አባላትን መልሶ መቅጠር የሚቻልበትና ሌሎች የሠራዊቱ መብትና ጥቅማ ጥቅሞችን እንዳካተተ ተገልጧል።
2፤ በሱዳን የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሱዳኑ ውጊያ ቢያንስ ስምንት ኢትዮጵያዊያን እንደተገደሉና ሌሎች አራት ኢትዮጵያዊያን የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸው መናገሩን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ኢትዮጵያዊያኑ ለሞት እና ለመቁሰል አደጋ የተዳረጉት፣ በተባራሪ ጥይት እና ከባድ መሳሪያ አረሮች ፍንጣሪ ሳቢያ መኾኑን ኢምባሲው መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። ከአገሪቱ መውጣት የሚፈልጉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ኢትዮጵያዊያን ዜጎች በአውቶብስ ወደ መተማ ለመሸኘት እየመዘገበ መኾኑን ኢምባሲው መግለጡን የጠቀሰው ዘገባው፣ የኢምባሲው ሠራተኞች ካርቱምን ለቀው ለኢትዮጵያ ቅርብ በኾነችው የሰሜን ሱዳኗ ገዳሪፍ ከተማ ሥራቸውን እያከናወኑ መኾኑን ጠቅሷል።
3፤ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ዛሬ መቀሌ መግባታቸውን የትግራይ ክልል ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከልዩ መልዕክተኛ ሐመር ጋር በኢትዮጵያ የአሜሪካ ዋና ጉዳይ አስፈጻሚ ትሬሲ ጃኮብሰን አብረው መቀሌ ይገኛሉ ተብሏል። ሐመር ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አመልክቷል። ሐመር፣ ባለፈው ኅዳር የሕወሃት የሰላም ተደራዳሪዎችን በአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላን አሳፍረው ወደ ፕሪቶሪያ መውሰዳቸው ይታወሳል።
4፤ ትናንት በታንዛኒያ ጉብኝት ያደረጉት ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ ዛሬ በኮሞሮስ ይፋዊ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው። ደመቀ ዛሬ ከኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ ጋር ተገናኝተው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሕወሃት ጋር በደረሰበት የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ ለፕሬዝዳንቱ ገለጻ እንዳደረጉላቸው ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ፕሬዝዳንት አዛሊ፣ በአፍሪካ ኅብረት አስተባባሪነት በሕዳሴ ግድብ ውዝግብ ላይ ተቋርጦ የቆየው የሦስትዮሽ ድርድር እንዲቀጥል ጥረት አደርጋለሁ በማለት ለደመቀ እንዳረጋገጡላቸው ተገልጧል። ፕሬዝዳንት አዛሊ የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ናቸው።
5፤ አውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዘላቂ አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ ከመንግሥት ጋር ያቋረጠውን ግንኙነት ደረጃ በደረጃ እንደገና ወደነበረበት ለመመለስ ጥረት እንደሚያደርግ ትናንት ባወጣው መግለጫ በድጋሚ አስታውቋል። ኾኖም ኅብረቱ፣ በሰሜኑ ጦርነት ኹሉም ተፋላሚ ወገኖች የፈጸሟቸው ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና በሰላማዊ ሰዎችና ስደተኞች ላይ የተፈጸሙ የጦር ወንጀሎች በገለልተኛ መርማሪ አካል አማካኝነት ግልጽና ገለልተኛ ምርመራ የማድረግ ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው እጅግ አስፈላጊ ነገር መኾኑን በመግለጫው አመልክቷል። ኅብረቱ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ባሁኑ ወቅት እየታዩ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ውጥረቶችና ግጭቶች እንዳሳሰቡት ገልጦ፣ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለማስፈንችግሮቹ በፖለቲካዊ እና ዲሞክራሲያዊ አግባብ በንግግር ብቻ እንዲፈቱ ጥሪ አድርጓል። ኅብረቱ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የበጀት ድጋፍ ያቋረጠው፣ ከኹለት ዓመት ከመንፈቅ በፊት ነበር።
