የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
5 576
Subscribers
-40724 hours
-2 4147 days
-2 42630 days
Posts Archive
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችንና ለጀግናው ለአገር መከላከያ ሠራዊታችን እንዲሁም ለመላው ቤተሰቦቻቸው ፣ እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል አደረሳችሁ፡፡
ዒድ ሙባረክ!
📹
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
ሶማሊያ ስትራቴጂካዊ ናቸው የተባሉ ወደቦችን አሜሪካ እንድትቆጣጠር ጥያቄ አቅርባለች።
ጥያቄው የቀረበውም አሜሪካ ከሶማሊያ ለተለዩ ክልሎች የሃገርነት ዕውቅና እንዳትሰጥ ነው ተብሏል።
ሴማፎር በመጋቢት 16 የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሃሰን ሼህ ሞሐመድ ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እነዚህን ስትራቴጂካዊ ወደቦች እንዲቆጣጠሩ በደብዳቤ መጠየቃቸውን ዘግቧል።
ለጥያቄ የቀረቡት ወደቦች በይፋ ባይገለፁም የበርበራ እና ቦሳሶ ወደቦች ሊሆኑ እንደሚችሉ ተገምቷል።
በደብዳቤውም አሜሪካ በቀጣናው ያላትን ቁጥጥር እንድታጠናክር እነደሚረዳት እና በወሳኙ የኤደን ባህረ ሰላጤ ላይም የሌሎች ሀገራትን ፉክክር እንድታስቀር እንደሚረዳት ስለመጠቀሱ ተመላክቷል።
የሶማሊላንዱ የበርበራ ወደብ የቀይ ባህር ንግድን ለማሳለጥ እና የሁቲ ጥቃትን ለመቀልበስ ወሳኝ ስለመሆኑ የተመላከተ ሲሆን በ2022 እራሷ ሶማሊላንድ አሜሪካ ዕውቅና እንድትሰጣት እና ወደቡን እንድትቆጣጠር መጠየቃቸው ይታወሳል።
ከወር በፊትም የሶማሊላንድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እስራኤል ዕውቅና ከሰጠቻቸው ከጋዛ ፍልስጤማውያንን እንደሚቀበሉ መናገራቸው ቢዘገብም ሚኒስትሩ ዘገባውን አስተባብለዋል።
ሶማሊያ በቀጣይ እርምጃዎች ዙሪያ ከአሜሪካ መንግስት ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኗን በደብዳቤው የተገለፀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የተጠየቁት የሃገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር እና በአሜሪካ የሚገኘው የሶማሊያ ኤምባሲ ሃሳብ ከመስጠት ተቆጥቧል።
ምንም እንኳን የበርበራ እና የቦሳሶ ወደቦች በሶማሊያ የፌዴራል መንግስት ቁጥጥር ስር ባይሆኑም የሶማሊያ ፌደራል መንግስት ግን አሁንም ወደቦቹን እንደራሱ ሉዓላዊ ግዛቶች ይቆጥራቸዋል።
Source: tikvahethmagazine
📹
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
በኢትዮጵያ የአየር ላይ ታክሲ ሊጀመር ነው‼
የአውሮፕላን መንደርደሪያ የማያስፈልጋቸው ሽቅብ ተነስተው ቁልቁል ማረፍ የሚችሉ የአየር ላይ ታክሲዎች ሀገራችን ሊከትሙ መሆኑ ታውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አርቸር አቬሽንስ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ላይ ትራንስፖርት መጓጓዣነት ለመጠቀም የሚያስችል የጋራ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ ዘመኑ የደረሰበትን የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠቱ በላይ ለአየር ንብረት መጠበቅ የራሱን የቻለ ትልቅ አስተዋፆ አለው ተብሏል።
ይህ አገልግሎት በመኪና ከ 60-90 ደቂቃ የሚፈጁ ጉዞን ወደ 10 ደቂቃ ዝቅ የሚያረግ ሲሆን ዕጅግ ፈጣን የትራንስፖርት ጉዞ ያደርገዋል
የአርቸር አቬሽን መስራች እና ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆነው አደም ጎልደንስቲን በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት በአቡዳቢ አቬሽን ተመሳሳይ አገልግሎት ለማስጀመር ስምምነት መፈጠራቸውን ገልፀው...
