🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts
Open in Telegram
ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100
Show more2 214
Subscribers
+124 hours
-67 days
-3430 days
Posts Archive
Repost from NESIHA TV | ነሲሓ ቲቪ
የተከበራችሁ የነሲሓ ቲቪ ቤተሰቦች
የነሲሓ ቲቪ ስርጭት ይመለስ ዘንድ መላው የነሲሓ ቤተሰቦች ጠንካራ ርብርቦሽ በማድረግ ላይ ናቸው። ኢን ሻ አላህ በናንተ ትብብር በቅርቡ ይመለሳል።
ነሲሓ ቲቪ ለኢስላማዊ እውቀትና ዳዕዋ ወሳኝ መድረክ ነውና በዚህ ጣቢያውን በዘላቂነት በምናስቀጥልበት ዘመቻ ኃላፊነትዎን ይወጡ። ሁላችሁም የተቻላችሁን ድጋፍ እንደምታደርጉ ተስፋ እናደርጋለን።
ጣቢያውን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚደረገውን ዘመቻ በማገዝ ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው።
የሚከተሉትን አካውንቶች በመጠቀም የበኩልዎን ድጋፍ ያድርጉ።
ባረከላሁ ፊኩም!
– ንግድ ባንክ 444 ወይም 1000145615929
– ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል 1445091300001
– አቢሲኒያ ባንክ 73169062
– ንብ ኢንተርናሽናል 7000025634638
– ዘምዘም ባንክ 7122
– አዋሽ ባንክ 01410844116300
https://t.me/nesihatv
ክሪስማስ እና መሰል በዓላትን ማክበር በኢስላማዊ ማንነት ማፈር እና ሌሎችን ለመምሰል መጣር ነውና አይፈቀድም። እንደውም አላህ በቁርአን ላይ የጠቀሰውን የሙእሚኖች ባህሪ የሚፃረር የጥፋት እርምጃ ነው። አማኞች አያከብሩም!!
{ وَٱلَّذِینَ لَا یَشۡهَدُونَ ٱلزُّورَ وَإِذَا مَرُّوا۟ بِٱللَّغۡوِ مَرُّوا۟ كِرَامࣰا }
እነዚያም በእብለት ላይ የማይገኙ፤ በውድቅ ቃልም ባለፉ ጊዜ የከበሩ ኾነው የሚያልፉት ናቸው Al-Furqân: 72
ታላቁ ሰሐቢይና የቁርአን ተንታኝ ኢብኑ ዓባስ (በእብለት የማይገኙ ወይም የማይመሰክሩ) የሚለውን (የሙሽሪኮች በአላት ብለው) እንደተረጎሙት ተዘግቧል።
አንዳንዶች እንደሚያስቡት ኃይማኖታዊ መቻቻል ወይም ስልጣኔ አይደለም። በርግጥ የእነሱ ከንቱ ምኞት በዚህ አይነቱ ማንነት እንድንታነፅ ነው። አላህም አትታዘዙ ብሎናል፦
(فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ)
አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ Al-Qalam 8 - 10
አላህ ይጠብቀን!
@abujunaidposts
{ٱلَّذِینَ قَالَ لَهُمُ ٱلنَّاسُ إِنَّ ٱلنَّاسَ قَدۡ جَمَعُوا۟ لَكُمۡ فَٱخۡشَوۡهُمۡ فَزَادَهُمۡ إِیمَـٰنࣰا وَقَالُوا۟ حَسۡبُنَا ٱللَّهُ وَنِعۡمَ ٱلۡوَكِیلُ}
እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፡- «ሰዎች ለእናንተ (ጦርን) አከማችተዋልና ፍሩዋቸው» ይሉዋቸውና (ይህም) እምነትን የጨመረላቸው «በቂያችንም አላህ ነው ምን ያምርም መጠጊያ!» ያሉ ናቸው፡፡
[Surah Âl-`Imrân: 173]
___
@abujubaidposts
የባጢል ሰዎች አጃቢ የፔጅና ግሩፖቻቸው አሟሟቂ እንዳንሆን!
√ እራስን ማጥራት ግዴታ ነው!
በሳንባ በሽተኞች መካከል፤ በተበከለ አየር ውስጥ ካለመከላከያ የሚኖር ሰው ስለጤንነቴ እጨነቃለው ቢለን አትቀልድ እንለዋለን።
ለፀረ ኢስላም አቡጃህሎች ጆሮውን ያዋሰ ሁሉ ሊነቃ ይገባዋል። ግሩፓቻቸውን ያሞቁ ፔጆቻቸውን በላይክ ያደመቁ ሁሉ ሊያስቡበት ይገባል። ለአላህና ለመልእክተኛው ያላቸውን ክብር፤ ለኢስላም ያላቸውን ቁርጠኛ እምነት ካስተዋሉ ከከሀዲያን ጋር ለመቀመጥ ትእግስቱ አይኖራቸውም። አራስን ማፅዳትም ተቀዳሚ ተግባራቸው ይሆናል።
( وَقَدْ نَزَّلَ عَلَيْكُمْ فِي الْكِتَابِ أَنْ إِذَا سَمِعْتُمْ آَيَاتِ اللَّهِ يُكْفَرُ بِهَا وَيُسْتَهْزَأُ بِهَا فَلَا تَقْعُدُوا مَعَهُمْ حَتَّى يَخُوضُوا فِي حَدِيثٍ غَيْرِهِ إِنَّكُمْ إِذًا مِثْلُهُمْ ) النساء/140 .
