en
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

Open in Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Show more
2 219
Subscribers
-124 hours
-77 days
-3530 days
Posts Archive
🌟 ብዥታና እውነታ! 👌 በአጥማሚዎች ሹቡሀት ላለመደናገር የሚያግዝ ወቅታዊ መልዕክት! 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/590 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የድብድብ ስፖርቶች ስፖርት መስራትና ራስን የመከላከያ መንገዶችን መማር ለአንድ ሙስሊም ጠቃሚ ነገር ነው። ነገር ግን በወህይና ሸሪዓዊ ደንቦች የታጠረ መሆን አለበት። ዑለማዎቻችን እንደ ቦክስ፣ ሙአይ ታይ፣ ዊንግ ቸን፣ እና ፍሪ ስታይል ሬስሊንግ... የመሰሉ ውድድሮች ውስጥ መሳተፍን እንደሚከለክሉ ማወቅ ይገባናል። ኢብኑ ባዝ፣ አል-ዑሰይሚን እና አል-አልባኒ ቦክስንና መሰል ውድድሮችን በመከልከል ላይ ስምምነት አላቸው። የሶስቱንም ፈታዋ ዩትዩብ ላይ ይገኛል። በተጨማሪም የኢስላማዊ ፊቅህ አካዳሚ በውሳኔ ቁጥር 50 (3/10) የቦክስ ውድድር ክልክል መሆኑን በመግለፅ የክልከላውን ምክንያቶች በዝርዝር አስቀምጧል። ኡለማዎቸ3 ለዚህ ክልከላ ከጠቀሷቸው ምክንያቶች የሚከተሉት ይገኙበታል፦ 1. አላህ ያከበረውን ፊት መምታት፦ የተመታው ሰው ሙስሊም ይሁን ወይም ሌላ (ሰላማዊ) ሰው፣ ፊትን መምታት አይፈቀድም። ቡኻሪና ሚስሊም ከአቡሁረይራ በዘገቡት ሀዲስ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፤ إذا ضرب أحدكم أخاه، فليجتنب الوجه «አንዳችሁ ሲመታ ፊት መምታትን ይራቅ» (ይህ የሙስሊም ዘገባ ቃላት ነው)። በሌላ ሐዲስ እንደተላለፈውም፦ لا تضرب الوجه «ፊትን አትምቱ» ኢማም አሕመድ ዘግበውታል። ኢብኑ ሐጀር፣ አልባኒና ሌሎችም ሀሰን ደረጃ ሰጥተውታል። 2. የፀረ-ተውሒድ የመጎንበስ ልማድ፦ ለሌላ አካል ማጎንበስና መስገድ (Incline/Bow) በሸሪዓ አይፈቀድም። የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ስለዚህ ተጠይቆ “ለሙስሊምም ሆነ ለካ_ፊ § ር በአክብሮት (ሰላምታ) መልክ በሰውነት የላይኛው ክፍል ወይም በራስ ብቻ መጎንበስ ቢሆንም እንኳ አይፈቀድም። ምክንያቱም በአክብሮት መልክ የሚደረግ መጎንበስ ዒባዳ ነው። ዒባዳ ከአላህ ብቻ በቀር ለማንም አይፈቀድም" የቋሚ ኮሚቴ ፈትዋዎች 1/171 3. ጭካኔና ነፍስን ለአደጋ ማጋለጥ፦ በጭካኔ መተላለቅና ተቃዋሚን በጣም ለመጉዳት ማለም፣ እንዲሁም በዚህ ድርጊት ማጨብጨብና መደሰት አይፈቀድም። ለዚህም ታላቁ ኢስላማዊ መርህ "መጎዳትም ሆነ መጉዳት የለም! የሚለው ነው። እንደዚሁ አንድ ስፖርተኛ በራሱ ላይ ጉዳት ማድረስና ነፍሱን ለጥፋት መዳረግ አይፈቀድለትም፣ ምክንያቱም አላህ እንዲህ ብሏልና፦ ﴿وَأَنفِقُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَلَا تُلْقُوا بِأَيْدِيكُمْ إِلَى التَّهْلُكَةِ﴾ በአላህም መንገድ ለግሱ፡፡ በእጆቻችሁም (ነፍሶቻችሁን) ወደ ጥፋት አትጣሉ፡፡ በጎ ሥራንም ሥሩ፤ አላህ በጎ ሠሪዎችን ይወዳልና) አልበቀራ 195 እውነታውን ካጤንን በርካታ ቦክሰኞች በጨዋታ ወቅት በሚደርስባቸው ጉዳት ለሞት ተዳርገዋል፣ ለዚህም አንዳንድ ሙስሊም ያልሆኑ ተቆርቋሪዎች እንኳ ድርጊቱ እንደ ስፖርት እንዳይታይና እንዲታገድ ሲጠይቁ ይሰማል። 4. ተጨማሪ ጥሰቶች፡– ኡለማዎች በተጨማሪ፤ የሰውነትን private ገላ (ዓውራ) መግለጥ፣ ሙዚቃ፣ ኢኽቲላጥ፣ ግዜን ማጥፋትና መሰል ተጨማሪ ጥሰቶችንም ዘርዝረዋል። ጥንቃቄ፡‐ እነዚህን ውድድሮች ወደ "ሃይማኖታዊ ፉክክር" መቀየር እንዲሁም የሃይማኖት መገለጫ ዒባዳዎችን ከውድድሩ ውጤት ጋር ማያያዝ ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል። ዲን (ያውም ባልተፈቀደ ጨዋታ) ሊነሰር አይችልም። ይህን ተከትሎ ብሽሽቅ ውስጥ በግባት ሌላ ጥፋት ነው። ዲናችን ከዚህ ሁሉ በእጅጉ የጠራና የላቀ ነው! ለወጣቶቻችን ያለኝ ምክር፦ ነገሮችን በሸሪዓ ሚዛን ሳትመዝኑ አታጨብጭቡ። ህይወታችን ሁሉ ለአላህ ይሁን የሚል ነው። {قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَንُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ} «ስግደቴ፣ መስዋዕቴ፣ ህይወቴና ሞቴ ለአለማቱ ጌታ ለአላህ ብቻ ነው በሉ።» አላህ የበለጠ ያውቃል አበጁነይድ 18/8/2018

እንኳን ደስ አላችሁ! ነዋሪነቱ በመዲና የሆነው ወንድማችን ኡስታዝ ጣሀ አህመድ ልጅ ተማሪ ሀፍሷ ጣሀ አህመድ፤ የመዲና ከተማን በመወከል የመከተል ሙከረማ አካባቢዋ ክልል የቁርኣን ሒፍዝ ውድድር የሁለተኛ ደረጃን በማግኘቷ የተሰማኝን ደስታ እየገለፅኩ ወላጆቿን እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እወዳለው። አላህ ከችሮታው እንዲጨምራት፣ ለወላጆቿም የዓይን ማረፊያ እንዲያደርጋት እንዲሁም ከክፉ ነገር ሁሉ እንዲጠብቃት እለምነዋለው። ቁርኣን በዱንያም በአኺራም የክብር ማማ ነውና ሴት ልጆቻችንና እህቶቻችን ሐፍሷን አርአያ አድርገው የአላህን ቃል ለመሀፈዝና በኢትቃን ሙራጀዓ ለማድረግ እንዲተጉ ጥሪ አደራ እላለው። الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات!

الحمد لله، والصلاة والسلام على رسول الله، وبعد: لقد لاحظنا جميعًا في السنوات الأخيرة محاولات لتعزيز العلاقات مع السفارة الإير
الحمد لله، والصلاة والسلام على رسول الله، وبعد: لقد لاحظنا جميعًا في السنوات الأخيرة محاولات لتعزيز العلاقات مع السفارة الإيرانية من قبل المجلس الفيدرالي، تمثلت في تبادل الزيارات، وهو أمر يُعد مخالفًا لما استقر عليه المجلس منذ تأسيسه. كما ساءني اليوم خبر قيام رئيس المجلس الأعلى ونائبيه بحضور مجلس المآتم الذي أقيم في السفارة الإيرانية نعيًا للخامنئي. وهذا بلا شك أمر يحزن الغيورين على الإسلام من منسوبي المجلس وغيرهم، خصوصًا في ظل ما هو معروف من سعي إيران إلى نشر المذهب الرافضي الاثني عشري في الدول الإفريقية على وجه الخصوص، وما نتج عن ذلك من إثارة الفتنة بين المسلمين كما حدث في نيجيريا وعدد من الدول. وأود أن أوضح أولًا أن هذا النقد لا يعني بحال من الأحوال الوقوف مع الصهاينة الذين يحتلون فلسطين ويعتدون على الدول المجاورة وينتهكون سيادتها ظلمًا وعدوانًا، نسأل الله أن يكفينا شرهم؛ فموقفنا منهم ثابت. غير أن رفض هذا العدوان لا يبرر السكوت عن أخطاء تُلحق الضرر بالمسلمين أو تفتح أبواب الفتنة بينهم. ومما يدل على أن هذا التصرف غير مدروس وغير حكيم كون تصريح رئيس المجلس الفدرالي بقوفه مع إيران جاء في وقت قيام اعتداءات إيران وأذرعها بإطلاق الصواريخ على دول الخليج، بما في ذلك المملكة العربية السعودية، بلاد الحرمين وقبلة المسلمين، التي تربطها علاقات وطيدة ببلادنا منذ تأسيس المجلس، ولا شك أن هذا يتعارض مع مصالح المسلمين في البلاد ويسيء إلى علاقة المسلمين في هذه البلاد بالدول السنية الصديقة. كما أنه يتعارض بوضوح مع سياسة المجلس ومبادئه الراسخة منذ التأسيس؛ إذ تؤكد لوائح المجلس الأعلى للشؤون الإسلامية في إثيوبيا، والوثائق المرجعية المصاحبة، أن المجلس هو الممثل الشرعي للمسلمين من أهل السنة، ويقتصر دوره على رعاية شؤونهم والتعاون مع طوائفهم، دون الطوائف الشيعية التي تخالف نهج أهل السنة في معتقداتها تجاه الصحابة وأمهات المؤمنين وتغلو في آل البيت، ولا يشملها تمثيله بأي حال من الأحوال. وتاريخ المجلس – حسب علمي – لم يشهد علاقات مع الطوائف الشيعية إلا في حالات نادرة ومحدودة قوبلت بالاستنكار من قبل العلماء وقطاعات من المسلمين، ولم نعرف علاقات رسمية أو تعاونًا معلنًا مع السفارة الإيرانية كما يجري اليوم، وهو أمر خطير يستوجب الاستنكار. كما لا يخفى أن وصف الميت بأنه شهيد لا يجوز الجزم به؛ إذ إن الحكم لشخص بعينه بالشهادة من مسائل الغيب التي لا يُقطع بها إلا بدليل. ولذلك بوّب الإمام البخاري رحمه الله بقوله: «باب: لا يُقال فلان شهيد». ويزداد الأمر خطورة عندما يُطلق هذا الوصف على شخصية معروفة بعداء السنة والاعتداء على أهل السنة في عدد من الدول ونشر الأفكار المتطرفة من معاداة الصحابة إلى غير ذلك مما يخالف أصل الإسلام. ومن هنا، فإن الواجب على القائمين على المجلس أن يراعوا الأمانة التي حُمِّلوها، وأن يعلموا أن مسؤوليتهم دينية في المقام الأول لا سياسية، وأنهم مسؤولون أمام الله ثم أمام المسلمين الذين حملوهم هذه الأمانة. كما ينبغي لهم الالتزام بالمنهج الذي قامت عليه هذه المؤسسة، وتقديم مصالح المسلمين وثوابتهم الشرعية على أي اعتبارات أخرى. والله المستعان. أبو جنيد صالح أحمد ١٦ رمضان ١٤٤٧هے

🍂 ቁርአን የልብ ብርሃን! ⌚️ የ 60 ደቂቃ ሙሀደራ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/97 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

منظومة_مولانا_في_الرد_على_المستغيث_بغير_الله.mp37.19 KB

🗞 በተወሱል ርዕስ የሚነሱ ብዥታዎች እና እርምቶቻቸው! በራሪ ወረቀት.. ፓምፕሌት @emnetihintebiq

አሊምም ይሁን ተራ ሰው ሲሞት መቀበር ያለበት በሙስሊሞች መቃብር ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ሶሐቦችና ሰለፎች ሁሉ የነበሩበት ተጨባጭ ነው። عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله ﷺ قال «لا تجعلوا بيوتكم مقابر....» رواه مسلم، 1/539 ሙስሊም ከአቡሁሑረይራ በተዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ (ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ... ) በማለት የተናገሩትን በማስመልከት አልሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር «ሐዲሱ በግልፅ የሚያመላክተው፤ በማንኛውም መልኩ በቤት ውስጥ መቅበር እንደተከለከለ ነው» ብለዋል። [ፈትሁልባሪ 1/130] ይህ ግንዛቤ የአል ሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር ብቻ አልነበረም። የኢስላም አዒማዎች በዚሁ መልኩ ከልክለዋል። አል ኢማም ማሊክ እንዲህ ብለዋል፤ لا يُدفن أحد في بيته ولا في بستانه إلا لضرورة <ማንም ሰው ከአቅም በላይ በሆነ ሁኔታ (ዶሩራ) ምክንያት ካልሆነ በቤቱ ወይም በእርሻ ቦታው አይቀበርም!> ብለዋል። [አልሙደወነቱል ኩብራ 1/155] ለሽርክ መስፋፋት ምክንያት እንዳይሆን ወይም ሙስሊም ካልሆኑ ሰዎች ጋር ላለመመሳሰል እና መሰል ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸው። በተለይ ደግሞ በማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ክብር የሚቸረው ሰው ሲሆን ክልከላው ይጎላል። ምክንያቱም በተውሒድ ላይ የሚደቀነው አደጋ የከፋ ስለሚሆንና ብዙ መዘዞችን ስለሚያስከትል ነው። ወደ ጥፋት የሚያዳርሱ መንገዶችን መዝጋት (ሰድዱ ዘራኢዕ) ታላቅ መርሆ መሆኑ አያጠያይቅም። አል ኢማሙ አሽሻጢቢይ እንዲህ ብለዋል፤ <መሰረታቸው ፍቁድ (ሙባህ) እንኳን ቢሆን ወደ ክልክል ነገር የሚያዳርሱ ከሆነ መከልከል ግዴታ ነው። ስለዚህም ጥንቃቄ ይፈልጋል። በተለያዩ ግዜያት የተንሰራፉ መጤ እምነቶች መነሻቸው ቀለል ያለ ከገር ነበር። ተሰሚነት ያላቸው ኡለማዎችና ዱዓቶች የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል። ወላሁ አዕለም ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔭 የፀሀይና የጨረቃ ግርዶሽ የታላቁን ነብይ ሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ነብይነትን ያረጋግጣል! ነቢዩ ﷺ እጅግ የሚወዱት ብቸኛ ልጃቸው ኢብራሒም በሞተበት ቀን የፀሐይ ግርዶሽ ተከሰተና ሰዎች በእርሱ ሞት
🔭 የፀሀይና የጨረቃ ግርዶሽ የታላቁን ነብይ ሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ነብይነትን ያረጋግጣል! ነቢዩ ﷺ እጅግ የሚወዱት ብቸኛ ልጃቸው ኢብራሒም በሞተበት ቀን የፀሐይ ግርዶሽ ተከሰተና ሰዎች በእርሱ ሞት ምክንያት የተከሰተ ነው ብለው አሰቡ። የአላህ መልዕክተኛ ጠላቶቻቸው እንደሚሉት፤ ሀሰተኛ ነብይ፣ ለንዋይ እውቅናና ዝና የተነሱ ቢሆን ኖሮ ይህ መልካም አጋጣሚ በሆናቸውና እምነቱ ይሰርፅ ዘንድ ዝም ባሉ ነበር። ነገር ግን (አሷዲቁል አሚን) ይባሉ የነበሩት እውነተውኛና ታማኙ የአላህ መልዕክተኛ መድረክ ላይ በመውጣት በመውጣት ግልፅ መልዕክት አስተላለፉ፤ «ፀሐይም ሆነች ጨረቃ ከአላህ ታላላቅ ምልክቶች ውስጥ ናቸው። በማንም ሰው መሞት ወይም ህያው መሆን ምክንያት አይጋረዱም። የዚህ አይነት ነገር ስታዩ ስገዱ አላህንም ተማፀኑ» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበው ታል ይህ ክስተት ለመስለም ምክንያት የሆናቸው ብዙዎች ናቸው። ፈረንሳዊው ኦረንታሊስት ኤይሜል ደርመንግሀም (Emile Dermenghem) በነብያችን ታሪክ ዙርያ በፃፈው  መፅሀፉ ይህንን ሀዲስ ከጠቀሰ በኃላ «ይህ የውሸታምና ቀጣፊ ሰው ንግግር ሊሆን አይችልም!» በማለት ደምድሟል (ሀያቱ ሙሀመድ‐የዓረብኛ ትርጉም ገፅ 318) ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔭 የፀሀይና የጨረቃ ግርዶሽ የታላቁን ነብይ ሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ነብይነትን ያረጋግጣል! ነቢዩ ﷺ እጅግ የሚወዱት ብቸኛ ልጃቸው ኢብራሒም በሞተበት ቀን የፀሐይ ግርዶሽ ተከሰተና ሰዎች በእርሱ ሞት
🔭 የፀሀይና የጨረቃ ግርዶሽ የታላቁን ነብይ ሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ነብይነትን ያረጋግጣል! ነቢዩ ﷺ እጅግ የሚወዱት ብቸኛ ልጃቸው ኢብራሒም በሞተበት ቀን የፀሐይ ግርዶሽ ተከሰተና ሰዎች በእርሱ ሞት ምክንያት የተከሰተ ነው ብለው አሰቡ። የአላህ መልዕክተኛ ጠላቶቻቸው እንደሚሉት፤ ሀሰተኛ ነብይ፣ ለንዋይ እውቅናና ዝና የተነሱ ቢሆን ኖሮ ይህ መልካም አጋጣሚ በሆናቸውና እምነቱ ይሰርፅ ዘንድ ዝም ባሉ ነበር። ነገር ግን (አሷዲቁል አሚን) ይባሉ የነበሩት እውነተውኛና ታማኙ የአላህ መልዕክተኛ መድረክ ላይ በመውጣት በመውጣት ግልፅ መልዕክት አስተላለፉ፤ «ፀሐይም ሆነች ጨረቃ ከአላህ ታላላቅ ምልክቶች ውስጥ ናቸው። በማንም ሰው መሞት ወይም ህያው መሆን ምክንያት አይጋረዱም። የዚህ አይነት ነገር ስታዩ ስገዱ አላህንም ተማፀኑ» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበው ታል ይህ ክስተት ለመስለም ምክንያት የሆናቸው ብዙዎች ናቸው። ፈረንሳዊው ኦረንታሊስት ኤይሜል ደርመንግሀም (Emile Dermenghem) በነብያችን ታሪክ ዙርያ በፃፈው መፅሀፉ ይህንን ሀዲስ ከጠቀሰ በኃላ «ይህ የውሸታምና ቀጣፊ ሰው ንግግር ሊሆን አይችልም!» በማለት ደምድሟል (ሀያቱ ሙሀመድ‐የዓረብኛ ትርጉም ገፅ 318)

👌 መውሊድን የተመለከቱ ብዥታዎችና መልሶቻቸው 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 72 ደቂቃ ሙሀደራ (64 kbps = 34.65 mb) 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/105 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

እውን ሙዚቃና ዘፈን በኢስላም አልተከለከለምን? ✍🏻 ሙሀመድ ሀሰን ማሜ (ጥር 2003) ┄┄┉┉✽‌»‌‌🌼»‌‌✽‌┉┉┄┄ አንደሚታወቀው ኢስላም ሰፊና ጥልቅ አስተምህሮቶች፤ ረቂቅና ጥልቅ መመሪያዎችና
እውን ሙዚቃና ዘፈን በኢስላም አልተከለከለምን? ✍🏻 ሙሀመድ ሀሰን ማሜ (ጥር 2003) ┄┄┉┉✽‌»‌‌🌼»‌‌✽‌┉┉┄┄ አንደሚታወቀው ኢስላም ሰፊና ጥልቅ አስተምህሮቶች፤ ረቂቅና ጥልቅ መመሪያዎችና ድንጋጌዎች አሉት፡፡ ሁሉንም የህይወት ዘርፎች  ዳሷል።  ሳያስተምረን ያለፈው የህይወት ጉዳይ የለም። በተለያየ መልክና ዘዴ እያንዳንዱን የህይወት ክፍል በመዳሰስም ወደር የሌለው ሃይማኖት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንንም እውነታ የማንኛውም አማኝ ልቦናና ህሊና ያውቀዋል፡፡ ሆኖም በኢስላም ድንጋጌ እና መመሪያ ላይ በየጊዜው እና በየወቅቱ የተለያዩ ብዥታዎችና ውዥንብሮችን የሚፈጥሩ ሰዎች አልጠፉም፣ ነበሩም፣ አሉም፣ ይኖራሉም፡፡ በየጊዜው ብቅ ጥልቅ ከሚሉ በርካታ ውዥንብሮች መካከል የሙዚቃን ብይን የተመለከተው ይጠቀሳል። የራሳቸውን ግንዛቤ ለማስተላለፍ ሲፈልጉ፤ ኢስላም ስለዘፈንም ይሁን ስለሙዚቃ ክልክልነት የተናገረው ነገር የለም፡፡ ክልክል ለመሆኑ የቀረቡ መረጃዎችንም የወደቁና ተቀባይነት የሌላቸው እንደሆኑ፤ ሲጠኑ በሁለት እግር መቆም የማይችሉ  እንደሆኑ አድርገው በማቅረብ የሚነዙት ብዥታ ተራ አሉባልታ እንደሆነ በእዚህ መልዕክቴ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡ በተለይም ሰሞኑን አቶ ሀሰን ታጁ በሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ የጣዕም ልኬት የሙዚቃ ዝግጅት ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ይህ አይነቱን አመለካከት በስፋት ስላብራራ አጠር ያለ ምላሽ አዘጋጅቻለው። አላህ ስራችንን ሁሉ በኢኽላስ የተፈፀመ እንዲያደርገውነ እለምነዋለሁ።  እግዛንም ከእርሱ ብቻ እጠይቃለሁ፡፡ ዘፈንና ሙዚቃ በኢስላም የተከለከለ መሆኑን በተለያዩ ኢስላማዊ መረጃዎች ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ 1ኛ- ከቁርአን                  2ኛ- ከሐዲስ 3ኛ- ከሰሃቦች                  4ኛ- ከታቢዒዮች 5ኛ- ከአራቱ መዝሃቦች     6ኛ - ከኢጅማዑ አሰለፍ 1ኛ- ከቁርአን በሱረቱል ሉቅማን ቁጥር 6 وَمِنَ النَّاسِ مَن يَشْتَرِي لَهْوَ الْحَدِيثِ لِيُضِلَّ عَن سَبِيلِ اللَّهِ بِغَيْرِ عِلْمٍ وَيَتَّخِذَهَا هُزُوًا ۚ أُولَٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ مُّهِينٌ [٣١:٦] “ከሰዎች ያለ እውቀት ሆኖ ከአላህ መንገድ ሊያሳስትና ማላገጫ አድርጎ ሊይዛት አታላይ ወሬን (ለህወል ሀዲስ) የሚገዛ አለ፤ እነዚያ እነሱ አዋራጅ ቅጣት አላቸው፡፡” በእዚህ አንቀፅ ውስጥ “ለህወል ሀዲስ” (አታላይ ወሬ) ተብሎ የተሰየመውና ቅጣቱም አወራጅ ተብሎ የተዛተበት ምን ይሆን? መልሱን ከሰሃቦች ማግኘት ይቻላል፡፡ ሀ. አብድላህ አብኑ መስዑድ (ስለቁርአን ጥልቅ እውቀት ባላቸው ስመጥር ሰሃባ አንዱ ነው፡፡) ስለ “ለህወል ሀዲስ” (አታላይ ወሬ) ሲጠየቅ ሶስት ጊዜ በመማል “ዘፈን ነው ዘፈን ነው ዘፈን ነው” በማለት መመለሱን ኢብኑ አቡ ሸይባ፣ ኢብኑ ጀሪር፣ አልሃኪም፣ አልበይሀቂ እና ኢብልጀውዚ ዘግበውታል፡፡ ለ. አብደላህ ኢብኑ ዐባስ (የዑማው አዋቂና በቁርአን ማብራሪያ ላቅ ያለ እውቀት ያለውና ረሱልም “አላህ ሆይ ሃይማኖቱን አስገንዝበው የቁርአንንም ማብራሪያ አሳውቀው፡፡” ብለው ዱዓእ ያደረጉለት ስመ ጥር ሰሃባ ነው፡፡) ስለ (ለህወል ሀዲስ) “ዘፈንና መሰሎቹ ናቸው” ማለቱን ኢብኑ አቡ ሸይባ፣ (ቡኻሪ፣ ኢብኑ ጀሪር፣ አልበይሀቂ፣ እና ኢብኑ ጀውዚ ዘግበውታል፡፡) ሐ. አብደላህ ኢብኑ ዑመር (የመዲና ሙፍቲና የፊቂህ ምሁር ) ለሕወል ሀዲስን በማስመልከት “እርሱም ዘፈን ነው” በማለት አብራርቶታል፡፡ መ. ጃቢር ኢብኑ አብደላህ  (ከኢብኑ ዑመር ቀጥሎ የመዲና ሰዎች ፊቂህ እንዲሁም ሙፍቲ የነበረው) “ዘፈንና ማድመጡ ነው” ማለቱን ኢብኑ ጀሪር ዘግበዋል፡፡ ታዲያ ከእነዚህ ታላላቅና ስመጥር ሰሃቦች ይህን አንቀፅ በተመለከተ (ዘፈን) መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የሰሃቦች ማብራሪያ ማስረጃ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንም ማብራሪያ የተቃረነ አንድም ሰሃባ የለም፡፡ ሰሃቦችም እንዲህ ብለው እንደተረጐሙት ሁሉ ታቢዒዮችም በተመሳሳይ መልኩ አብራርተውታል፡፡ እንደሚከተለውም ዝርዝራቸውን እጠቅሳለሁ፡፡ 1.ሙጃሂድ ኢብኑ ጃቢር 2. ዒክሪማህ         3. መክሁል        4.ኢብራሂም አል ነኸዒ                           5. ዐጣእ          6.ሰዒድ ኢብኑ ጁበይ    7.አል ሐሰን አል በስሪ                                    8.ቀታዳህ ኢብኑ ደዓማ                                 9.መይሙን ኢብኑ ሚህራን                                       1ዐ. ሀቢብ ኢብኑ አቢሳቢት                                                       11. ዐምር ኢብኑ ሹዓይብ                         12. አብዱልመሊክ ኢብኑ ጁረይጅ                                                      13. ሰኢድ ኢብኑልሙሰይብ ናቸዉ፡፡ ሱረቱ ነጅም ቁጥር 59 – 61 أَفَمِنْ هَٰذَا الْحَدِيثِ تَعْجَبُونَ [٥٣:٥٩]وَتَضْحَكُونَ وَلَا تَبْكُونَ [٥٣:٦٠]وَأَنتُمْ سَامِدُونَ [٥٣:٦١]   “በዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?! ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን? እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡” ይህንም አንቀፅ በማስመልከት ዘንጊዎች ተብሎ የተተረጐመው ቃል በአረብኛው “ሳሚዱን” የሚለው ቃል ሲሆን ትርጉሙን በተመለከተ የየመን ቋንቋ እንደሆ በመጥቀስ “ዘፈን” እንደሆነ አብደላህ ኢብኑ ዐባስ ፣ ሙጃሂድ፣ ዒክሪማና አደሃክ ተናግረዋል፡፡ ሱረቱል ኢስራእ ቁጥር 64 وَاسْتَفْزِزْ مَنِ اسْتَطَعْتَ مِنْهُم بِصَوْتِكَ وَأَجْلِبْ عَلَيْهِم بِخَيْلِكَ وَرَجِلِكَ وَشَارِكْهُمْ فِي الْأَمْوَالِ وَالْأَوْلَادِ “ከእነሱ ያቻልከውንም ሰው በድምፅህ አታል በእነሱም ላይ በፈረሶኞችህም ለልብ በገንዘቦቻቸውም፣ በልጆቻቸውም ተጋራቸው፡፡” ሙጃሂድ ኢብኑ ጃብር (የአብደላህ ኢብኑ ዓባስ ታላቅ ተማሪ) የኢብሊስ ድምፅ ምንነት ሲገልፁ እንዲህ ነበር ያሉት፡፡ “እርሱም ጊና (ዘፈን)፣ ሙዚቃ መሳሪያ፣ ላግጣና  ከንቱ ነገር ነው፡፡” አድሃክም የዘፋኝ (የሙዚቃ መሳሪያ) ድምፅ ነው” ብለዋል ኢብኑል ቀይምም እንዲህ በማለት ስለዘፈን ሁኔታ ይገልፃሉ :- “ዘፈን ከታላላቅ የሰይጣን ድምፃችና ነፍስን የሚያስበረግግበት፣ የሚረብሽበት እና ሰላም የሚነሰት ለመሆኑ አያጠራጥርም የቁርአን ወደሚረጋጋበት፣ ሰላም የሚያገኝበትና ወደጌታዋ እንድትመለስ የሚያደርገውን ተቃራኒ ነው፡፡” 👉 ቀሪውን ክፍል በሚከተለው ሊንክ ያንብቡ https://nesiha.com/%e1%8a%a5%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%88%99%e1%8b%9a%e1%89%83%e1%8a%93-%e1%8b%98%e1%8d%88%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%88%b5%e1%88%8b%e1%88%9d-%e1%8a%a0%e1%88%8d%e1%89%b0%e1%8a%a8%e1%88%88%e1%8a%a8/ ┄┄┉┉✽‌»‌‌🌼»‌‌✽‌┉┉┄┄ © ተንