cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

"ኢ ቶ❤️ዮጵ" ግጥም(በAbi)

ለወዳጅ ለጓደኛ ግጥም እንዲፃፍላቹ ምትፈልጉ አናግሩን እንዲሁም ...ግጥም ያላቹ ደሞ ላክ ላክ አርጉልን..... @abironaldo #ምርጥ 👇 -ግጥም ❤️ -አጫጭር ታሪኮች👏 -ምርጥ አባባሎች👌 -ሰነ ክዋክብት✨ ..... #ለመንገድ ...#አፍታ ....#ለፈገግታ ከተሰኙ ልዩ መስገንዘበያዎች ጋር !! @abipoem

Show more
Advertising posts
448
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ከጠዋት ጣይና - ከጨረቃ ብርሃን ? ከፊያሜታና - ከሸገሯ ሮማን ? እንዲህ ያለው ምርጫ ደስታ ነው እርግማን ? በረሃብ አይደለም በሲኦል አይደለም ፈጣሪ 'ሚቀጣህ ምርጫ እየሰጠ ነው ደስታ የሚያሳጣህ ። Hd @
Show all...
የስም ቀለም ጠፍቶ የዘመን ገፅ አድፏል ከስንት እልፍ ተራማጅ ቆሞ ቀሩ ያልፋል ትነፍሳለች ፀሀይ ይሞቃል ደመና እየኖርኩ ያለሁት ካቻምናን እን አምና እናምልሽ ደ'ሞ ለስንት ተሰባሪ ወድቆ ነው ሚነሳው የሚሉት እንቅፋት ምክር ይደመጣል የት ያየነው ሁሉም የት ቦታውን ሳይለይ ለመውደቅ ይመጣል እኔ በዚህ መሀል ከመቆም አልታረቅኩ ካለማሰብ ፍቺ ይኸውልሽ ዛሬም እንዳዲስ ኖራለው ዛሬም ለይ ስለንቺ እና ግን እወቂ የጠራሽ ለት እንደው የፍቅር ወዘና የትዝታ ስበት አለሁኝ በናፍቆት በስጋ ጥለሽኝ በነፍስ ካለሽበት ትመጪአለሽ አይደል? ልጅ አማን @Zefrata
Show all...
❤️💋በፍቅር ልሸኝህ🤦‍♀🤦‍♀ ጊዜ እንደማይቆመው ሰአትን ጠብቆ ማለዳ ለቀትር ቦታውን አስታጥቆ ደቂቃዎች ሰአት ቀናትና ወራት ለአመት ሲያዘግሙ በራሪ ሰከንዶች መርቄ ልሸኝህ ነበርን ተክቼ ትላንቴን ዛሬዬን አሁኔን እረስቼ ለካ ነበርን ማለት እንደዚ ይከብዳል ያ ሁሉ ትዝታ እንዳልነበር ያልፋል በሂወት መወሰን መደሰትም ያልቃል ሳቅም ተቀይሮ እንባ እንኩዋን ይደርቃል ለካ ነበርን ማለት እጅጉንም ያማል ምክንያት አልባ ሲሆን ውስጥንም ያደማል ቢለያይ ስሜቱ የሁለት አንዳችን ህመሙ ቢያጋድል አንዱ ላይ ቢገንም ሚዛኑ ቢዛነፍ ለብይን ባይሆንም ከሳሽም ተከሳሽ ሆኜ ቀርቤአለሁ ደስ ያለህን ፍረድ ደስ ያለህን በይን ይግባኝ አልጠይቅም ያሻህንም ተግብር ባይሆን ....................... ፍቅርህን በቃላት በተግባር ስትገልፀው መውደድንም ችለህ በእምነት ስትኖረው ይህን ሁሉ አይቶ ለሽሽት መቅረቤ ይቅርታ ለራሴ መውደድን መቀበል ለተሳናት ልቤ ላልታደለች ነብሴ አሺ በቃ hubi መርቄ ልሸኝህ ፍቅር እሚያፈቅረው ልዩ ማንነትህ ከደስታ አጣምሮ ሳቅህን ያብዛልህ💔 @hikpoem @hikpoem @jemthelast @abipoem ✍Hiku neberku/neqe ተፃፈ Le amar Date30/10/2014
Show all...
