en
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Open in Telegram

Addis abeba Ethiopia

Show more
5 400
Subscribers
-22624 hours
-2 2007 days
-2 65830 days
Posts Archive
ኢትዮጵያ M-20 የተሰኙ ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ሶማሊያ ድንበር ማስጠጋቷን የሞቃድሾ የዜና ምንጮች እየዘገቡ ነው።ይህ የሆነው የግብፅ ወተደሮች ሶማሊያ መግባታቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል። #Ethio
ኢትዮጵያ M-20 የተሰኙ ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ሶማሊያ ድንበር ማስጠጋቷን የሞቃድሾ የዜና ምንጮች እየዘገቡ ነው።ይህ የሆነው የግብፅ ወተደሮች ሶማሊያ መግባታቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል። #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

ስለ አሁናዊ ቀጠናዊ ሁኔታ ምን ማወቅ ይጠበቅብኛል? (የ 4 ደቂቃ ንባብ) የኢትዮጵያ መንግስት ከወራት በፊት ከሶማሌላንድ ራስ ገዝ አስተዳደር ጋር ያደረገውን የባህር በር መግባቢያ ስምምነት ተከትሎ ሶማሊያና ኢትዮጵያ መካከል አለመግባባት መፈጠሩ ይታወሳል። ° ኢትዮጵያ እና ለሶማሊያ ባለፈት ዓመታት በ1966 ዓ.ም ሶማሊያ የአረብ ሊግን መቀላቀሏን ተከትሎ በወቅቱ የሶማሊያ መሪ የነበረው ሜጀር ጄኔራል ሲያድ ባሬ ኢትዮጵያን ወረረ። በዚህ የተነሳው ጦርነት የመጨረሻው ውጊያ በተካሄደበት #ካራማራ የኢትዮጵያ ጦር የዚያድ ባሬን ጦር በመርታት ሉዓላዊ ግዛቱን ማስከበር ቻለ። ከዚህ በኋላ ታላቂቷ ሶማሊያ ተብላ ትጠራ የነበረችው ሀገር መሪዋ በመኮብለሉ እንዲሁም ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረት ስለተሳናት ወደለየለት እርስ በእርስ ጦርነትም ገባች። በዚህ ውስጥ በ1983 ዓ.ም ሶማሌላንድ ነጻ ሀገር መሆኗን አወጀች እሱን ተከትሎ ፑንትላንድም ራስገዝ አስተዳደር መሰረተች። ይህን ተከትሎ እስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት (ICU) በሶማሊያ ያለው ጣልቃ ገብነት እየጨመረ መጣ። ይህ ያሳሰባት ኢትዮጵያ በአሜሪካ ድጋፍ በሀገሪቱ የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት አስቻለች። ሆኖም ይሄ ኃይል አቅም አልነበረውም። ከዚህ በኋላ በቀጠናው አልሸባብን ጨምሮ አክራሪ ቡድኖች ተፈጠሩ። ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ አልሸባብ በተለይ ደቡባዊ እና መካከለኛው ሶማሊያን ላይ የበላይነት አሳይቷል። በቀጠናው ሀገራትም የሽብር ጥቃቶችን በመፈጸም ብዙ ጥፋት አደረሰ። ይህን ተከትሎ በአፍሪካ ኅብረት የሚመራ የሰላም አስከባሪ ጦር (#AMISOM) ተቋቋመ። በዚህ ውስጥ ኢትዮጵያ ጉልህ አስተዋጽኦ ነበራት። በዚህ ኃይል በ2004 ዓ.ም ሶማሊያ ህገ-መንግስት እና የመጀመሪያውን ፕሬዚዳንት ለመሾም በቃች። የአሚሶም ሰላም አስከባሪ ሀይም በዚህ ስኬት ተልዕኮውን በ2014 ዓ.