6፤ የሱዳን ጦር ሠራዊትና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት በአሜሪካ አደራዳሪነት ከትናንት እኩለ ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ስምምነት ካርቱም ውስጥ ከሞላ ጎደል ተግባራዊ እየኾነ መኾኑን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። በኦምዱሩማንና ሌሎች ከተሞች ግን ውጊያው እንደቀጠለ መኾኑን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የጦር ሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጀኔራል አል ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ ተገናኝተው ፊት ለፊት እንዲነጋገሩ ጥረቶች እየተደረጉ መኾኑን የግብጽ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ1241 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2066 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ3057 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ5918 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ6015 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ7935 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን🙏
👉 የቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት በማስጠበቅ በየጊዜው አለኝታነታቸውን አስመስክረዋል‼--ሌተናል ጄኔራል አለምእሸት ደግፌ
♦ የሀገርን ጥሪ ተቀብለው በግንባር ቀደምትነት በመሰለፍ ተልዕኳቸውን በድል ላጠናቀቁ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት የሽኝትና የምስጋና መርሀ ግብር ተካሂዷል።
በሽኝት መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና የሜካናይዝድ አስተባባሪ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አለምእሸት ደግፌ እንደተናገሩት፤ የሠራዊት አባላቱ በሀገር ላይ ያጋጠሙ አደጋዎችን በመቀልበስ ህዝብና መንግስት የማይረሳው አኩሪ ሀገራዊ ገድል ፈፅመዋል።
ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ሠላምና መረጋጋት የሠራዊት አባላቱ በግንባር በመሰለፍ ያደረጉት ተጋድሎ ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት ሌተናል ጄኔራል አለምእሸት፤ ተሞክሯቸውን ለተተኪ የሠራዊት አባላት በማካፈል፣ ጠንካራ ዲስፕሊንና የሀገር ፍቅርን በማላበስም ጉልህ አሥተዋፅኦ ማበርከታቸውን ገልፀዋል።
የመከላከያ ሰው ሀብት አመራር ዋና መምሪያ ሀላፊ ሌተናል ጄኔራል ሃጫሉ ሸለመ በበኩላቸው፤ የሠራዊት አባላቱ ከሁሉም በላይ ኢትዮጵያን በማስቀደም በተለያየ ጊዜ ያጋጠሙ ጠላቶችን ድባቅ በመምታት አይበገሬነታቸውን ያስመሰከሩ መሆናቸውን አውስተዋል።
በክብር የተሸኙት የቀድሞ መከላከያ ሠራዊት አባላቱ በሚሄዱበት አካባቢ ሁሉ ሠላምን በማፅናት ረገድ የበኩላቸዉን ሚና መወጣት እንደሚገባቸው ሌተናል ጄኔራል ሃጫሉ አሳስበዋል።
ሽኝት የተደረገላቸው የሠራዊት አባላት የሀገርን ጥሪ ተቀብለው ሠላምና አንድነትን ለማረጋገጥ በከፈሉት ዋጋ ኩራት እንደተሰማቸውና ወደፊትም በማንኛውም ሁኔታ ሀገራቸውን በሚችሉት ሁሉ ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።
#Ethiopia
'' መከላከያ ሚኒስቴር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች የውትድርና ስልጠና ወስደው ብሔራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ይችላል " - ዲማ ኖጎ ( ዶ/ር)
መከላከያ ሚኒስቴር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በፈቃዳቸው ወታደራዊ ስልጠና ወስደው ብሔራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ሊያደርግ እንደሚችል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) አሳውቀዋል።
ሰብሳቢው ይህንን ያሳወቁት ዛሬ የሕዝብ ተወካዮቸ ምክር ቤት የመከላከያ ሠራዊት አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ባጸደቀበት ወቅት ነው፡፡
ዶ/ር ዲማ ናጎ ምን አሉ ?
" ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዕድሜያቸው 15 ዓመት የሞላቸው እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወይም የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በፈቃዳቸው ወታደራዊ ስልጠና ወስደው ለሁለት ዓመት ብሔራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ሊያደርግ ይችላል።
ተማሪዎች በፈቃዳቸው በመደበኛ የመከላከያ ሠራዊት ወይም የብሔራዊ ተጠባባቂ ኃይል አባላት የሚሆኑ ከሆነ፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተያያዥ መብቶችንና ጥቅሞች እንዲጠበቁላቸው ያደርጋል። "
የተሻሻለው የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ ሆኖ የተጣለበትን ሀገር የመጠበቅ ተልዕኮ በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲወጣ የሚያስችል ነው ተብሏል።
የተሻለ ሠራዊት ለመገንባት ማነቆ የሆኑ ሕግ ማዕቀፎችን እና ተቋማዊ አስተሳሰቦችን በመፈተሽ ለሀገር እና ሕዝብ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ነው የተገለፀው።
ምክር ቤቱ በተሻሻለው ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1286/2015 አድርጎ በስድስት ድምጸ-ተኣቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
Via HoPR
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻለውን የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ፡፡
በረቂቅ አዋጁ የመከላከያ ሰራዊት ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የተጣለበትን ሀገርን የመጠበቅ ተልዕኮ በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲወጣ ለማድረግና ህብረ ብሔራዊ ተዋፅኦውን የጠበቀ የዘመነ ሰራዊት ለመገንባት ማነቆ የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን ለማሻሻል የተካተተበት እንደሆነ ተገልጿል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን አሁን ካለው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ለማጣጣም እንዲሁም የወደፊቱን ግዳጅ ታሳቢ ያደረገ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱም ተመልከቷል።
ይሁን እንጂ አሁን በስራ ላይ ያሉት አዋጆች በተግባር ሲፈተሹ አዳዲስ አስተሳሰቦችን ስራ ላይ ለማዋል አዳጋች ከመሆናቸውም በላይ በርካታ ክፍተቶች የሚታዩበትና የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ውጤታማነት ላይ ጫና መፍጠሩ ተጠቁሟል።
በመሆኑም ተሻሽሎ የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ያሉትን ችግሮችና ክፍተቶች በመሙላት ሊያሰራ የሚችል የህግ ማዕቀፍ፣ አደረጃጀት እና አሰራር ለመዘርጋት የሚያስችል በመሆኑ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአብላጫ ድምፅ አፅድቆታል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም
የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የክልል ልዩ ሃይሎችን በተመለከተ ከተናገሩት የተወሠደ፦
