en
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Open in Telegram

Addis abeba Ethiopia

Show more
5 082
Subscribers
-11024 hours
-1 9137 days
-2 77030 days
Posts Archive
ሰኞ ጠዋት! ነሃሴ 22/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች 1፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የሕዳሴ ግድብን አራተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጀመሩን ዋዜማ ከኹነኛ ምንጮቿ ሰምታለች። የግድቡ የዘንድሮ ክረምት ውሃ ሙሌት በነሃሴና መስከረም እንደሚካሄድ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ. እንዲኹም ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ ቀደም ሲል መናገራቸው ይታወሳል። የውሃ ሙሌቱ በሰከንድ 1 ሺህ 200 ሜትር ኪዩብ መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች። መንግሥት ግድቡ በዘንድሮው ክረምት እንዲይዝ ያቀደው የውሃ መጠን፣ ከ10 ነጥብ 8 እስከ 11 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ነው። 2፤ ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ አቋርጠውት የቆዩትን የሕዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር ትናንት ካይሮ ውስጥ መጀመራቸውን የግብጽ መስኖ ሚንስቴር አረጋግጧል። የሦስቱ አገራት ተደራዳሪዎች ካይሮ ውስጥ ድርድሩን የጀመሩት፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና የግብጹ ፕሬዝዳንት አል ሲሲ ባለፈው ወር የሦስትዮሽ ድርድሩን በአራት ወራት ውስጥ እንደገና ለመቀጠል በተስማሙት መሠረት ነው። በባለፉት ድርድሮች ስምምነት ካልተደረሰባቸው ነጥቦች መካከል፣ በድርቅ ጊዜ ኢትዮጵያ ምን ያህል ውሃ ለታችኛው ተፋሰስ አገሮች መልቀቅ እንዳለባትና የወደፊት የውዝግብ መፍቻ ሥርዓት ይገኙበታል። 3፤ የኢትዮጵ ፕሬስ ድርጅት የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ "ኢትዮጵያ ኢሉሚናቲ" ለተሰኘ ማኅበር ከኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ እንደተሰጠው ተደርጎ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የተሠራጨው መረጃ ሃሰት እንደኾነ አስታውቋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ እንዲህ ዓይነት በማኅበር የመደራጀት ጥያቄ ቀርቦለት እንደማያውቅ፣ ቢቀርብለትም የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ እንደማይሰጥና በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የተሠራጨው ሰርትፍኬት የሃሰት መኾኑን አረጋግጦልኛል ሲል መረጃ ማጣሪያው ገልጧል። 4፤ የኬንያ ፖሊስ ከሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል ጋር በተያያዘ 71 ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ማቻኮስ ከተማ ውስጥ ቅዳሜ'ለት በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ዘ ስታር ጋዜጣ ዘግቧል። ኢትዮጵያዊያኑ የተያዙት ባንድ ቤት ውስጥ ተደብቀው መኾኑንና ፖሊስ ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚያቀርባቸው ዘገባው አመልክቷል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል ኢትዮጵያዊያን መካከል፣ 33ቱ ታዳጊዎች እንደኾኑ ተገልጧል። 5፤ ቻይና ሦስተኛውን የቻይና-አፍሪካ የሰላምና ጸጥታ ፎረም ዛሬ ማዘጋጀት ትጀምራለች። ቻይና የምታዘጋጀው የሰላምና ጸጥታ ምክክር እስከ ቅዳሜ ይቀጥላል። የስብሰባው ዓላማ፣ በቻይና እና አፍሪካ አገራት የመከላከያ ሚንስትሮች መካከል ስትራቴጂካዊ ኮምንኬሽን መፍጠር እንደኾነ የቻይና መከላከያ ሚንስቴር አስታውቋል። የቻይና ውጭ ጉዳይና መከላከያ ሚንስትሮች በመድረኩ ላይ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል።

ወቅታዊ መረጃ ተቋርጦ የነበረው የሶስትዮሽ የህዳሴ ግድብ ድርድር በዛሬው እለት በግብፅ ካይሮ ተጀምሯል። የሶስትዮሽ ድርድሩ ከዚህ በፊት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አቡዳቢ ሲደረግ ቆይቶ ረቂቅ ስምምነ
ወቅታዊ መረጃ ተቋርጦ የነበረው የሶስትዮሽ የህዳሴ ግድብ ድርድር በዛሬው እለት በግብፅ ካይሮ ተጀምሯል። የሶስትዮሽ ድርድሩ ከዚህ በፊት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አቡዳቢ ሲደረግ ቆይቶ ረቂቅ ስምምነት ማዘጋጀት ላይ ደርሶ የነበረ ቢሆንም ከዛ ወዲህ ድርድሩ ሳይካሄድ ቆይቷል። ይሁንና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በግብፅ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ከግብፁ ፕሬዝዳንት አብደልፈታህ አልሲሲ ጋር በደረሱት ስምምነት መሰረት የሶስትዮሽ ድርድሩ ዳግም ተጀምሯል። በዚህም ረቂቅ ስምምነቱ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ድርድር እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ድርድሩ የኢትዮጵያን ተጠቃሚነት እና የወደፊት የመልማት መብት ባስከበረ መልኩ ለማካሄድም አስፈላጊው ዝግጅት ተከናውኗል። _____ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተጨማሪ ሃገራዊ መረጃዎችን ለማግኘት ተከታዮቹን ገፆቻችንን ይጎብኙ

#BRICS BRICS ዛሬ አዳዲስ አባል ሀገራትን መቀበሉን አሳውቋል። እነዚህም ፦ 🇪🇹 #ኢትዮጵያ 🇦🇷 አርጀንቲና 🇪🇬 ግብፅ 🇮🇷 ኢራን 🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ 🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤ
#BRICS BRICS ዛሬ አዳዲስ አባል ሀገራትን መቀበሉን አሳውቋል። እነዚህም ፦ 🇪🇹 #ኢትዮጵያ 🇦🇷 አርጀንቲና 🇪🇬 ግብፅ 🇮🇷 ኢራን 🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ 🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ናቸው። አዳዲሶቹ አባል አገራት ከጥር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ቡድኑን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀላቀሉ  የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተናግረዋል፡፡ የሀገራችን ኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የBRICS ጉባኤ ኢትዮጵያን በአባልነት ተቀብሎ ማፅደቁን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት  ፤ " ይህ ለሀገራችን ታሪካዊ ሁነት ነው " ብለዋል። " ኢትዮጵያ ሁሉን አካታች ለሚሆን የበለፀገ የዓለም ስርዓት መስፈን ከሁሉም ጋር ለመስራት ሁሌም ዝግጁ ናት " ሲሉም ገልጸዋል። BRICS አዳዲስ አባል ሀገራትን መቀበሉን ተከትሎ አጠቃላይ አባላቱ አስራ አንድ (11) ይሆናሉ። እነሱም ፦ 🇧🇷 ብራዚል 🇷🇺 ሩስያ 🇮🇳 ህንድ 🇨🇳 ቻይና 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ 🇦🇷 አርጀንቲና 🇪🇬 ግብፅ 🇪🇹 ኢትዮጵያ 🇮🇷 ኢራን 🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ 🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ናቸው።

🇪🇹 የዛሬ መርኸግብር ~~~~~~~~~~~ 10ሺህ ሜትር ፍፃሜ ይጠበቃል በሁለተኛው ቀን በሀንጋሪ ቡዳፔስት በሚካሄደው የ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትካፈልበት የውድድር መርሃ-
+4
🇪🇹 የዛሬ መርኸግብር ~~~~~~~~~~~ 10ሺህ ሜትር ፍፃሜ ይጠበቃል በሁለተኛው  ቀን በሀንጋሪ  ቡዳፔስት በሚካሄደው የ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትካፈልበት የውድድር መርሃ-ግብር እሁድ ነሐሴ 14/2015 ዓ.ም  👇👇 🇪🇹1500 ሜትር ሴቶች  ግ/ፍፃሜ   ቀን 12፡05 🔸ሂሩት መሸሻ 🔸ብርቄ ኃየሎም 🔸ድርቤ ወልተጂ 🇪🇹10,000 ሜትር ወንድ ፍፃሜ   ምሽት 01፡25 🔸በሪሁ አረጋዊ 🔸ሰለሞን ባረጋ 🔸ይስማው ድሉ 🇪🇹ድል ለአትሌቶቻችን! #አትሌቲክስ #ቡዳፔስት #Ethiopian #WorldAthleticsChamps

"መላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ" ደራርቱ ቱሉ ትላንት ምሽት በተደረገው የ10000 ሜትር ሴቶች ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባታቸው እጅግ መደሰቷን የኢትዮጵያ አት
+5
"መላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ" ደራርቱ ቱሉ ትላንት ምሽት በተደረገው የ10000 ሜትር ሴቶች ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባታቸው እጅግ መደሰቷን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ተናግራለች። " በጣም ደስ ብሎኛል ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለሁ " ያለችው ጀግናዋ የቀድሞ አትሌት ደራርቱ ቱሉ " ፈጣሪ ረድቶን ከአንድ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘን ማጠናቀቅ ችለናል።"ብላለች። ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ አክላም " ፈጣሪ ይመስገን የመጀመሪያ ቀናችንን በወርቅም በብርም በነሀስም ጀምረናል ፍፃሜውም ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።"በማለት ለቪኦኤ ተናግራለች።

አረንጓዴው ጎርፍ በቡዳፔስት‼ በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ላይ በሴቶች 10ሺ ሜትር የፍፃሜ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቅ የአረንጓዴውን ጎርፍ ታሪክ ደግመዋል። በዚህ ርቀት በሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተመሳሳይ ታሪክ ሲሰሩ የዛሬው ሶስተኛ ነው። ከዚህ ቀደም እኤአ 2001 ኤድመንተን ቻምፒዮና ላይ ደራርቱ ቱሉ፣ ብርሃኔ አደሬና ጌጤ ዋሚ ከአንድ እስከ ሶስት ያጠናቀቁ አትሌቶች ሲሆኑ 2005 ላይ በሄልሲንኪ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ብርሃኔ አደሬና እጅጋየሁ ዲባባ ይሄንኑ ታሪክ ሰርተዋል። ባለፈው ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ለተሰንበት ያገኘችው የወርቅ ሜዳልያ በቻምፒዮናው ታሪክ ለኢትዮጵያ ስምንተኛው የወርቅ ሜዳልያ ነበር። ዛሬ ይሄው ክብረወሰን በጉዳፍ ፀጋይ ቀጥሏል። የወርቅ ሜዳሊያውን ከትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን ለማስጣል እልህ አስጨራሽ የአጨራረስ ትግል ያደረገችው ጉዳፍ በ31:27.18 ቀዳሚ ሆናለች። ያለፈው ቻምፒዮና አሸናፊዋ ለተሰንበት ግደይ በ31:28.16 ሁለተኛ፣ በ31:28.31 ሰዓት እጅጋየሁ ታዬ ሶስተኛ ሆነው ጨርሰዋል። ይህም በቡዳፔስቱ ቻምፒዮና የመጀመሪያ ቀን ኢትዮጵያ በአንድ ርቀት ብቻ ሶስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በማእከላዊቷ አውሮፓ ደምቃ እንድትታይ አድርጓታል። በዚህ ርቀት ጌጤ ዋሚ በ1999፤ ደራርቱ ቱሉ በ2001፤ ብርሃኔ አደሬ በ2003፤ ጥሩነሽ ዲባባ በ2005 በ2007 እና በ2013 እንዲሁም አልማዝ አያና በ2017 እኤአ ላይ 7ቱን የወርቅ ሜዳልያዎች አግኝተዋል። 7 የብር ሜዳልያዎች ብርሃኔ አደሬ በ2001ና በ2005 ፤ ወርቅነሽ ኪዳኔ በ2003፤ መሰለች መልካሙ በ2009፤ ገለቴ ቡርቃ በ2015፤ ጥሩነሽ ዲባባ በ2017 እንዲሁም ለተሰንበት ግደይ በ2019 እኤአ ላይ አግኝተዋል። 4 የነሐስ ሜዳልያዎችን ደግሞ ጌጤ ዋሚ በ2001፤ እጅጋየሁ ዲባባ በ2005፤ ውዴ አያሌው በ2009 እና በላይነሽ ኦልጅራ በ2013 እኤአ ላይ ተጎናፅፈዋል። ቦጋለ አበበ አዲስ ዘመን ነሐሴ 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🏴󐁧󐁢󐁥󐁮󐁧󐁿በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 10:00 | አስቶን ቪላ ከ ኤቨርተን 12:30 | ዌስትሃም ከ ቼልሲ 🇪🇸 በስፔን ላሊጋ 02:00 | ጅሮና ከ ጌታፌ 02:3
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🏴󐁧󐁢󐁥󐁮󐁧󐁿በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 10:00 | አስቶን ቪላ ከ ኤቨርተን 12:30 | ዌስትሃም ከ ቼልሲ 🇪🇸 በስፔን ላሊጋ 02:00 | ጅሮና ከ ጌታፌ 02:30 | ባርሴሎና ከ ካዲዝ 04:30 | ሪያል ቤቲስ ከ አትሌትኮ ማድሪድ 🇩🇪 በጀርመን ቡንደስሊጋ 10:30 | ዩኒየን በርሊን ከ ሜንዝ 18:30 | ኢንትራ ፍራንክፈርት ከ ዳርምስታድ 🇮🇹 በጣሊያን ሴሪ ኤ 01:30 | ሮማ ከ ሳለርኒታና 01:30 | ሳሱሎ ከ አትላንታ 03:45 | ሊስ ከ ላዚዮ 03:45 | ዩዴኔዜ ከ ጁቬንተስ 🇫🇷 በፈረንሳይ ሊግ 1 10:00 | ሊል ከ ናንትስ 10:00 | ሊ ሀቭሬ ከ ብረስት 10:00 | ሎረንት ከ ኒስ 10:00 | ሬምስ ከ ክሌሞንት 02:00 | ሞናኮ ከ ስታራስበርግ 03:45 | ሌንስ ከ ሬንስ 🏆በሴቶች አለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ 07:00 |  ስፔን ከ እንግሊዝ

+2
" የህዝባችን ፀሎት ሰምሯል " - ጉዳፍ ፀጋይ የወርቅ አሸናፊዋ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ከድሏ በኃላ ስለ ቡድን ስራ እንዲሁም ደግሞ አጠቃላይ የተሰማትን ስሜት ተጠይቃ ተከታዩን ብላለች። ጉዳፍ ፀጋይ ፦ " ተነጋግረን ነበር የገባነው። ዋናው ነገር #ወርቁን ማምጣት ስለሆነ ተነጋግረን እኔ 16 እና 17 ፤ ከዛ ሁለት ዙር ሲቀር በራሳችንን አቅም መሄድ ነበርና ወርቁ ከራሳችን እንዳይወጣ ነበር ጥረት ስናደርግ የነበረው። እግዚአብሔርም ሲጨመርበት ነውና ውጤት የሚያምረው የህዝባችን ፀሎት ሰምሯል። " ጉዳፍ ውድድሩን በበላይነት ያጠናቀቀችው እግሯ እየደማ ሲሆን ይህ እንዴት እንደተፈጠረ ተጠይቃ መልሳለች። " ሩጫ ላይ እንዲህ ያለው ነገር ያጋጥማል። በሩጫው መሃል ላይ ተነክቼ ነው እንደዛ የሆነው። 