1 334
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+4730 days
Posts Archive
1 334
#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_6
#ሐዲሥ 49 / 396
ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት ዐብደላህ ኢብኑ ዑትባህ ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ)፥ አስተላልፈዋል፦ “በነቢዩ (ﷺ) የሕይወት ዘመን የሰዎች (እውነተኛ) ማንነት በራዕይ (ወሕይ) ይገለጽ ነበር። ራዕዩ (ወሕዩ) ተቋርጧል። ስለዚህም አሁን ማንነታችሁን የምንወስነው በገሃድ በምናየው ሥራችሁ ነው። መልካም (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን እናምነዋለን። እናቀርበዋለን። ውስጡን የመፈተሽ መብት አልተሰጠንም። ውስጡን አላህ ይፈትሸዋል። ክፉ (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን ደግሞ አናምነውም። እውነት ብለን አንቀበለውም። ውስጡ መልካም እንደሆነ ቢናገረም። (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሰዎችን በግልጽ ከሚያሳዩት ባሕሪና ሥራ አንጻር ብቻ እስልምናቸውን መቀበል ግድ ነው። ውስጥን መፈተሽ የሰዎች መብት አይደለም።
2/ መልካም ኒይያ (ልበ-ውሳኔ) ከሸሪዓዊ ቅጣት አያድንም።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
1 334
#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_5
#ሐዲሥ 49 / 395
ጁንዱብ ኢብኑ ዐብደላህ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፥ የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንድ የሙስሊሞች ጦር ወደ አጋሪዎች አዘመቱ። (ሁለቱ ኃይሎች) ተገናኙ። ከአጋሪዎች መካከልም ከሙስሊሞች አንዱን (በመግደል) ከፈለገ የሚገድል (አልሞ የማይስት) አንድ አጋሪ ነበር። ከሙስሊሞች መካከል አንዱ _ ኡሳማ ኢብኑ ዘይድ ነው ብለን እናስባለን_ ሰውየው እስኪዘናጋ ጠብቆ (ሊገድለው) ሰይፍ ሲያነሳ (አጋሪው)፦ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ” አለ። ግና ገደለው። ብስራት (መልዕክት) ነጋሪው ወደ አላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዘንድ ቀረበ። ጠየቁት፡፡ የሆነውን ሁሉ ይነግራቸው ጀመር። የሰውየውን ሁኔታና ምን እንደ ፈፀመ ሲነግራቸው (ገዳዩን) ጠርተው “ለምን ገደልከው?” ሲሉ ጠየቁት፡፡ “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሙስሊሞችን አወከ። እገሌን፥ እገሌን ገደለ” በማለት ስሞችን ዘረዘረላቸው። “ዘመትኩበት፡፡ ሰይፍ ሲያይ ላ ኢላሀ ኢልለላህ አለ” ሲልም (ምክንያቱን) ነገራቸው። የአላህ መልዕክተኛም፥ “ገደልከውን?” አሉት፡፡ “አዎ” አላቸው። “በዕለተ ትንሳኤ ላ ኢላሀ ኢልለላህ ስትመጣ ምን ልታደርጋት ነው?” አሉት፡፡ “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ምሕረት ይጠይቁልኝ” አላቸው። “በዕለተ ትንሳኤ ላ ኢላሀ ኢልለላህ ስትመጣ ምን ልታደርጋት ነው?” ከማለት ውጭ ያከሉት ነገር የለም። (ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
፨ ይህና ከዚህ ቀደም የተወሳው ሐዲሥ የሚተርኩልን አንድ ዓይነት ክስተት እንደሆነ ዑለሞች ይናገራሉ። የትረካ ስልቱ የተለያየው ሐዲሡን ያስተላለፉት ግለሰቦች በመለያየታቸው ነው። ስለዚህ ለላይኛው ሐዲሥ የተዘረዘሩ አስተምህሮዎችን ይህም ሐዲሥ ያስተምራል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
1 334
#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_4
#ሐዲሥ 49 / 394
ኡሳማ ኢብኑ ዘይድ (ረ.ዐ) ተከታዩን አስተላልፈዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) የጁሀይና ጐሣ አባል ወደ ሆነው ጁሀይና ወደ ተባለ ጦር አዘመቱን። ሰዎችን በጧት መጣንባቸው (ማልደን ዘመትንባቸው)። እኔና አንድ የአንሷር ሰው ከነርሱ ከሆነ አንድ ሰው ጋር (ፍልሚያ) ተገናኘን። ስንከበው “ከአላህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም” አለ። የአንሷሩ ሰው እጁን ሰበሰበ። እኔ ግን በጦር ወግቼ ገደልኩት፡፡ መዲና ስንገባ ይህ (ድርጊቴ) ለነቢዩ (ﷺ) ተነገራቸው። “ኡሳማ ሆይ! ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት እኮ ከግድያችን ለመጠበቅ ነው” አልኳቸው። “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ በድጋሜ። ከዚያን ቀን በፊት ባልሰለምኩ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን ጥያቄ) ደጋገሙት፡፡ (ቡኻሪና ሙስሊም)
በሌላ ዘገባ ደግሞ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ)፦ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት ሰይፍ ፈርቶ ነው” አልኳቸው። “የተናገራት ከአንጀቱ ይሁን ከአንገቱ ልቡን ከፍተህ አይተኸዋልን?” አሉ። የሰለምኩት የዚያኑ ቀን በሆነ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን አባባል) ደጋገሙት፡፡
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው መስለሙን ለመቀበል ግልጽ ቃል ወይም ተግባር ማየቱ በቂ ነው። ውስጥን መፈላፈል አግባብ አይደለም። ይህ ሸሪዓዊ ድንጋጌ “ውስጡ አልሰለመም ይሆናል” በሚል ሰበብ ብቀላ ለሚሹ ወገኖች መንገድ ለመዝጋት ነው።
2/ የአላህ መልዕክተኛ በኡሳማ ላይ የሞት ብይን (ቂሷስ) ያላስተላለፉት ነገሩ ግልጽ ስላልሆነለት (ሹብሃ ስለነበረበት) ነው። የሞት ቅጣት በእንዲህ ዓይነት ሹብሃዎች ይቀራል። ይሁንና የደም ካሳ (ዲያህ) አይቀርም።
3/ ታላቅ ወንጀል የሠራ “ከዚያ በፊት ባልሰለምኩ” ብሎ መመኘት አይፈቀድለትም። ኡሳማ ይህን ያለው _ የሚፈቀድ ሆኖ ሳይሆን _ ከነቢዩ ጠንካራ ውግዘት የተነሳ ልቡ በፍርሃት ስለራደና ስለተጨነቀ ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