👉 ሁሉም ሃይል ሁሉም አቅም ወደ ጦርነት ስለገባ ቢያንስ ወዶ ዘማችም መዝመት ሥለነበረበት ምንም እንኳ ህጋዊ ባይሆንም የክልል ልዩ ሃይል የተደራጀ፣ የታጠቀና የሠለጠነ ሃይል ሥለሆነ ጦርነቱ ላይ አሥተዋፆ እንዲኖረው ተደርጓል፡፡
👉 መከላከያ የጦርነቱን ስትራቴጅ ፣የጦርነቱን ኦፕሬሽናል እና የጦርነቱን ታክቲካል ዕቅድ አውጥቶ ነው የተዋጋው፡፡ የክልል ልዩ ሃይሎች በዚህ እቅድ ውስጥ ገብተው የመከላከያን ቀዳዳ እየሞሉ እንዲሠሩ ተደርጓል፡፡ በዚህ መሠረት ጥሩ ሠርተዋል፡፡ ሀገራቸውን ከመፍረስ በመታደጋቸው ሊመሠገኑ ይገባል፡፡
👉 በሶስተኛው ዙር ጦርነት ላይ የአማራ ክልል ልዩ ሃይሎች በክፍለ ጦሮች ተደራጅተው ከመከላከያ በወጣው እቅድ ውስጥ በመካተት ግዳጅ እየተሠጣቸው ከመከላከያ ሠራዊቱ ጋር አብረው እየተዋደቁ ፣አብረው እየተሠው እና አብረው እየደሙ ጦርነቱ በድል እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አሥተዋፆ አበርክተዋል፡፡
👉 በሁለተኛው ዙር ውጊያ የሁሉም ክልል ልዩ ሃይሎች ተሳትፈዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ሰላሳ ሺህ ልዩ ሃይል እና ሚሊሺያ ልኳል በዉጊያም ተሳትፈዋል ፣የሱማሌ ክልል ልዩ ሃይሎችም በኦፕሬሽኑ ላይ ተሳትፈዋል ፣በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያለውን ፀጥታ ለማረጋገጥ የደቡብ ክልል፣ የጋንቤላ ክልል እና የቤኒሻንጉል ክልል ልዩ ሃይሎች ሃላፊነቱን ወሥደው ተንቀሳቅሰዋል ከፍተኛ አሥተዋፆ አበርክተዋል፡፡
👉 የሁሉንም ክልል ልዩ ሃይሎች ለሀገሪቱ በሚጠቅም መንገድ አደረጃጀቱን ቀይሮ ለማደራጀት እቅድ ወጥቶ በተቋቋመው ሃገራዊ ኮሚቴ አማካኝነት የሁሉም ክልል የበላይ አመራሮች ፣የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊዎች ፣ፖሊሥ ኮሚሽነሮች ፣የልዩ ሃይል አዛዦች ተሳታፊ በመሆን ሁሉም በዕቅዱ ተሥማምተዋል፡፡
👉 አማራ ክልል ልዩ ሃይሉ ላይ በተገቢው መንገድ ሀገራዊ መልእክቱ እንዲደርስ ያልፈለጉ ፅንፈኞች ልዩ ሃይሉ እንዲጎዳ እና እንዲበተን ተንቀሳቅሠዋል፡፡ በኃላ ላይ በጋራ ርብርብ በተሠሩ ሥራዎች ልዩ ሃይሉ በአዲሱ መዋቅር ውስጥ እንዲካተት የሚያሥችሉ ሥምምነቶች ተፈጥረዋል መልክም ይዟል፡፡
👉 እቅዳችን ላይ ትጥቅ አስፈታ የሚል አልነበረም፡፡ መከላከያ የሚገባው መከላከያ ይታጠቃል፡፡ ፌዴራል ፖሊስ የሚገባው ፌዴራል ፖሊስ ይታጠቃል፡፡ በክልል የሚቀረውም ይታጠቃል እንጂ ትጥቅ አስፈትተህ ከአንዱ ወደ አንዱ ለፌዴራል አስረክብ ያለ የለም፡፡ በዚህ ጉዳይ ከፍተኛ የፈጠራ ፕሮፖጋንዳ ተሠርቶ የማደናገሪያ አጀንዳ ሁኗል፡፡
👉 አደረጃጀቱን ቀይረን ለሀገር በሚመች መንገድ እናደራጀው ነው እንጅ ያልነው ልዩ ሃይሉ ፈርሶ ይበተን የሚል አልነበረም ፡፡ ልዩ ሃይሉ ፈርሶ ይበተን ተብሏል በሚል የተሠራጨው አፍራሽ ፕሮፖጋንዳ የተወሠነ መደነጋገር በህዝቡም በመዋቅሩም በራሱ በልዩ ሃይሉም ፈጥሯል ከዚህ በተረፈ ግን የወጣው ፕላን በሚገባ ተሠርቷል፡፡
👉 በልዩ ሃይል ሥም ከቦታ ወደ ቦታ የሚንቀሳቀስ፣ ተልዕኮ የሚቀበል እና ግዳጅ የሚቀበል ሃይል ከእንግዲህ አይኖርም፡፡ አደረጃጀቱ የመከላከያ ሠራዊት ፣የፌዴራል ፖሊስ ፣የክልል መደበኛ ፖሊስ ፣የክልል ሚሊሺያ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ የሚኖር አደረጃጀት ህገ ወጥ ነው፡፡
የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር ሚንስትር ዶክተር አብርሃም በላይ በቢሾፍቱ ከተማ ተገኝተው የኢትዮጵያ መከላከያ ዩንቨርስቲን እየጎበኙ ነው።