ም አጠናቀቀ። ° ከ AMISOM ወደ ATMIS የ #ATMIS ዋና ዓላማ የነበረው የወታደራዊ ቁጥጥር ኃይሉን ለሶማሊያ መንግስት ማስተላለፍና የሀገሪቱን ጦር ማደራጀት ነበር። ይህ ኃላፊነት በተያዘው የፈረንጆቹ ዓመት ይጠናቀቃል። በዚህም በሶማሊያ የነበሩት የሰላም አስከባሪዎች በዙር የመቀነስ እቅድ ተቀምጧል። የ ATMIS ተልዕኮ ቢያበቃም በቀጠናው ያለው የሰላም እጦት እንዲሁም የሶማሊያ ጦር ሙሉ ለሙሉ ጸጥታውን መቆጣጠር እስከሚችል ድረስ ቀነ ገደቡ እንዲራዘም ኢትዮጵያን ጨምሮ የቀጠናው ሀገራት ጥያቄ አቅርበዋል፤ የሰላም አስከባሪ ኃይላቸውንም ለመላክ ፈቃደኝነታቸውን ገልጸዋል። ° የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት ህጋዊ መብቷን ተጠቅማ አንስታለች። ለዚህም በቅርቡ ከሶማሌላንድ ራስ ገዝ አስተዳደር ጋር ያደረገውን የባህር በር መግባቢያ ስምምነት ማድረጓን አስታውቃለች። ይህን ተከትሎ ለራስ ገዟ አስተዳደር እውቅና ያልሰጠችው ሶማሊያ ይህንን ስምምነት ከቀን አንድ ጀምሮ በመንግሥት ደረጃ መቃወም ጀምራለች። ቱርኪዬ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መንግስት በኩል የነበረውን አለመግባባት ለመፍታት ያደረገችው ጥረት እስካሁን ፍሬ አላፈራም። ° የሶማሊያ መንግስት መግለጫዎች የ ATMIS የተልዕኮ ጊዜ መገባደዱን ተከትሎ አሁን ላይ #Aussom የተሰኘ የሰላም አስከባሪ ኃይል እየተቋቋመ ነው። የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ባሬ በቅርቡ ኢትዮጵያ የዚህ ኃይል ተሳታፊ እንደማትሆን መግለጫ ሰጥተዋል። ለ2 ዓመታት በተራዘመውና እንደ አዲስ ይቋቋማል በተባለው የ Aussom የሰላም አስከባሪ ኃይል 10 ሺ የሚቆጠሩ የግብፅ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ ማቅናታቸው አሁን ላይ ለተባባሰው ውጥረት ምክንያት ነው። ሰሞኑን ተካሄደ በተባለው ዝግ ስብሰባ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ወታደራዊ ልብስ ለብሰው ከሀገሪቱ የጦር አመራሮች ጋር ተሰብስበዋል። የሶማሊያ መንግስት ስብሰባው "በፀጥታ ማጠናከርና ሀገሪቱን ነፃ ማውጣት ላይ ያተኮረ ነው ሲል ገልጿል። የሶማሊያ የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ ሌሎች ዜጎች ግብፅ በዚህ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ መካተቷን የተቃወሙ ሲሆን በፕሬዚዳንቱ እስከመባረር እርምጃ ተወስዶባቸዋል። ° ኢትዮጵያ ምን አለች? የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ  (አምባሳደር)  ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ ‹‹የሶማሊያን ድንበርና ሉዓዊነት እናከብራለን፣ ምንም ጥያቄ የለውም፡፡ የምንፈልገው ነገር ግን አስተማማኝ የባህር በር ነው፤›› በማለት፣ ይህ ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን ሕጋዊና ይህ ትውልድ መልስ ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቱርክ አደራዳሪነት እንዲሁም በጉዳዩ ላይ በተደጋጋሚ ባወጣችው መግለጫ ከሶማሊያ ጋር ያለውን ውጥረት በውይይት ለመፍታት እንደምትሻ ስትገልጽ ቆይታለች። አምባሳደሩ የግብጽ በቀጠናው ያላት ተሳትፎ በተመለከተም "ግብፅ በሶማሊያ በኩል መጥታ ኢትዮጵያን አጣቢቂኝ ውስጥ መክተት ትችላለች ማለት የቀን ቅዠት ነው" ሲሉ ተናግረዋል። ° የግብፅ ያልተጨበጠ ፍላጎትና አቀጣጣይነት ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር በባህር በር ጉዳይ የመግባቢያ ስምምነት በተፈራረመች በሰዓታት ውስጥ " አይዞሽ እኔ አለሁልሽ፤ በማንኛውም መንገድ አብሬሽ ቆማለሁ " ያለቻት ግብጽ ነች። ይኽም ወታደራዊ ስምምነት እስከመፈራረም ዘልቋል። ይህ እንዳለ የሶማሊያ ሰላም ሳይሆን የሚከነክናት የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ በመሆኑ " ማንኛውም አይነት እርምጃ ውስዳለሁ " የሚል ዛቻሞ እያሰማች ትገኛለች። ይህን ብላም ለተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ደብዳቤ ልካለች። ° ከሰሞኑ . . . የሶማሌላንድ መንግስት ፕረዚዳንት ሙሴ ባሂ አብዲ የኢትዮጵያ አዲስ አምባሳደር ሆነው የሹመት ደብዳቤያቸውን ያቀረቡትን አምባሳደር ተሾመ ሹንዴን ተቀብለው ማነጋገራቸውን ጽ/ቤታቸው አስታውቋል። ከኢትዮጵያ በኩል ግን ስለሹመቱ ይፋዊ ማረጋገጫ አልተሰጠም። ኢትዮጵያ በሀርጌሳ የሚገኘውን ቆንጽላ ጽ/ቤት ወደ ኢንባሲ ልታሳድግ በሚል ሶማሊያ በተከታታይ ስትቃወም ቆይታለች። ጅቡቲ ደግሞ አማራጭ ያለችውን የታጁራ የወደብን ጨምሮ በጋራ ማስተዳደር የሚያስችሉ ሌሎች አማራጮችን ለኢትዮጵያ አቅርባለች። ይህ አማራጭ የጦር ኃይልን ለማስፈር ጭምር ይሁን ለሲቪል አገልግሎት ብቻ ግልጽ አልተነገረም። ኢትዮጵያም ለዚህ ይፋዊ ምላሸ አልሰጠችም። ©tikvahethmagazine

ግብፅን ያሳበደው  የኢትዮጵያ ከሞሮኮ ጋር የተደረገ ድንቅ ወታደራዊ  ስምምነት..🇪🇹👌 ግብፅን ለምን አስደነገጠ ? ኢትዮጵያ ለምን ሞሮኮ ሄደች? ሞሮኮስ ለምን ኢትዮጵያን መረጠች ? የሚለውን  የኢትዮጵያን ብዙዎችን ያስገረመ የጂኦ-ፖለቲካዊ  ድል አጠር ባለ መልኩ እንመልከት ። ግብፅ ከስልጣን አልባው የበናዲሩ ሞቃዲሾ መሪ ሀሰን ሼይክ መሀመድ ጋር ያደረገችው የወታራዊ ስምምነት  ብዙ የተወራለት ነገር ግን ሁለቱንም መንግስታት ባላሰቡት መንገድ ቅርቃር ውስጥ የከተተ ሆኖ መጥቷል። ግብፅና ሞቃዲሾ ከተፈራረሙት የጦር ስምምነት እንደሚታወቀው በቀጥታ ኢትዮጵያን ለናጥቃትና ወደ ኤደንና ቀይ ባህር እንዳትወጣ ያለመ  ነው። ታዲያ ከስምምነታቸው አንዱ የሆነው ኢትዮጵያን በባህር የምታደርጋቸውን  ከንግድ  እስከ የባህር ሀይሏ የሚኖሩትን  እንቅስቃሴዎች... ግብፅ የአለማችን ወሳች የመርከቦች መተላለፊያ የሆነውን  የሲዊዝ ቦይን ኢትዮጵያ ላይ በመዝጋት ፣ ሞቃዲሾ የኢትዮጵያ መርከቦች ወደ ጅቡቲና በርበራ  እንዳያልፉ በማገት ኢትዮጵያ ከምግብ እስከ ጦር መሳሪያ ወደ ሀገሯ እንዳታስገባ በመከርቸም ማስገደድ ነው።  ( በመሀል ኤርትራም ያለች ሲሆን  ለግዜው እንዝለላት) ታዲያ ይህችን የ129ሚሊየን ህዝብ እናት የሆነች ታላቅ ሀገር ወደ ባህር እንዳትወጣ የተሸረበው ሴራ ሳያንስ እህልና ነዳጅ እንኳን እንዳታስገባ የተሸረበውን ቀመር የተረዳችው ኢትዮጵያ   በቀጥታ ያመራችው ቀድማ ወደ አዘጋጀቻት የሰሜን አፍሪካ ወደጅ ሀገር ሞሮኮ (አል-መግሪቢ) ጋር ነበር። ሞሮኮ በአለማችን ላይ ስትራተጂካዊ የጂኦፖለቲክስ አቀማመጥ ላይ ከሚገኙ ሀገራት አንዷ ነች ። ሞሮኮ በአጭሩ ለማስረዳት ሌሎች አህጉርና ሀገራትን ትተን  ወደ ግብፅ የሚሄዱ አብዛኛው መርከቦች መተላለፊያ የሆነው Strait of Gibraltar የባህር ወሽመጥ ባለቤት  ነች ። በዚህም የተነሳ  ግብፅ ልክ ኢትዮጵያን በአባይ ምክንያት ታሪካዊ ጠላት እንዳደረገቻት ሁሉ ሞሮኮንም  በተመሳሳይ መንገድ በጠላትነት ይዛት ኖራለች። ግብፅ በዚህም የተነሳ ልክ ኤርትራን  ከኢትዮጵያ እንድትገነጠል እንደሰራች ሁሉ  የሞሮኮን ተገንጣይ ራሳቸውን ሳህራዊ ሪፐብሊክ ብለው ሚጠሩትን ቡድኖች በመደገፍ ላይ ትገኛለች። በመሆኑም ኢትዮጵያ በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አማካኝነት  ከሌላኛዋ የግብፅ ስትራቴጂካዊ  ጠላት  ሜዲትራኒያንና  አትላንቲክ ውቂያኖስን ከምታገናው ወሳኝ ሀገር  ሞሮኮ  ሊፐብሊክ ጋር እጅግ ወሳኝ የወታደራዊ ስምምነት ከቀናት በፊት ፈርማለች ። በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ከግብፅ ሲዊዝ ካናል ላይ የሚደርስባት የመርከብ መታገት ካለ  የግብፅ መርከብ Strait of Gibraltar እንዳያልፍ ይዘጋበታል ማለት ነው።  በተመሳሳይ ኢትዮጵያም በኤደን ባህረሰላጤ ላይ አልፎ የሚወጣና የሚገባ የግብፅን መርከቦች ማነቅ ትችላለች። ይህን ለማድረግ ኢትዮጵያ በቅርብ ኤደን ላይ ከሚሰፍረው ባህር ሀይሏ ባሻገር የመድፍ እርቀት ላይ የሚገኘውን ምድሯንም መጠቀም ትችላለች። የሞሮኮና ኢትዮጵያ ወታደራዊ  ስምምነት  በዚህ ብቻ  አያበቃም ምናልባትም  ሩቅ ባልሆነ ግዜ ሁለቱም ሀገራት ኢትዮጵያ  በሜዲትራኒያን አቅራቢያ በሞሮኮ የናቫል ቤዝ ሊኖራት በተመሳሳይ ሞሮኮም በቀይ ባህር ዙሪያ የወታደር ሰፈር የሚኖራት ይሆናል። በመጨረሻም ይህ የኢትዮጵያ አስደናቂ  የወታደራዊ ዲፕሎማቲክ አካሄድ ሁለት የግብፅ ታሪካዊ ባላንጣ የሞሮኮና ኢትዮጵያ ልዩ አስተማማኝ ጥምረትን የፈጠረ ሲሆን  ከፈረሰ መንግስት ጋር  ኢትዮጵያ ላይ ያሴረችውን ግብፅን ምትይዝ ምትጨብጠውን አሳጥቷታል።  ይበልጥ ለመገንዘብ ይረዳችሁ ዘንድ Ahmed Habib Alzarkawi #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

የግብፅ ነገር #2 ? ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር በባህር በር ጉዳይ የመግባቢያ ስምምነት በተፈራረመች ወቅት ሰዓታት ሳይቆጠር ተቃውሞ ያሰማችው ግብፅ ነበረች። ከሶማሊያ ጋር ተደዋውላም  " አይዞሽ እኔ አለሁልሽ፤ በማንኛውም መንገድ አብሬሽ ቆማለሁ " ብላት ነበር። ባለስልጣናቶቿም ኢትዮጵያ ለሶማሊያን ስንትና ስንት የደም ዋጋ እንዳልከፈለች ዛሬ ደፍረው " ኢትዮጵያን እንዳለመረጋጋት ምንጭ " አድርገው ለመሳልም ሞክረዋል። የኢትዮጵያን ስም እያነሱ ሲለፈልፉ ከርመዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ከኢትዮጵያ ጋር መቃቃር ውስጥ ገብተው ወደ ግብፅ ሲመላለሱ ነው የከረሙት። በቅርብ ደግሞ " ከግብፅ ጋር ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረምን " ብለው ብቅ ብለዋል። ይህ ተሰምቶ ብዙ ሳይቆይ የተለያዩ የጦር መሳሪያ ቁሳቁሶችን የያዙ የግብፅ ፕሌኖች ሞቃዲሾ ሲያርፉ እና ቁሳቁስ ሲያራግፉ ነው የከረሙት። ሶማሊያ ደም አፍስሶ ዋጋ የከፈለላትን የኢትዮጵያ መከላከያ በATMIS እንዲቀጥል አልፈልግም ማለቷ ፤ ግብፅ ደግሞ በሶማሊያ ወታደሮቼን ማሰማራት