17 ወይም 18 ላልፍ አካባቢ ነው እግሬ የደማው " ብላለች። ምናልባት ሲፋን ሀሰን ባትወድቅ ኖሮ ውጤቱ ይቀየር ነበር ? ተብላ ተጠይቃም መልሳለች። ጉዳፍ ፀጋይ ፥ " እኔ እስከመጨረሻው ድረስ በጭራሽ እጅ አልሰጥም ብዬ ነው የገባሁት። ምክንያቱም እኔ ህዝቤ ይደግፈኛል ከሚገባው በላይ ፤ ወርቅ ማምጣት ምን ያህል እንደሆነ የህዝቡን ስሜት አይቻለሁ ፤ ከጎኔ ሆነው የሚደግፉኝ የኢትዮጵያ ህዝብ አሉና እነሱን ለማስደሰት ፣ ለራሴም ታሪክ ስለሆነ እስከመጨረሻው ተስፋ አልቆረጥኩም " ብላለች። ሲፋን ሀሰን ምን አለች ? በመጨረሻ ጥቂት ሰደንዶች ላይ ወድቃ ተሸናፊ የሆነችው ሲፋን ሀሰን " ተገፍቼ ነበር " ስትል ቃሏል ለቢቢሲ ሰጥታለች። " እሷ ወደ ውጭ እየሮጠች ነበር እናም ተዘግቶብኝ ነበር " ያለችው ሲፈን ፤ " ግን ምን ታደርጋለህ ስፖርት ነው፣ ሊከሰት ይችላል " ስትል ተናግራለች። የቪድዮ ባለቤት ፦ አረጋ ከፈለው ፎቶ ፦ @tikvahethsport

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም "ቀዩ ቦኔት" የከበሩ ሰማዕታት....ሀገርን አጽኚ አናብስት፣ ስለ ኢትዮጵያ በፈሰሰ..ቀይ ደማቸው ያቀለሙት፣ ተጽፎ የማይጨረስ...መቼም ማያል
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም                        "ቀዩ ቦኔት" የከበሩ ሰማዕታት....ሀገርን አጽኚ አናብስት፣ ስለ ኢትዮጵያ በፈሰሰ..ቀይ ደማቸው ያቀለሙት፣ ተጽፎ የማይጨረስ...መቼም ማያልቅ  ቢተርኩት፣ ቢነገር ቢነገር ሁሌ...ችለው ማይገልጹት ቃላት፣ የበራሪ ነብሩ ጀግና...የግርማ ሞገሱ ውበት፣ ታሪክ አለው የገዘፈ...የኮማንዶ ቀዩ ቦኔት። የደም አደራውን ውርስ..በራስ ለማኖር በክብር በእሳት መሃል የማለፍን..ስለ ኢትዮጵያ ፍቅር፣ ገደልን የሜዳ ያህል...ተረማማጅ ባለጥበብ ድቅድቅ ጨለማ ግርዶሽ..በውጣ ውረድ ሳያሳብብ፣ እንደ ድንገቴ መብረቅ...ከላይ የሚወርድ ከአየር፣ ሰማይ ጠቀሱ ተራራ...ቋጥኝ አለቱ ቢከመር የመሬት መልክ በሞላ...የትኛውም መልክዓ ምድር፣ ምንም ማንም የማይገታው..ወንዝ ሀይቁና ባህር፣ አዎ እሱ አይሳነውም....ባለ ቀይ ቦኔቱ ወታደር። ለዚያም ነው ቀይ ለባሹ...ትላንት የፃፈው ታሪክ፣ መግነጢሳዊ ገድሉ...ድንቅ ስራው ሲተረክ፣ "የውጊያ ማርሽ ቀያሪ"..."የምድር ድሮን"  የሚሉት፣ ልዩ የሆኑ ማዕረጎች...ለባለ ቀዩ የተሰጡት። ከዚህ ታለቅ መለዮ......ከቀዩ ቦኔት ስር፣ ህልቆ መሳፍርት የለሽ...ወደር የሌለው ሚስጢር፣ ሁሉን የመቻል ብቃት...አለ የሌለው ስፍር፣ ጀግንነት አሸናፊነት....የማያልቅ ቢጻፍ  ቢነገር። በአሥቻለው ሌንጫ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 11 ቀን 2015 ዓ.ም የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ...... የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ተግባራዊ የሚያደርጋቸው ለተልዕኮው ስኬት ዕውን መሆን የሚያግዙት መሠረታዊ ሥራዎች አሉት ለማሸነፍ መዘጋጀት ፣በሥልጠና ራስን ማብቃት ፣ ውጊያ ለማሥቀረት የሚያሥችሉ የዝግጁነት ሥራዎች ላይ ማተኮር የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሠጣቸው ተግባራቶች ናቸው። እንደእየ ግንባሩ ሁኔታ እየታየ ክፍተቶችን በመለየት ሠልጣኞች ምን ላይ አተኩረው እንደሚሠለጥኑ በጥናት ላይ ተመሥርቶ ተግባራዊ እንደሚሆን እና በተለይም ደግሞ ተጣጣፊ ሆኖ ግዳጁን መፈፀም የሚችል የኮማንዶ ሃይል አሠልጥኖ ማብቃት እየተቻለ መሆኑንም ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ተናግረዋል። የተጓደሉ የስታፍ ሙያተኞችን በአጫጭር ሥልጠና የማሟላት እና ለማንኛውም ግዳጅ አጋዥ እንዲሆኑ ማሥቻል ለአሥልጣኞች