«በእናንተም ላይ በመጽሐፉ ውስጥ፤ የአላህን አንቀጾች በርሷ ሲካድባትና በርሷም ሲላገጥባት በሰማችሁ ጊዜ፣ በሌላ ወሬ ውስጥ እስከሚገቡ ድረስ ከነርሱ ጋር አትቀመጡ ማለትን በእርግጥ አወረደ፤ እናንተ ያን ጊዜ ቢጤያቸው ናችሁና፤ አላህ መናፍቃንን እና ከሐዲዎችን በሙሉ በገሀነም ውስጥ ሰብሳቢ ነውና»
ኒሳእ 140
ኢስላምን ከምንጩ መማር፤ ልብን ንፁህ በማድረግ፤ እራስን በእውቀት በማበልፀግና በአላህ በመታገዝ ማንኛውንም አይነት መደናገርና የቀልብ በሽታ መከላከል ይቻላል።
የአላህን ውዴታና ፍቅር ከፈለግን ኢስላማዊ እውቀትን ከትክክለኛ ምንጮች እናጣጥም።
ባወቅን ቁጥር ብርሀን እንደሆነና ጨለማን እንደሚገላልጥ እንረዳለን።
አዎ! ኢስላምን ከምንጩ እንረዳው፤ ያን ግዜ ለሚነሱ ሹቡሀቶች ሁሉ የኢስላም ሊቃውንት ምን ያክል የማያዳግሙ ምላሾችን እንደሰጡ በዝርዝር ማወቅ እንችላለን። እነዚህ ግሳንግስ ማወናበጃዎች ሁሉ በቁርአናዊ አስተምህሮ እንደሸረሪት ድር ሲበጣጠሱ እናስተውላለን።
ኢስላምን ስንኖረው ጉዞአችን መሰናክሎች የተደረደሩበት ነው። ስሜታችንን ተከትለን ለዱንያ እጅ ሰጥተን ከመስመር እንድንወጣ፤ አለያም ውዥንብሮችን በመስማት መደናገር ውስጥ እንድንገባ ሌት ተቀን የሚለፉ የሸይጣን ወታደሮች ብዙ ናቸው። ከኛ የሚጠበቀው፤ ጥሩ የጉዞ ጓደኞችን መቅረብና ጉዞአችንን የሚያሰናክሉ ሽፍቶችን መራቅ ነው።
አላማ ያለው ሰው ለስኬት የሚያበቁትን እርምጃዎች መሳት የለበትም፤ መርከብ በየብስ አይጓዝምና!!
Abujunaid
https://t.me/abujunaidposts/15
🍂 የትዕግስት ፍሬ በነብዩ አዩብ ታሪክ
https://youtu.be/nPQu_7p3wRg
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🍂 የተውሒድ እውነታ በቁርአን እይታ
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/360
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
ابو العتاهية » الخير أفضل ما لزمتا
عدد الابيات : 11
الخَيرُ أَفضَلُ ما لَزِمتا
وَالشَرُّ أَخبَثُ ما طَمِعتا
وَالناسُ ما سَلِموا عَلى الـ
ـأَيّامِ مِنكَ وَقَد سَلِمتا
أَمّا الزَمانُ فَواعِظٌ
وَمُبَيَّنٌ لَكَ إِن فَهِمتا
وَكَفى بِعِلمِكَ بِالأُمو
رِ إِنِ انتَفَعتَ بِما عَلِمتا
أَنتَ المُهَذَّبُ إِن
رَضيــتَ بِما رُزِقتَ وَما حُرِمتا
إِنَّ الأُلى طَلَبوا التُقى
يَتَيَقَّظونَ وَأَنتَ نِمتا
أَحسِن وَإِلّا لَم تُصِب
إِن أَنتَ لَم تُحسِن نَدِمتا
وَإِذا نَقِمتَ عَلى امرِئٍ
خُلُقاً فَجانِب ما نَقِمتا
وَارحَم لِرَبِّكَ خَلقَهُ
فَلَيَرحَمَنَّكَ إِن رَحِمتا
لا تَظلِمَنَّ تَكُن مِنَ الـ
ـأَحزارِ وَاعفُ إِذا ظُلِمتا
وَإِنِ اتَّقَيتَ اللَهَ في
كُلِّ الأُمورِ فَقَد غَنِمتا
____
@Abujunaidposts
⛱️ ከተርቢያ ጥበቦች
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/341
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🔍 የከሽፉ ሹቡሃት ኪታብ መልእክቶች
👉 የመልክተኞች ተፃራሪ የሆኑ ሙሽሪኮች ሰዎችን ከመልክተኞች ሃይማኖት ለማራቅ እና ለማስወጣት የተለያዩ ማምታቻዎችን በማምጣት ያደናግራሉ። ከሽፉ ሹቡሃት እነዚህን የሙሽሪኮች ማመሳሰያና ማምታቻ ብዥታዎች ለማጋለጥ አጠር ተደርጎ የተዘጋጀ ኪታብ ነው። ከአመታት በፊት በአብነት ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር የቀረበ ባለ 8 ክፍል ደርስ ተጋብዛችኃል።
✍ የኪታቡ አቅራቢ፦
ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ዓብዲልወሓብ
🎙የደርሱ አቅራቢ፦
አቡ ጁነይድ ሳላህ አሕመድ
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🍂||• #تلاوات_تعجبني •||🍂
📖 [ أَفَمَن یَعۡلَمُ أَنَّمَاۤ أُنزِلَ إِلَیۡكَ مِن رَّبِّكَ ٱلۡحَقُّ كَمَنۡ هُوَ أَعۡمَىٰۤۚ إِنَّمَا یَتَذَكَّرُ أُو۟لُوا۟ ٱلۡأَلۡبَـٰبِ] الرعد ١٩
تلاوة متميزة جدا للشيخ محمد عابد من قيام ١٤١٠هے في المسجد النبوي
#ሸይኽ_ሙሐመድ_ዓቢድ
https://t.me/abujunaidposts/91
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