ፈልጋለሁ ማለቷ አስገራሚ ነገር ሆኗል። " እኛ የግብፅ ወታደር እንዲመጣ አንፈልግም፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ዋጋ ከፍለውልናል ፤ እንዳይወጡ " ያሉ የሶማሊያ የምክር ቤት ሰዎች እና ነዋሪዎች አደባባይ ወጥተው ድምጻቸውን አሰምተዋል። ፕሬዝዳንቱ " ኢትዮጵያን በአቋማችሁ ደገፋችኋል " ያላቿውን ሰዎችን ከስራ ማባረር እንደተያያዙ ተሰምቷል። ይኸው ቀጠናዊ ጉዳይ እንዳለ ደግሞ ግብፅ ሆዬ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብን ጉዳይ በማንሳት " ማንኛውም አይነት እርምጃ ውስዳለሁ " ብላ ዛቻ ማሰማት ጀምራለች ፤ ምንም እንኳን የግብፅ ዛቻ አዲስ ባይሆንም። እዛው ባለችበት በርቀት ሆና መዛት ፤ መጮህ ፣ ማውራት መብቷ ነው ኢትዮጵያን መንካት ግን ፈጽሞ አትችልም። #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

የግብፅ ነገር ? ሀገራችን ኢትዮጵያ " እኔ ማንንም ሳልጎዳ የራሴን ሃብት እጠቀማለሁ " ብላ በራሷ የዓባይ ወንዝ ላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት መሰረት ከጣለችበት ጊዜ አንስቶ ስትጮህ ፣ ስትዝት፣ ለማስፈራራት ስትሞክር የነበረችው ግብፅ ዛሬም ግድቡ ወደ መጠናቀቁ ደርሶም ዛቻና ቀረርቶዋን አላቆመችም። ዛሬ ወደ ተመድ ፀጥታው ምክር ቤት አንድ ደብዳቤ ልካለች። ሀገሪቱ በቅርቡ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ግድቡን ከጎበኙና ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ መግባታቸውን ካበሰሩ በኃላ ስለ ግድቡ ውሃ መያዝ እና ከሞላ ጎደል የሲቪል እና ኤሌክትሮ መካኒካል ስራ ወደ መጠናቀቁ መድረሱን በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ እጅግ አናዷታል፤ አንጨርጭሯታል። ለጸጥታው ም/ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ላይም " በግብፅ መንግሥት ዘንድ ተቀባይነት የለውም " ብላለች። ሀገሪቱ ግድቡን ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያን ጎረቤቶቿን ተንኳሽ አድርጋ ለማቅረብም ሞክራለች። ኢትዮጵያ ስንት አመት ሙሉ ለሁሉም ጠቃሚ በሆነ መንገድ መፍትሄ ለማምጣት እንነጋገር እንስማማ ፤ መፍትሄ እንዲመጣ ቁርጠኛ ነኝ ስትል እንዳልከረመች ግብፅ እንደሁል ጊዜ ክሷ " ኢትዮጵያ ሌሎችን አግልላ የአንድ ወገን ፖሊሲ ታራምዳለች፣ መፍትሄ እንዲመጣም አትፈልግም " ብላለች። ግብፅ ለጸጥታው ምክር ቤት በጻፈችው በዚህ ደብዳቤ ፤ " ኢትዮጵያ እየተከተለች ነው ያለችው ህገወጥ ፖሊሲ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ማለትም በግብፅ እና በሱዳን ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል " የሚል የተለመደውን ክሷን አቅርባለች። " ጥቅሜን ለማስጠበቅ ሁሉንም አይነት ህጋዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ " ስትልም ዛቻዋን ገልጻለች። " ሁኔታዎችን በቅርብ እየተከታተልኩ ነው " ያለችው ሀገሪቱ " ህልውናዬን እና የህዝቤን ጥቅም ለማረጋገጥ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር የተረጋገጡ ሁሉንም አይነት እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ ነው " ያለችው። ግብፅ እንዲህ አይነት ዛቻ ስታሰማ ይህ የመጀመሪያ አይደለም። ገና ግድቡ መገንባት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እንዲሁ ስትል ነው የኖረችው። ምንም እንኳን በቀጥታ ሞክራው ባታውቅም ኢትዮጵያን ይጠላሉ፣ ወይም ያዳክሙልኛል የምትላቸውን ኃይሎች በግልፅና በህቡ ስትደግፍ ፤ የግድቡን ስራም ለማደናቀፍ ስትሰራ ነው የኖረችው። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቅፍ ጫና ለማሳደር ሁሌም እንደተሯሯጠች ነው ፤ ግድቡ ግን ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። አሁን ላይም ወደመጠናቀቁ ነው። ግብፅ ዛቻዋን አላቆመችም፤ አርፋም አልተቀመጠችም። በምንም አይነት መንገድ ለኢትዮጵያ የምትተኛም አይመስልም። " ኢትዮጵያን ይጎዳል " የምትለውን ክፍተት ሁሉ ከመጠቀም ወደኃላ የምትመለስም አይደለችም። #Ethiopia #ኢትዮጵያ #GERD🇪🇹

የሞቃዲሾውን ፕሬዚዳንት ወገብ ሰባሪ አዲስ ዜና ሰምቷል‼️ ከአገሪቷ የፓርላማ አባላት እስካሁን 40% ከኢትዮጵያ ጎን ቆሟል። ከ6 የአገሪቱ ግዛቶች ወደ 5 የሚሆኑት ኢትዮጵያን ደግፈዋል። የሞቃዲሾዎ
+2
የሞቃዲሾውን ፕሬዚዳንት ወገብ ሰባሪ አዲስ ዜና ሰምቷል‼️ ከአገሪቷ የፓርላማ አባላት እስካሁን 40% ከኢትዮጵያ ጎን ቆሟል። ከ6 የአገሪቱ ግዛቶች ወደ 5 የሚሆኑት ኢትዮጵያን ደግፈዋል። የሞቃዲሾዎ ሰውዬ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብቷል። የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ ክልል የፓርላማ አባላት ሀሰን ሼክ መሀመድን የጨው ሃውልት ያደረገ ባለአምስት ነጥብ አቋም መግለጫ አውጥተዋል። ''በናይል ወንዝ ጉዳይ ከጎረቤታችን ኢትዮጵያ ጋር መካረር ውስጥ የገባችውን ግብጽን ወደሶማሊያ መጋበዝ ለሦስተኛ ወገን ጥቅምና ፍላጎት ሃገርን የማስረከብ አደገኛ የሃገር ክህደት ሲሉ በማስጠንቀቀ በአንድ ግለሰብ የተሳሳተ ስሌት ሃገራችን ሶማሊያ የግጭት አውድማ እንድትሆን በፍጹም አንፈቅድም'' ሲሉ አቋማቸውን አሳውቀዋል። ============================== ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

ሶማሊላንድ ግብጽ ወታደሮቿን በሶማሊያ ማሰማራቷን አጥብቃ እንደምትቃወም ገለጸች‼️ ራስ ገዟ ሀገር ከሰሞኑ በሶማሊያ የግብጽ የጦር አውሮፕላኖች ማረፋቸውን ተከትሎ ካይሮ በአካባቢው እያደረግች የምትገኝ
ሶማሊላንድ ግብጽ ወታደሮቿን በሶማሊያ ማሰማራቷን አጥብቃ እንደምትቃወም ገለጸች‼️ ራስ ገዟ ሀገር ከሰሞኑ በሶማሊያ የግብጽ የጦር አውሮፕላኖች ማረፋቸውን ተከትሎ ካይሮ በአካባቢው እያደረግች የምትገኝው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለሶማሊያ እንዲሁም ለመላው የአፍሪካ ቀንድ ጸጥታ እና ደህንነት ስጋት ነው ብላለች፡፡ የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባወጣው መግለጫ የውጭ ሀይሎች በጎረቤት ሶማሊያ መስፈር ሽብርተኝነትን ለመዋጋት እና ሰላምን ለማስፈን ሲደረግ የነበረውን ጥረት የሚጎዳ ነው ሲል ግልጿል፡፡ አለምአቀፉ ማህበረሰብ የግብጽን አደገኛ እንቅስቃሴ እንዲያወግዝ የጠየቀው መግለጫው “የእኛንም ሆነ የጎረቤቶቻችንን ሰላም አደጋ ላይ የሚጥል የማንኛውንም የውጭ ሀይል ጣልቃገብነት አንታገሰም” ብሏል፡፡ #Ethiopia #Ethiopiaዬ #ኢትዮጵያ 🇪🇹