💞💞💞ተፈቃሪዬ❤️❤️❤️ እንደ ለሊት ሰላም ውስጥ እንደ ሚያድሰው የጀምበር ወገግታ ቀን እንደ ሚያፈካው የጠዋቷ ፀሀይ በጅግ ተናፋቂ ልክ እንደ ህፃን ሁልጊዜ አኩራፊ የቀትሩ ሀሩር ሁሌም ጉልበተኛ በፍቅር ምተሀት የታየ አስማተኛ መበገርን ማያውቅ ሽንፈት ያልዳበሰው ሁሉን ተቆጣጥሮ እጅን በሚያሰጠው በተሰጠው ልኬት በስልጣኑ ቀመር የቀትሩ ሀሩር ከቶም አይበገር ፀሀይን ስጠራ ፀሀዬን አስታወሰኝ በኔ ላይ ጀግኖ እኔነቴን ቀማኝ ህልሜንም ሰውሮ እሱን አሳለመኝ ኮልታፋ አንደበቱን ሳቢ ፈገግታውን ማራኪ ሳቁን ውብ ማንነቱን ደስ ከሚል እብደት የተገኘ ልቡን ለፀሀዬ ጥላ ከለላ ብፈልግ ለካ የኔ ፀሀይ በጥላ አይከለል ልደብቅህ በቃ አሙ የኔ ልኡል ልከልልህ ብዬ ሆንኩልህ ጨረቃ ማንም ላይጋራኝ ላቶነኝ ፈረቃ የተፀነሰ ፍቅር መወለድ የራበው የታፈነ ናፍቆት ፍንዳታ የቀረበው እልፍ አእላፍ ናፍቆተረ በልቤ ተከትቦ ሊገለኝ ነው መሰል ................. አማሬን አምጪ ብሎ አንገብግቦ አንድ ፀሀይ ብትኖር ለአንድ ጨረቃ ምድር ብትከለል በብርሀን ታጭቃ ኮከቦች ቢኖሩ እይታ ሚያዛቡ ከፀሀይ አርቀው ጨረቃን ሚስቡ እይታዬን ጋረድኩ ከፀሀይ እራኩኝ ባንተ ውብ ነብስ ስር እራሴን ሰወርኩኝ መዳጁ ልቤንም አንተን ያስወደደው መውደዴን ወደድኩት ........... በፍቅርህ ተማርኮ ምርኮኛህ የሆነው ዛሬ በእቅፍህ በጅህ እንዳለሁኝ ቃልንም ግባልኝ ፍቅርህን አሳየኝ ሀላልህ አድርገህ በጉድለትህ ሙላኝ ደስታችን ይሟላ እንሁን አንድ አካል ሸይጣን ከኛ ይራቅ በኒካህ እንከለል ከቤተሰብ ዘመድ በዱአ አስወጣኝ እኔነቴን ወስደህ አንተነትን ስጠኝ ✍ hiku neberku/ neq ተፃፈ ....... le amar date 17/10/2014 @hikpoem @jemthelast @hikpoem @abipoem
Show all...
❤️❤️ልብህን አደራ🙏🙏 ደስ የሚል ማንነት አስደሳች ልቦና የራስ ልዩ ጥበብ ገራሚ ስብእና ፍቅርን የሚያኖር በ እፁብ ሰረገላ በ አማን በደስታ ሰርክ የማይላላ በብዛታ ማይሰለች በማነስ ማይደበዝዝ ቅንጣት ፍቅር ቀምሶ ልብን የሚመርዝ እኔነትን ለቆ አንተነትን መያዝ በእንጭጩ ልቤ በአፍታ ልጅነት ተፈቅሮ አፍቅሮ ባላየው ጊዜያት ድንገት ብትከሰት ልቤን ብትረታ ወደቁ ተሸነፍኩኝ መኖሬም ተረታ ስቀርብህ ስትርቅ ስርቅ ስትቀርበኝ ደስታህን ለማየት ደስታዬን ሲያሸሸኝ ልብህ ወድጄ ፍቅርህን አምኜ ከፍቅርም በላይ ማፍቀሬን አፍኜ ከመውደድም በላይ ውዴታዬኝ ችዬ ደስታን ልሰጥህ ደስታዬን ገድዬ መኖርን መረጥኩኝ ባንተ ተከልዬ ዛሬ ሀዘን ደርሶ በኔ ሳይሳለቅ ፍቅርህ ልቤ ገብቶ በደማቁ ሳይደምቅ አውቃለሁ አምናለሁ ............. መውደድ ማይሰለች ንፁ ልቦናህን መስዋት ከፋዩ አፍቃሪ ልብህን ዛሬን እየኖሩ ነገን የሚያስናፍቅ ሳቢ ፈገግታህን ጆሮ ላይ ሚያቃጭል ውብ አንደበትህን እውነትን የሚኖር ልዩ ማንነትን ዛሬ ልብህ ዞሮ ብትሆን ደንዳና ፍቅርህ ከጉም ተኖ ስሜትህ ቢፀና ከቶም አልከስህም ጎድተኸኛል ብዬ ደሞም አልጠላህም በፈጣሪ ምዬ ባይሆን ልብህ አደራ!!......... ጠብቃት በብዙ አኑራት በደና ክፍት ቦታ መተው ፈተና ነውና አጥብቀህ ጠብቃት ልብህን አደራ በችግር በደስታ በሀዘን መከራ ህልምህ እውን ሆኖ ደስታህ ተንሰራፍቶ ሳቅህን ያሳየኝ ፈጣሪ አሳክቶ የኛ እህል ውሀ አልሰመረም እና አትርሳኝ አልልም መቼም ሰውነህና ግን እንደ ትላንቱ አስታውሰኝ አልልም ጥላቻንም ፍቅር መሸከም አልችልም በዝምታ ልርሳህ እራሴን እስካገኝ የመውደዴን ብስራት ፅድቁን እስከማገኝ።። @abipoem @abipoem ✍Hiku neberku/neqe Date 11/09/2014
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.