H@ppïy
የምትማሩበት እራሳቺሁን የምትቀይሩበት የፍቅር💛 ጥቅስ ምክሮች ሌሎችንም💞💛 የምታገኙበት ▬▬▬▬▬▬▬▬►🍀 DON'T WORRY, ♥♥BE♥♥ ╗╔╔╗╔╗╔╗╗╔ ╠╣╠╣╠╝╠╝╚╣ ╝╚╝╚╝ ╩ ╩ ❕ 😞 ➔ ❌ 😃 ➔ ⭕ 🌸◄▬▬▬▬▬👇👇▬▬▬ 🌺🌹🌸🍀 @hawlitiii
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
188
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
😰ለምቶዱት ሰው ስትሉ የምትጠሉትን
ነገር መውደድ ትጀምራላቹ
እንደዚህማ በፍፁም አልሆንም ያላቹት ሰው ሆናችዋል💔
የሆናቹትም ግን የወደዳቹትን
ላለማጣት ነው…………
@hawlitiii
Photo unavailableShow in Telegram
አልደነቅም ...... የምትነግረኝን ነገሮች ሆኜ አልፊያቸዋለሁ ...... እየተራመድክበት ያለኸውን መንገድ በድል ካጠናቀቅኩ ቆየሁ....... የባሰና የለየለት ፈተና ውስጥ ለመሆን ዝግጅቴን ጨርሻለው ስልህ በልበ ሙሉነት እንደምወጣው ስለማምን ነው........
ና ...... ጆሮ ካለህ አልቅሼባቸው ግን ደግሞ ታግሼ ስላሳለፍኳቸው ውጥንቅጥ ጊዜዎቼ ልንገርህ......... የሚደላ ሜዳ ላይ ስላልተረማመደው........ የጎረባበጠ ድንጋይ ስላቆሳሰለው ..........እየሻረ ስላለው የውስጥ እግሬ ላውጋህ...........
" መቼ ፈተናን ለመፈተን ደርሰሽ? " አትለኝም አይደል? ....... መገረምንም፤ መደነቅንም እፈቅድልሃለው ......... እያንዳንዱን ልተርክልህ ዝግጁ ነኝ........ አለፍኩ ብዬ ሳይሆን የሚቀረኝን ደግሞ ጠንቅቄ ስለማውቀው..........
ስነግርህ ላግዝህ ነው ........ ሳወጋህ እንድታዝንልኝ ሳይሆን ለሚመጡት ፈተና ደጋፊዬ እንድትሆን ነው ....... ስነግርህ ያለፈ እንባዬን እንድታብስልኝ ሳይሆን የሚመጡት የዕንባ ዘለላዎቼ ላይ አንተ እንዳትገኝባቸው ነው ......... ስነግርህ ለሳቄ እንጂ ለሀዘኔ ምክንያት እንዳትሆን ነው........
ስለማልደነቅባቸው......... በድል ስለተወጣዋቸው......... ስለምኮራባቸው ነገሮች ጆሮህን ከነልብህ ያዋስከኝ ቀን እተርክልሃለው !.......
.
.
🦋 @hawlitiii ||
@hawlitiii
Photo unavailableShow in Telegram
አለማፍቀር እኮ የምድርን የተዘበራረቀ ደስታ የሚሰጥ ስሜትን...... የሰው ልጅ ሊደርስበት የሚችለውን የጥንካሬ ጥግ...... እራስን ውብ አድርጎ በራስ ላይ ሌላን አንግሶ የራስ ያለመሆንን ጥግ ........... በፍቃደኝነት ጎንበስ ብሎ መገዛትን.... መልካም የሚባሉ የህይወት ገፆችን መመልከቻ ቁልፍ ማጣት ነው!...…...
አለማፍቀር የማጣት ፍርሀትን........ ያለምክንያት መናፈቅን....... ያለትግል መረታትን..... ከራስ ላይ መገለልን እንዳናይ የሚያግድ ግድግዳ ነው........
አለማፍቀር አለም ላይ ያሉ ውብ..... አስደሳች..... እጅግ አስከፊ የሚባሉ ስሜቶችን አለማጣጣም እና አለማወቅ ነው.......
ምክንያት አልባነት የፍቅር መሰረት ነው......
ያለምክንያት ማፍቀር........ ያለምክንያት መፈለግ..... ያለምክንያት መናፈቅ..........ያለምክንያት የራስ አለመሆን....... ያለምክንያት ..........
ምክንያቱም ለሁሉም ፍቅር በቂው ምክንያት ነው፡፡
ሳላወራህ መቆየት መፍራቴን........ ሳላይህ መሰንበትን መጥላቴን....... ድምፅህን የመስማት ጉጉቴን እኮ እወደዋለሁ....... ፍቅር ነዋ!......
.
.
@hawlitiii
Photo unavailableShow in Telegram
እንዳልመለስበት አድርገህ ድክመት እና ጥፋቶቼን ስለምታሳየኝ ወድሃለው....... ሰዎችን መፈተን ባይዋጣልኝም ሆን ብዬ ማጥፋት ወዳለው..... ለምን ካልከኝ...... የልብ ወዳጄ ጥፋቴን አይቶ ዝም የሚለኝ አይደለም..... ለኔ የቀረበ ለራሴው ጉዳይ እኔን የሚጣላኝ እንደሆነ አምናለው......
ዝምታ አንድም ለጥልቅ ህመም..... አንድም ለቸልታ..... አንድም ደግሞ ከራስ ለመማከር....... የትኛውን ዝምታ ዝም እንዳልኩህ ለማወቅ እኔ ጋር አትምጣ....... ከራስ ጋር ለመማከር የሚሆነውን ዝምታ መርጠህ ዝም በል........
ዝም ያልኩህ ጊዜ የሆነ ነገርህን አጥቼዋለው...... የሆነ ነገሬን ነጥቄሃለው....... አስከመች?..... እንጃ...... ምናልባት ዝምታው እስኪሰበር!......
.
.
@hawlitiii
💡ማነው?
ማነው?
🔸ብርሃንና ጨለማን ፥ ሜዳና ተራራን ፥ ፍቅርና ጥላቻን ፥ የሕይወትን ዉጣ ዉረድ በዉስጡ ሳያልፍ ፥ በዉስጡ ጥልቅ የመኖር ግንዛቤ ያገኘው?
ማነው?
ባለንበት ምድር ያለ አንዳች ችግር ጥበብን ያጠና?
ማነው?
🔹በቤተሰብና በሕብረተሰቡ ዉስጥ ቢያንስ ቢያንስ መጠነኛ ግጭት ሳያጋጥመው ፍቅርና ሰላምን ያየ?
ማነው?
🔸በዓለም ላይ ፈተና ሳያጋጥመው ከተለመደው የሕይወት ዕርዳታ ሳይወጣ ታላቅ ተግባርን ያከናወነ?
__ማንም የለም !
🔹ሕይወት ማዕበሉንና ወጀቡን ዳር ይዘን ተግ እስኪል እንድንጠብቅ አትፈልግም ፥ ይልቁንስ በዝናቡና በወጀቡ መካከል ሆነን መደነስን እንድንለምድ እንጂ።
ደግሞም
🔸አምላክ ስቃይ አልባ ቀናትን ቃል አልገባልንም።ለሃዘን አልባ የፈንጠዝያ ጊዘያትም ቃሉን አልሰጠንም፡፡ዝናብ የሌለባቸዉን ጸሃያማ ቀናትንም ተስፋ አልሰጠንም።ይልቅ ለስቃይና ለመከራችን ጥንካሬን ፥ ለሃዘናችን መጽናናትንና ለመንገዳችን ብርሃንን ነው ቃል የገባልን፡፡
እናም
🔹ፈጣሪያችንን መለመን ያለብን ችግሮችን ከእኛ እንዲያርቅልን ሳይሆን ፥ ችግሮቻችንን ተጋፍጠን በአሻፊነት እንድንወጣ ጥንካሬውን እንዲሰጠን ነው፡፡
እኛ የቻልነዉን ካደረግን ፥ ፈጣሪ ደግሞ ያልቻልነዉን ያደርግልናልና፡፡
ጥንካሬዉን ይለግሰን፣
join 👇join👇join👇join👇😁
@hawlitiii❤️
@hawlitiii🥰
@hawlitiii❣
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.