አሁን ደሞ በአፍሪካ ወደር ከሌለው ከግዙፉ የኢትዮጲያ አየር መንገድ መንገድ ጋር ለመስራት በመስማማታቸው ዕጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሳው በበኩላቸው በኤሌክትሪክ በሚሰሩ የአየር ላይ የታክሲ አገልግሎት ለመጀመር ከአፍሪካ ቀዳሚው ሀገር በመሆናችን ደስተኛ ነን በስምምነቱም በዘርፉ ግንባር ቀደም መሆናችን ያሳያል ያሉ ሲሆን አክለውም ለካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ያለንን ቁርጠኝነት ያሳየ ነው ብለዋል።
📹
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
አንካራ‼
የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሃሰን ሼህ ሞሐመድ ትናንት ከቱርክዬ ፕረዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ግብዣ ከቀረበላቸው በኋላ ወደ አንካራ አምርተው ነበር።
ፕሬዚዳንቱ ወደ አንካራ ካመሩ በኋላም ከፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ጋር በወታደራዊ ዘርፎች ውይይት ማድረጋቸው ተነግሯል።
ከውይይቱ በኋላ ዝርዝር መረጃዎች ባይወጡም ቱርኪዬ ሶማሊያን በመደገፍ የጦር ኃይል ለመላክ አዲስ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት እንደሚኖር ተገልጿል።
በተጨማሪም ቱርኪዬ ዘመናዊ የሆነውን የባይራክታር ድሮን ለመጠቀም የሚያስችል ስምምነት እንደሚደረግ እንዲሁም በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ወደ ሶማሊያ በቅርቡ እንደምትልክ ምንጮች ገልጸዋል።
ቱርክ በሶማሊያ ትልቁ የወታደራዊ ሰፈር ባለቤት ስትሆን በቱርክና ሞቃዲሾም የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር አባላትን እያሰለጠነች ትገኛለች። ለተጨማሪ መረጃ 👇
📹
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
የወንድ ዘር ፈሳሽ ልገሳን ሊጀመር ነው‼
በኢትዮጵያ ኩላሊት እና የወንድ ዘር ፈሳሽን ጨምሮ የተለያዩ የአካል ክፍሎች ልገሳን ለማስጀመር እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።
የወንድ ዘር ፍሳሽ እና የሰውነት አካል ልገሳን እንዲሁም መዳን በማይችል በስቃይ ውስጥ ያሉ ታማሚዎች በሐኪሞች እርዳታ እንዲሞቱ የሚፈቅደውን ሕግ ጨምሮ አዳዲስ የጤና አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ ሕጎችን የያዘው የጤና አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቀርቦ መጽደቁ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ደምና ህብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ጤናዬ ደምሴ ለአሐዱ ሬዲዬ ሲናገሩ እንደተሰማው ከሆነ ተቋሙ ከዚህ ቀደም የደም አገልግሎትን ብቻ ይሰጥ እንደነበር አስታውሰው፤ በ2015 ዓ.ም. ጀምሮ የዓይን ብሌን ልገሳን በማካተት እየሰራበት ይገኛል ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ህብረ-ህዋስን ጨምሮ የተለያዩ የሰውነት አካል ልገሳን ለማከናወን አዲስ ኃላፊነት መቀበሉንም ጨምረው ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት ሂደቱ እንደ ዓይን ብሌን ልገሳ ሁሉ በፈቃደኝነት የተመሰረተና ሰዎች በሕይወት እያሉ በሚገቡት ቃልና ፊርማ መሠረት የሚከናወን ሲሆን፤ "ኩላሊትን ጨምሮ የተለያዩ የአካል ክፍሎችን ያጠቃለለ ነው" ብለዋል።
📹https://youtu.be/evyZWwQJS80
https://youtu.be/evyZWwQJS80
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
🇪🇹 የአሜሪካ የስለላ ተቋም ሲአይኤ የሙሴ ጽላት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚገኝ በምናብ ምልከታ እንዳረጋገጠ የሚያሳይ ሰነድ ይፋ ሆነ
ሰነዱ የስለላ ተቋሙ እ.አ.አ 1988 ባካሄደው 'የርቀት ምልከታ' ሙከራ የአግዚአብሔር የቃል ኪዳን ታቦት የሆነው የሙሴ ጽላት በኢትዮጵያ እንደሚገኝ ማረጋገጡን ይገልፃል።
የሲአይኤ ሰነድ ነገሮችን ከሩቅ ሆነው የማየት ተሰጥኦ ያላቸው ሰዎች የታቦቱን መገኘ እንደለዩ አመላክቷል። የሩቅ ተመልካቾቹ ፅላቱ በእንጨት፣ ወርቅ እና ነሃስ ከተሠራ ሳጥን ወስጥ እንደሚገኝ እና የሚጠብቁት አካላት እንዳሉ ገልፀዋልም ተብሏል።
የሙሴ ጽላት በሰሜናዊ ኢትዮጵያ የአክሱም ከተማ እንደሚገኝ ይታመናል።
©sputnik_ethiopia
+2
የአውደ ውጊያ ድል መሠረቱ ጠንካራ ወታደራዊ ዝግጅት መፍጠር መሆኑ ተገለፀ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የአውደ ውጊያ ድል መሰረቱ ጠንካራ ወታደራዊ ዝግጅትና የማይናወጥ የሀገር ፍቅር መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አዛዡ በስልጠና ላይ ከሚገኙት የክፍሉና የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሀይል መካከለኛ አመራሮች ጋር የተወያዩ ሲሆን ዕዙ ሀገራዊ ግዳጁን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም ሰፋፊ የአቅም ግንባታ ስራዎችን እየሠራ መቆየቱን አሥታውሰው በየትኛውም አቅጣጫ በህዝብና በሀገር ላይ የሚቀሰሩ የጥፋት ጣቶችን ለመቁረጥ ዛሬም ሁለቱም ክፍሎች ከምንግዜውም ባላይ ዝግጁ ናቸው ብለዋል፡፡
ለነገ ድል ዛሬ መዘጋጀትን መቸም ቢሆን የማንዘነጋው የእለት ተእለት ስራችን ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የክፍሉ አመራር በእሳት ተፈትኖ በእሳት ውስጥ ያለፈ ጠንካራ በራስ መተማመንን የገነባ ሀይል መሆኑን በመግለፅ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ይህንን አቅም በማጎልበት አመራሩን ለላቀ ሀገራዊ ግዳጅ ማዘጋጀትና የነገ ተኪ የሠራዊት አመራሮችን ማፍራት ጭምር አላማ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጀግኖች ባለአደራ የአድዋ ድል የትውልድ ትውልዶች ነንና በህይወት ቆመን ተላላኪ ባንዳዎችም ሆኑ ላኪ ቀቢፀ ተስፈኞች ኢትዮጵያንም ሆነ ህዝቦቿን በመከፋፈል ማዋረድ አይችሉም፤ ይህ እንዳይሆን ደግሞ የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የህዝቦቿን ክብር ጠብቀን ለቀጣዩ ትውልድ የለማች ኢትዮጵያን ለማሰረከብ ሁሌም እንዘጋጃልን ብለዋል፡፡
ፅንፈኛውና ሸኔ ህዝብን ለያይቶ በማባላት ኢትዮጵያን ለማፍረስ የዘረጋውን የጥፋት መረብ በመበጣጠስ በኩል ክፍሉ ትልቅ ስራ መስራቱን የተናገሩት ሌተናል ጅኔራል ሹማ አብደታ ሰልጣኝ አመራሩ የተጣለበትን ሀገራዊ ሃላፊነት በጥልቀት ተገንዝቦ ስልጠናውን በብቃት በመወጣት ለነገ ድል መዘጋጀት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ ዘገባው የአብዱራህማን ሀሰን ነው።
አሜሪካ ለግብፅ የምትሰጠውን እርዳታ ልታቋርጥ ነው
#Ethiopia | ግብፅ የጋዛ ዜጎችን ለማስፈር የወጣውን ዕቅድ አልቀበልም በማለቷ አሜሪካ ለሀገሪቷ የምትሰጠውን እርዳታ ልታቋርጥ እንደምትችል ምንጮች ገለጹ።
የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር በጋዛ የመልሶ ግንባታ ለማከናወን ያቀረበውን እቅድ ግብፅ በመቃወሟ ለካይሮ የሚሰጠውን ወታደራዊ እርዳታ ለመቀነስ ማቀዱን ለግብፅ እንዳሳወቀ ምንጮች ተናግረዋል።
የፖሊሲ ለውጡ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ለማፈናቀልና በግብፅ እና በዮርዳኖስ ውስጥ ለፍልስጤማውያን አዲስ መንደር መገንባትን የሚያጠቃልለውን የመካከለኛው ምስራቅ የትራምፕ እቅድ ግብፅ አለመቀበሉን ተከትሎ የመጣ ነው።
በዋሽንግተን የሚገኙ የግብፅ ዲፕሎማት እንደተናገሩት፤ ለግብፅ የሚሰጠው ዕርዳታ ትክክለኛ መጠን እስካሁን ባይታወቅም ቅነሳው በሚቀጥለው ዓመት ተግባራዊ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
እንደ ዘገባው ከሆነ ትራምፕ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ በማውጣት ወደ ጎረቤት ሀገራት ለማዘዋወር ባቀዱት እቅድ ሁለቱ ሀገራት ካልተስማሙ ለግብፅ እና ለዮርዳኖስ የሚሰጠውን እርዳታ እንደሚቆም ፍንጭ ሰጥተዋል።
ግብፅ ህዝቧን ሳያፈናቅል ጋዛን መልሶ ለመገንባት የ53 ቢሊዮን ዶላር እቅድ አቅርባለች። የውሳኔ ሃሳቡ የአረብ ሊግ ባሳለፍነው ሳምንት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የፀደቀ ሲሆን፤ ከምዕራባውያን እና ከአውሮፓ ድጋፍ አግኝቷል።
ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ መንግስታት የትራምፕን የጋዛ እቅድ የጦር ወንጀል ነው በማለት የዘር ማጽዳት ሲሉ ተቃውመዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ ለግብፅ በዓመት ሁለት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ዕርዳታ ትሰጣለች።
አሜሪካ ለግብፅ መንግሥትና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ጭምር ኢኮኖሚያዊ ዕርዳታ መስጠት ከጀመረችም መከራረሟ የሚታወስ ነው። ዘገባው የሚድል ኢስት ሞኒተር ነው።
#gazette_plus
ባሉበት ሆነው ትኩስ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኝት ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
"""""""""""***""""""""""
ዩቲዩብ ገጽ:
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
ቴሌግራም ገጽ:
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ✅
📢🔴https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
📢🔴ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
አሜሪካ ኢራንን ብታጠቃ 'ከባድ ጥፊ' ይጠብቃታል ሲሉ አያቶላ አሊ ካሜኔይ ተናገሩ
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ካስጠነቀቁ በኋላ የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኔይ የአሜሪካ ዛቻን ተከትሎ ኢራንን ተጋፍጠው የትም አያደርሱም ብለዋል። አሜሪካ እና ሌሎች በኢራን ህዝብ ላይ መጥፎ ነገር ካደረጉ ማወቅ አለባቸው ከባድ ጥፊ ይደርስባቸዋል” ሲሉ አያቶላ አሊ ካሜኒ በቀጥታ የቴሌቪዥን ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል ።
በየመን ሁቲዎች የሚተኮሱት "እያንዳንዱ ጥይት" የኢራን ጥቃት ተደርጎ ይወሰዳል ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ማስፈራሪያ ውጥረቱን አባብሷል።የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በበኩላቸው አሜሪካ በየመን ላይ የምታደርሰውን አውዳሚ የአየር ጥቃት እና የእስራኤል መንግስት በጋዛ ፍልስጤማውያን ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት በመቃወም የፀጥታው ምክር ቤት እነዚህን እኩይ ተግባራት በመጋፈጥ የወሰደውን አዝጋሚ እርምጃ ነቅፈው አውግዘዋል።
ኢስማኢል ባጋሃይ በሰጡት መግለጫ በንፁሃን ሴቶች እና ህፃናት ላይ በሰላማዊ ሰዎች ላይ በደረሰው የጅምላ ግድያ እና የየመንን ጠቃሚ መሰረተ ልማቶች በዩናይትድ ስቴትስ የቦምብ ድብደባ ምክንያት በመውደሙ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል። የአሜሪካ የአየር ላይ ጥቃት የጦር ወንጀሎች እና የጥቃት ወንጀሎች በማለት የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት እና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት በነዚያ ግፍ ላይ ያደረጉት ዝምታ “አሳፋሪ እና ምክንያታዊ ያልሆነ” ነው ሲሉ ተቃውመዋል።
ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ✅
📢🔴https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
📢🔴ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
Breaking news : በብርጋዲየር ጄኔራል ምግበ ሀይለና ግብረ አበሮቹ አደራጅነትና አይዞህ ባይነት ዘመቻ አንድነት በሚል ስያሜ በተለያዩ የአማራ ክልል የዞን ወረዳዎች ትንኮሳ ለመፈፀም የሞከረው ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛው ቡድን ተደምስሷል።
ብርጋዲየር ጄኔራል ምግበ ሃይሌ እድሜ ልኩን በታሪኩ ግጭት እየጠመቀ የትግራይን ሕዝብ ወደ ጦርነት በማስገባት ያለ ምንም ወታደራዊ ዕውቀት ወጣቱን ወደ እሳት አሥገብቶ የማስፈጀት ታሪክ ያለው ፀረ ሠላምና ፀረ ልማት አራማጅ ነው።
ውጊያ ከብዶት የሸሸውን ወጣት ለምን ሸሸህ በሚል ሰበብ በጅምላ የመረሸን ልምድ ያለው ያለ ዕውቀት የትግራይን ወጣቶች ደም ሲመጥ የቆየ መሆኑ ሳያንሠው አሁን ላይም በሞኙ የፅንፈኛው መሪዎች ነን ባዮች አማካኝነት የሠላም ፈላጊውን የአማራን ወጣት ህይወት ለመቅጠፍ እንቅስቃሴ የጀመረ መሆኑ ታውቋል።
ባለፈው ጊዜ በነበረው የሰሜኑ ጦርነት በመቶ ሺህ የሚቆጠር የትግራይ ወጣትን እየረሸነ እያሥረሸነ የፈጀ የጥቁር ታሪክ ፀሃፊነቱ ሳያንስ አሁን ላይም መሠል ድርጊት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሰ ነው።
ምዕራብ ትግራይን አስመልሳለሁ በሚል እሳቤ ሁለት ጊዜ የፌዴራል መንግስት ሠራዊትን ለማጥቃት ሞክሮ በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶችን ያሥበላ ዉጊያ እምቢ ሲለው የራሱን ታጣቂዎች ረሽኖና ገድሎ ውጊያው ሳይሳካለት አከርካሪው ተመትቶ ሸሽቷል።
ምግቤ ሃይሌ ዘረፋና ሌብነት የተካነበት መደበኛ ሥራው ነው ። በአሁኑ ጊዜ የትግራይን ወርቅ እየዘረፈ በኤርትራ በኩል አድርጎ እየሸጠ ይገኛል። በኢህአዴግ ዘመን በዘረፋና ሌብነት ታዋቂ የነበረ ብቻ ሳይሆን በሰረቀውና በዘረፈው ገንዘብ አዲስ አበባ ላይ ፎቆችን የደረደረ አለፍ ሲልም ዱባይ ላይ ፎቆችን ለመሥራት በቅርብ ጊዜ የተዋዋለ ሥለመሆኑ በሶሻል ሚዲያ ሲነገር ቆይቷል።
በጦርነት ከቀቀለው ወጣት በተጨማሪ የረሸናቸው በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በመኖራቸው ትግራይ ሰላም እንድትሆን ከቶውንም አይፈቅድም። ምክንያቱም ደግሞ የትግራይ ሕዝብ ልጆቹን ይጠይቀኛል የሚል ስጋት አንደኛው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ እያደረገ ያለው የወርቅ ዘረፋ እንዳይጋለጥበት በማሠብ ነው።
በሌላ በኩል ምግበ ሀይለ የፕሪቶሪያን ስምምነት እንዲፈርስ እንዳይሳካ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ያለ ከመሆኑም በላይ የጊዜያዊ መሥተዳድሩን ማህተም ለመንጠቅ እና በሀይል አፍርሶ ሥልጣን ለመያዝ የሞከረ የፀረ ሠላምና ፀረ ልማት አራማጅ ነው።
የሠላም ጠንቅ የሆነው ምግበ ሃይሌ ለዚህ መሰሪ ተግባሩ ጅላጅሉን ፋኖ እንደ ተባባሪነት በመጠቀም ፅንፈኛው ፋኖ በራሱ ክልል ላይ ያልተገባ ውድመት እንዲፈፅም አዞታል። ነገር ግን ዘመቻ አንድነት በሚል ስያሜ ፅንፈኛውን አሥተባብሮ በጀመረው ትንኮሳ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷበታል።
በደቡብ ጎንደር፣ በምዕራብ ጎንደር፣ በሰሜን ጎጃም፣ በምስራቅ ጎጃም፣ በምዕራብ ጎጃም እንዲሁም በሰሜን ወሎ የምግበ ሀይለ ተላላኪ ፅንፈኞች በለኮሱት እሳት ተለብልበዋል።
በዚህ ሁለት ቀናት ብቻ 317 የተገደለ፣ 41 የተማረከ፣ 125 የቆሰለ፣ 27እጅ የሠጠ፣ 51 በምህረት የገባ፣ 15 መረጃ አቀባይ የተያዘ፣ በድምሩ 576 የሠው ኪሳራ ሲደርስበት 01መትረየስ፣ 119 ክላሽ፣ 46 ኋላቀር መሣሪያ፣ 08 ሽጉጥ፣ 22 ቦምብ፣ 2290 የተለያዩ ዓይነት ተተኳሾች፣ 28 ትጥቅ፣ የመገናኛ ራዲዮ፣ ተሽከርካሪ፣ ባጃጅ፣ ሞተር ሳይክል እና ሌሎች ቁሶችም በሠራዊታችን ቁጥጥር ስር ውለዋል።
ይህ በምግበ ሃይለ እና በግብረ አበሮቹ አይዞህ ባይነት የተጋለበው ፅንፈኛ ቡድን በዚህ ልክ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን በህይወት የተረፈው የትም የተበታተነ መሆኑ ተረጋግጧል።
https://aaaonline.info/cp7cat
ይህንን አፕሊኬሽን አውርዳችሁ አክቲቭ አድርጉ በየቀኑ በኮይን የሚከፍል ከቲክቶክ የተሻለ የሚከፍል በተላይ ለሴቶች በእጥፍ የሚከፍል አፕሊኬሽን ነው እርግጠኛ ሁኜ የሚነግራችሁ ቶሎ አውርዳችሁ ቤተሰብ ሁኑ።
https://aaaonline.info/cp7cat