ዩንቨርስቲው የመማር ማስተማር ስርዓቱን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ በኮሌጆች ያሉ እጥረቶች እና ችግሮችን ለሚኒስትሩ ቀርበዋል።
የዘመናዊ ሠራዊት ግንባታን እውን ለማድረግ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩንቨርስቲ የሰለጠኑ ወታደር ሙያተኞችን በማፍራት እና አዳዲስ የፈጠራ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመስራት ተቋሙን የመደገፍ ስራ ይሰራል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩንቨርስቲ በትምህርት እና በስልጠናው ዘርፍ የኢንጂነሪንግ፣ የጤና ሳይንስ፣ የሪሶርስ ማኔጅመንት እና በምርምር ዘርፍ የምርምር ልማት ኢንስቲቲዩት በስሩ ይዞ እየሰራ የሚገኝ ዩንቨርስቲ መሆኑ ተገልጿል።
የመከላከያ ኢንዱስትሪዎችን እና ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ የሆኑ የተቋሙ ክፍሎችን በመደገፍ ረገድ ዩንቨርስቲው ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳበረከተም በውይይቱ ተመላክቷል።
በዛሬው እለትም የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ በዩንቨርስቲው የጉብኝት እና የውይይት ቆይታቸው ለቀጣይ በመማር ማስተማሩ ስርአት ላይ አቅጣጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የማራቶን ውድድሯን በመኪና ያጋመሰችው አትሌት ሜዳልያዋን ተነጠቀች!!
አትሌቷ በ48 ስአታት ውስጥ ረጅም ርቀት በመሮጥ የአለም ክብረወሰንን በያዘች ማግስት በቅሌት መዝገብ ያሰፈረ ድርጊትን መፈጸሙ አነጋጋሪ ሆኗል
የማራቶን ውድድሯን በመኪና ያጋመሰችው አትሌት ሜዳልያዋን ተነጠቀች።
የ47 አመቷ ስኮትላንዳዊ ጆሲያ ዛክሬውስኪ በብሪታንያ ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደ የ80 ኪሎሜትር የሩጫ ውድድር 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
መነሻውን ማንቸስተር አድርጎ በሊቨርፑል በተጠናቀቀው ውድድር የነሃስ ሜዳሊያ በመሸለሟም ደስታዋ ከፍ ብሎ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ምስሎችን አጋርታለች።
ያልጠበቀችውን ድል ማግኘቷ ቢያስፈነድቃትም ስጋት ያጫረባት ጉዳይ ግን ነበር፤ የውድድሩን ህግ መተላለፏን ባትዘነጋውም እንዳይደረበት ግን መጸለይ መርጣ ደስታዋን እያጣጣመች ነበር።
የፈራችው ነገር ግን አልቀረላትም፤ ስሟን የሚያጎድፈው ተግባሯ በአንገቷ ያጠለቀችው ሜዳልያንም እንድትመልስ ግድ ሆኗል።
ዛክሬውስኪን ለዚህ ያበቃት የውድድሩ አዘጋጆች ከሁለት ማራቶን የማይተናነሰውን (80 ኪሎሜትር) ውድድር ቪዲዮ እና የአትሌቶቹን ፍጥነት ሲመለከቱ ነው።
ስኮትላንዳዊቷ አትሌት በውድድሩ ለአጭር ጊዜም ቢሆን በስአት 56 ኪሎሜትር የመሸምጠጧ ነገር አጃኢብ ያሰኛቸዋል፤ ፍጥነቷ ጃማይካዊውን ዩዜን ቦልት ተክታ የአለማችን ፈጣን ሯጭ የሚያደርጋት ነውና።
ጉዳዩ ያጠራጠራቸው የውድድሩ አዘጋጆችም ቪዲዮ ሲመለከቱ ዛክሬውስኪ ውድድሩን አቋርጣ ወጥታ ዳግም የሸመጠጠችበት ምክንያት ምንድን ነው የሚል ጥርጣሬያቸው ያይላል።
የአይን እማኞችን አነጋግረው አትሌቷን ለማብራሪያ ሲጠሯትም የተፈጠረውን ነገር ሳትደብቅ ትናገራለች፤ “ውድድሩ ሲጋመስ በጣም የህመም ስሜት ተሰማኝ፤ አቋርጨውም ወደ ጓደኛዬ መኪና ውስጥ ገባሁ፤ በዚህ ወቅትም ለምን በመኪና አልሸኝሽም የሚለውን ሃሳብ ተቀበልኩ” ትላለች አትሌቷ።
የውድድሩ ማጠናቀቂያ ሲቃረብ ከመኪና ወርዳ መሮጥ መጀመሯን የምትገልጸው ዛክሬውስኪ፥ “አሞኝ መኪና ውስጥ ነበርኩ ስላቸው (ተቆጣጣሪዎቹን) ውድድሩንማ ማጠናቀቅ አለብሽ የሚል ሞራል ሰጡኝ” ትላለች።
ይሁን እንጂ በውድድሩ የነሃስ ሜዳልያ የሚያስገኝ ውጤት እንደምታስመዘግብ በፍጹም አለመጠበቋን በመጥቀስ እየመራች ያለችውን አትሌት ስትመለከት መቅደም አለመፈለጓንና ማጠናቀቅ ብቻ ግቧ እንደነበርም ታነሳለች።
የ80 ኪሎሜትር የሩጫ ውድድሩን ጀምራው በመኪና አጋምሳ የጨረሰችው ጆሲያ ዛክሬውስኪ ያደረገችው ፍጹም ስህተትና ሙያዊ ስነምግባርን ያልጠበቀ መሆኑን አምናበት ጭምር የነሃስ ሜዳልያዋን መልሳለች።
ባታምንበትም ሜዳልያውን መነጠቋ አይቀርም የሚሉ የስፖርት ቤተሰቦች ግን አትሌቷ አዘጋጆቿ ሳይጠሯት በፈቃዷ ሄዳ ሜዳልያውን መመለስ ነበረባት በሚል እየተቃወሟት መሆኑን ኦዲቲ ሴንትራል አስነብቧል።
በ48 ስአታት ውስጥ ረጅም ርቀት በመሮጥ የአለም ክብረወሰንን ከሳምንታት በፊት የያዘችው ጆሲያ ዛክሬውስኪ ስሟ በቅሌት መዝገብ ውስጥ መስፈር እንዳልነበረበትም የሚያነሱ በርካታ ናቸው።
ምንጭ አል ዐይን
#ድርድር
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሸኔ ወይም እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ገልጸዋል።
ይህንን ያሳወቁት ፥ በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ግጭት በሰላም ስምምት እንዲቋጭ ቁልፍ ሚና ለነበራቸው አካላት የምስጋና እና የዕውቅና ሥነ ስርዓት በተካሄደበት ወቅት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ የወለጋ ሕዝብ እፎይ እንዲል ሁሉም ወገን የበኩሉን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል በቀጣዩ ሣምንት በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት የተመራ ልዑክ ወደ መቐለ እንደሚያቀና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሳውቀዋል።
ልዑኩ የሁሉንም ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች ያካተተ እንደሚሆን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
ፎቶ፦ ኤፍቢሲ
በጦርነት ይብቃ
ሰላም ይፅና መርሃግብር ላይ ጌታቸው ረዳ የተናገረው
"የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲፋጠን የጠሚ አብይ አህመድ ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው። አሁንም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣን እርምጃዎች የተጀመረውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ መስራት አለበት እላለሁ።
የትግራይ ህዝብ ጦርነት ሰልችቶታል። ከማንም ጋር ጦርነት መግባት አንፈልግም። ከአማራም ከአፋርም የሚያቀራርብ እንጂ የሚያቃቅር ነገር የለንም።
ትናንት በአፋር በኩል የሰላም ባስ አገር አቋራጭ አልፏል። ሐጂ አወል ይህንን ለማጠናከር መስራት ይገበዋል።
በተመሳሳይ ከአማራ ክልል ጋር በተያያዘም ዶክተር ከፋለ ኃላፊነት ወስደህ መስራት አለብህ ለማለት እፈልጋለሁ።
ዶክተር አብይ በጀመረው እጁ በሌሎች አካባቢዎች የሚታዩ ግጭቶችን በሆደ ሰፊነት ለመፍታት መስራት እንደለበት ለመጠቆም እፈልጋለሁ!
በመጨረሻ ከይዋጣልን መንፈስ ወጥተን የፍቅር፣ የስራ ቋንቋ መጀመር አለብን። ሰላም እንዲፀና የትግራይ ክልል ጊዚያዊ መንግስት የበኩሉን ይሰራል"
አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ መስተዳድር ፕሬዚደንት
የአፍሪካ አገራት በሰሜን ኢትዮጵያ አጋጥሞ የነበረው ችግር ከተፈታበት መንገድ ትምህርት ሊወስዱ ይገባል
- ኡሁሩ ኬኒያታ የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት
በግጭት ውስጥ ያሉ የአፍሪካ አገራት በሰሜን ኢትዮጵያ አጋጥሞ የነበረው ችግር ከተፈታበት መንገድ ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ ተናገሩ።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በመንግስትና ህወሃት የሰላም ስምምነት የመጣውን ውጤት ተከትሎ “ጦርነት ይብቃ ሰላምን እናጽና” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ወዳጅነት ፓርክ የእውቅና እና ምስጋና መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የተከናወነው ስራ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ኩራት ስለመሆኑ ጠቅሰዋል።
የዛሬው እለት የኢትዮጵያውያን ቀን ነው ያሉት ኡሁሩ ኬንያታ "ለሰላም ጥረት ያደረጋችሁ ሁሉ እና መላ ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል።
በኢትዮጵያ የሚፈለገው ሰላም እውን ሆኗል፤ በመሆኑም በግጭት ውስጥ ያሉ የአፍሪካ አገራት በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ችግር ከተፈታበት መንገድ ትምህርት በመውሰድ ሰላም ማምጣት አላባቸው ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
አፍሪካ ለራሷ ችግር በራስ መፍትሄ ማምጣት እንደምትችል በተግባር አሳይታለች ያሉት የቀድሞው ፕሬዝዳንት በኢትዮጵያ የመጣው ሰላም ለመላ አፍሪካዊያን ጥሩ ተምሳሌት ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ነው ያሉት።
መጪው ጊዜ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና አጠቃላይ ለአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግና እውን እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፣ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፣ የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር፣ የአፍሪካ ሀብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳፋኪ ማሃማት እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ከሱዳን ዜጎቻቸውን ማስወጣት የቻሉ ሀገራት እነማናቸው?
ጦርነቱ ሰፊ ቦታን በማካለሉ እና በሱዳን ዋና ከተማ የሚገኘው የካርቱም አለምአቀፍ አየርመንገድ የጦር ቀጣና በመሆኑ በሀገሪቱ ያሉ ዲፕሎማቶችን ማስውጣት አስቸጋሪ ሆኗል።
https://am.al-ain.com/article/countries-evacuate-nationals-sudan
ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፦ #ሼር #Join
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