ሶማሌላንድ ዜጎች ለኢትዮጵያ ባንዲራ ያለቸው ፍቅር ተመልከቱ 👉🇪🇹 👇ዝርዝር መረጃዎችን #subscribe በማድረግ ያግኙ🙏 https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

የግብፅ ጦር በሀያልነቱ በአለም 15ኛ ሲሆን ከአረቡ አለም ደግሞ በቀዳሚነት ይቀመጣል። ይሁን እንጅ ይህ ጦር በታሪክ አንድት ጦርነት ሳይሆን አንድት ውጊያ እንኳ አሸንፎ አያውቅም! እስራኤል ይህንን ጦር ለማሸነፍ የፈጀባት ስድስት ቀናቶች ብቻ ነው። በስድስት ቀን ውስጥ እስራኤል የግብፅን ጦር አንበርክካ ሲና በረሀ ላይ ራቁቱን እየነዳች  ለአለም በማሳየት አዋርዳዋለች መሳቂያ መሳለቂያ አድርጋዋለች። ሲናይ በረሀንም ለቃ የወጣቺው በድርድር ብቻ ነው ያም የሆነው ግብፅ ለእስራኤል እውቅና እሰጣለሁ ወዳጅነትም እመሰርታለሁ የወረረቺውን ግዛቴን ለቃ ትውጣ በማለቷ ነበር። እናም ግብፅ ለእስራኤል የሀገርነት እውቅና በመስጠትና ከእስራኤል ጋር በመወዳጄት ከአረቡ አለም የመጀመሪያዋ ሀገር ለመሆን ችላለች። ከዚያ ክስተት በሗላ የግብፅ ጦር እስራኤል የሚባል ስም ሲሰማ ልቡ ይርዳል ! ግብፅ አሁን እስራኤል ጠላቷ አይደለችም ለእስራኤል እጅ ከሰጠች ቆይታለችና ! አሁን ጠላቴ የምትላት ሀገራችን ኢትዮጵያን ነው። ግብፅ ኢትዮጵያን በቀጥታ እንደማትዳፈራት ይታወቃል። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ጦር ከአፍሪካ እጅግ ጠንካራው ጦር ነውና! የግብፅ ጦርና የኢትዮጵያ ጦር ተቃራኒ ታሪክ ነው ያላቸው! የግብፅ ጦር በታሪኩ አንድ የውጭ ሀይል አሸንፎ የማያውቅ ሲሆን የኢትዮጵያ ጦር ደግሞ በታሪኩ በአንድ የውጭ ሀይል ተሸንፎ አያውቅም ! እናም ይህንን ጠንቅቃ የምታውቀውና ኢትዮጵያን ብትነካ የሚደርስባትን ውርደት በደንብ የምትገነዘበው ግብፅ በቀጥታ አትዳፈርም። ከዚያ ይልቅ የእጅ አዙር ጦርነትና የውስጥ ባንዳዎችን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማዳከም ስትሰራ ቆይታለች ። እስካሁን አልተሳካላትም! ኤርትራን ለመጠቀም ያደረገቺው ልፋት ፍሬ አላፈራም ! ሱዳንን ተጠቅማ ኢትዮጵያ ላይ ለማንዣበብ የሞከረው ክንፏም ሲሰበር አመት እንኳ አልፈጀበትም! አሁን የፈራረሰቺዋንና ለምልክት ያክል ብቻ ማእከላዊ መንግስት ያላትን ሶማሊያን ተጠቅማ ኢትዮጵያን አለሁ አለሁ ለማለት እየሞከረች ነው። ያው የጨነቀው ዱቄት ከነፋስ ተጠጋ እንዲሉ ግብፅ ሶማሊያ መሄዷ ቢጨንቃት እንጅ ሶማሊያ ኢትዮጵያን ባላንስ ማድረግ የምትችል ሀገር አይደለችም። ይልቁንስ ይህ የሶማሊያ ድርጊት ለራሷ ከባድ መዘዝ የሚያስከትልባት ነው የሚሆነው። ከማእከላዊ የሶማሊያ መንግስት በላይ ትልቅ አቅም ያላትን ሶማሌላንድን የኢትዮጵያ አንድ አካል እንዳታደርጋት ብትፈራ ይሻላት ነበር። የግብፅ ነገር የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም ነው። ወኔ አልባውና መሳሪያና በጀት እንጅ ልብና ጀግንነት የሌለው የግብፅ ጦር እንኳንስ ለሌላ ለራሱም አይሆንም !

#ሰበር_ዜና #አስደሳች_ዜና ምዕራብ ክልል የሚገኘው የሶማሊያ ህዝብ ግብጽ በሶማሊያ ያሰማራችውን ሃይል በመቃወም አደባባይ ወጥቷል። 👇ዝርዝር መረጃዎችን #subscribe በማድረግ ያግኙ🙏 https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

ልዩ ዜና ምዕራብ ክልል የሚገኘው የሶማሊያ ህዝብ ግብጽ በሶማሊያ ያሰማራችውን ሃይል በመቃወም አደባባይ ወጥቷል::
+5
ልዩ ዜና ምዕራብ ክልል የሚገኘው የሶማሊያ ህዝብ ግብጽ በሶማሊያ ያሰማራችውን ሃይል በመቃወም አደባባይ ወጥቷል::

የፐርፐዝ ብላክ ኢ ቲ ኤች ትሬዲንግ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስፈጻሚዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ሥራ አስፈጻሚዎቹ ስልጣንን አለአግባብ በመገልገል እና ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀሎች ተጠርጥረው ዛሬ በ
የፐርፐዝ ብላክ ኢ ቲ ኤች ትሬዲንግ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስፈጻሚዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ሥራ አስፈጻሚዎቹ ስልጣንን አለአግባብ በመገልገል እና ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀሎች ተጠርጥረው ዛሬ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ በማኅበሩ ተጭበርብረናል ያሉ ባለአክሲዮኖች ለፖሊስ ባቀረቡት አቤቱታ መነሻነት ምርመራ ተጀምሮ የአክሲዮን ማኅበሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ከላይ በተገለጹት ምክንያቶች በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ማኅበሩ መሀል ሜክሲኮ ላይ ገና በእጁ ባላስገባው መሬት እና ይዞታ ቤት ገንብቶ ባለ 3 መኝታ አፓርትመንት በ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚሸጥ መሆኑን በሚዲያ እና በራሪ ወረቀቶች በማስተዋወቅ ከሕዝቡ ገንዘብ ሲሰበስብ መቆየቱን በተለያየ መንገድ ከሕብረተሰቡ ሲቀርቡ የነበሩ ቅሬታዎች ያመላክታሉ ተብሏል። በዚህ መነሻም ሥራ አስፈጻሚዎቹ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፍትሕ ሚኒስቴር ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ፍስሃ እሸቱ ከወራት በፊት ሀገር ጥለው አሜሪካ መግባታቸው ይታወቃል።

ኢማራት ከፈረንሳይ ጋር ያላትን የ 20 ቢሊዮን ዶላር የጦር ስምምነት አቋረጠች። ፈረንሳይ ሰሞኑን የቴሌግራሙን መስራችና ባለቤት ትውልደ ሩሲያውን ፓቨል ዱሮቭን ማሰሯን ተከትሎ ኢማራት በድርጊቱ ክፉኛ
ኢማራት ከፈረንሳይ ጋር ያላትን የ 20 ቢሊዮን ዶላር የጦር ስምምነት አቋረጠች። ፈረንሳይ ሰሞኑን የቴሌግራሙን መስራችና ባለቤት ትውልደ ሩሲያውን ፓቨል ዱሮቭን ማሰሯን ተከትሎ ኢማራት በድርጊቱ ክፉኛ ተቅጥታለች። እናም ድርጊቱን በዝምታና በቀላሉ አላልፈውም ያለቺው ሀብታሟ ሀገር ዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ በፈረንሳይ ላይ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምራለች። በዚህም መሰረት ከአመታት በፊት ከፈረንሳይ የ 20 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸውን 80 የጦር ጄቶች ስምምነቷን ሰርዛለች። ይህም ፈረንሳይን አስንደንግጧል። በጉዳዩ ላይ የተደናገጠቺው ፈረንሳይ በፕሬዚዳንቷ ማኑኤል ማክሮን በኩል በሰጠቺው መግለጫ የዱሮቭ እስር ፖለቲካዊ አይደለም ብትልም ኢማራት ግን አልተቀበለቺውም። እናም ፈረንሳይ በአስቸኳይ ፓቨል ዱሮቭን የማትለቅ ከሆነ እርምጃዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ኢማራት ፍንጭ ሰጥታለች። ፓቨል ዱሮቬ ከሩሲያ ከተሰደደ በሗላ የፈረንሳይ ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ቢኖረውም አሁን ላይ ዋና ሀገሩ አድርጎ የመረጣት ኢማራትን ነው። ኢማራትም በአሁኑ ሰአት የቴሌግራም ዋና መቀመጫ ሆናለች። ፈረንሳይ ፓቨል ዱሮቭ የቴሌግራም ዋና መቀመጫን ፈረንሳይ እንዲያደርግ ብዙ ግፊት ስታደርግ ብትቆይም ሳይሳካላት ቀርቶ ዱሮቭ ኢማራትን መርጧል። እናም ለፓቨል እስራት አንዱ ምክንያት ይሄ ነው ይባላል። ታዲያ እኔን ካልመረጥክ በሚል ዜጋዋን ያሰረቺባት ኢማራት ፈረንሳይ ላይ እየወሰደች ባለው እርምጃ ኢኮኖሚዋን እየጎዳችው ትገኛለች ። ኢማራት ቢሊየሮችን ወደ ሀገሯ በመሳብ በአለም ከቀዳሚዎቹ ናት።