የቅድመ ሥልጠና መሥጠት እና ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲይዙ ማሥቻል ላይ ባለፉት ጊዜያቶች የተሠሩት ሥራዎች ሀገሩን የሚወድ ለመለዮው ክብር የሚሠጥ ኢትዮጵያን የሚመጥን ስፔሻል ኮማንዶዎችን መፍጠር እየተቻለ ነው። በመሆኑም ብላቴ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል የመሠረታዊ ውትድርና ሥልጠና ወሥደው መሥፈርቱን ያሟሉ ምልምል ወታደሮችን አሠልጥኖ ለወራት የመሠረታዊ ኮማንዶ ሥልጠና በመሥጠት ከሠሞኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር) የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች  በተገኙበት በብላቴ ማሠልጠኛ በደማቅ ሥነ ሥርዓት አሥመርቋል። ማሠልጠኛው የሃገራችንን ወቅታዊ የፀጥታ ችግር ሊፈታ በሚችልበት አግባብ ሥልጠናውን የተከታተሉ በአሥተሳሰብ እና በሥነ ልቦና የተገነቡ ችግርን ተቋቁመው ማለፍ የሚችሉ ለሀገራቸው እና ለህዝባቸው ቅድሚያ የሚሠጡ በመልካም ዲስፕሊን የተቃኙ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኮማንዶ እና አየር ወለድ አባላትን ለማሥመረቅ ችሏል። ማሠልጠኛ ማዕከሉን የማዘመን እና በአፍሪካ ቀዳሚ ለማድረግ መሠረተ ልማቶችን የመገንባት እንዲሁም የማሟላት ሥራ እየተተገበረ ነው ።በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመረቀው ከአሥር ሺህ በላይ ሠው መያዝ የሚችል አምፊ ቲያትርን ጨምሮ ደረጃውን የጠበቀ የአየር ማረፊያ ግንባታ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት እንዲሁም ሌሎች ለሥልጠና አጋዥ የሆኑ ግንባታዎች እየተከናወኑ ነው ። ከዚህ በዘለለ የመንግስትን እና የተቋሙን መርህ በመከተል በግብርናው መሥክም በርካታ ሥራ እየተሠራ ነው።  አትክልትና ፍራፍሬ ማምረት በምግብ ራስን ለመቻል የግብርና ሥራዎችን ማሥፋፋት ዘመናዊ የሥልጠና አሠጣጥ ሂደትን መከተል ተጠቃሽ ሥራዎች ናቸው። በድምሩ የኢትዮጵያን ዕድገት ለማፋጠን መከላከያ እንደ ተቋም የሚያከናውነውን ሠላም የማረጋገጥ ተግባር በማሳካቱ ረገድ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ሚና ከፍተኛ ነው። ዘመናዊ ሠራዊት በመገንባት ረገድም የተቋሙን ፍላጎት መነሻ አድርጎ ዕዙ በውጤት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። እስከአሁን የተወጣቸው ተልዕኮዎች እና የተገኙ ድሎች እንደተጠበቁ ሆነው ቀጣይም ኢትዮጵያ ከመላው የመከላከያ ሠራዊታችን  ብዙ የሠላም ሥራዎችን ተጠብቃለች። ሠላም ለሀገራችን ሠላም ለህዝባችን።

ቴሌ ብርን በመምሰል በቴሌግራም አማካኝነት እየተፈፀመ የሚገኝ የማጭበርበር ድርጊት ከሰሞኑ የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት የሆነውን ቴሌ ብርን መስሎ በመቅረብ እና የተለያዩ ሰዎችን በማናገር እየተፈፀመ የሚገኝ የማጭበርበር ድርጊት እንዳለ ኢትዮጵያ ቼክ መመልከት ችሏል። ይህ የቴሌግራም ቻናል ቦት "Telebirr Online customer servive" የሚል ስም ያለው ሲሆን የቴሌ ብር አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ደረጃ ለማሳደግ (upgrade ለማድረግ) በሚል የስልክ እና የሚስጥር ቁጥር በመጠየቅ የሚሰራ የማጭበርበር ድርጊት እንደሆነ ማየት ችለናል። "የቴሌ ብር ደንበኝነት ደረጃን (customer level) በኦንላይን ለማሳደግ በመጀመርያ ትክክለኛ የእርስዎ አካውንት እና ስልክ ቁጥር መሆኑን ማረጋገጥ ስላለብን ሙሉ ስም፣ ስልክ ቁጥር እና የቴሌ ብር ይለፍ ቃል (PIN CODE) ይላኩልን። በመቀጠል ከጥሪ ማዕከላችን የምንልክሎትን ስድስት ዲጂት የማረጋገጫ ኮድ (verification code) ይልኩልናል፣ ይህን አገልግሎት ለማግኘት ቢያንስ 1 ሺህ ብር አካውንትዎ ላይ ሊኖር ይገባል" በማለት የማጭበርበር ድርጊት እየተፈፀመባቸው እንደሆነ አንዳንድ ግለሰቦች ለኢትዮጵያ ቼክ አሳውቀዋል። ኢትዮጵያ ቼክ መገንዘብ እንደቻለው አንድ ሰው ስልክ ቁጥሩን እና የይለፍ ቃሉን ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ ከሰጠ የማረጋገጫ ቁጥሩ (verification code) እንዲመጣ ማድረግ ይቻላል። ይህን ከኢትዮ ቴሌኮም የሚመጣ የማረጋገጫ ቁጥር አሳልፎ መስጠት ደግሞ ለዘረፋ ያጋልጣል። በዚህ ዙርያ ኢትዮጵያ ቼክ ኢትዮ ቴሌኮምን ያነጋገረ ሲሆን የድርጅቱ ዋና የኮሚዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ መሳይ ውብሸት ይህ የቴሌግራም ቦት ሀሰተኛ መሆኑን አረጋግጠው "እኛ ብቸኛ የምንጠቀምበት ቦት "አርዲ/Ardi" የሚባል ሲሆን ይህም በተረጋገጠው የቴሌብር አካውንቶች ላይ ይገኛል" ብለዋል። የማረጋገጫ ቁጥርን አሳልፎ መስጠት ለመጭበርበር ስለሚያጋልጥ ጥንቃቄ እናድርግ። #EthiopiaCheck Scam Alert

#ጥቆማ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ✓ ሰልጣኝ አብራሪ/ፓይለት (Trainee Pilot) ✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን (Trainee Aircraft Maintenance Technician) ✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic) ✓ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Cors) ✓ ሰልጣኝ የመንገደኛ አገልግሎት ኢጀንት (Trainee Customer Service Agent) አመልካቾች ለምዝገባ ሊያሟሉ የሚገባቸው፦ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውንና ኮፒው፣ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ፣ የልደት ካርድ፣ የታደሰ የቀበሌ የነዋሪነት ማረጋገጫ ካርድ እና አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ አመልካቾች ከተዘረዘሩት የሥራ መደቦች ውስጥ ማመልከት የሚችሉት በአንዱ ብቻ ነው። የምዝገባ ጊዜ፦ ከነሐሴ 10 እስከ 25/2015 ዓ.ም ምዝገባ ፦ በተቋሙ ኢሚል አድራሻ ኢሚል ethiopianairlinevacancy@gmail.com የተመዝጋቢዎች ፎርም https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdvTQgKpgGZZlwJFSL5CxZESJvmVduTU3zwXpiWPS8Igcm8HA/viewform?usp=pp_url የስልጠናው ቦታ፡- ➤ አዲስ አበባ በኦንላይን፣ ➤ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ደብረ ማርቆስኦኒቨርሲቲ፣ ➤ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ሮቤ ቲቺንግ ኮሌጅ፣ ➤ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ➤ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ማሳሰቢያ  ይህ ምዝገባ ሲያልቅ ስልጠናው  የሚጀምር ሲሆን ተመዝጋቢዎች የማመልከቻ ፎርም ሲሞሉ ለስልጠናውን ብር እንደሚከፍሉ ተቋሙ አሳውቋል (ተቋሙ ያወጣው ማስታወቂያ ከስር ተቀምጧል።)

👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneCommand ሰብስክራይብ ያድርጉን 👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034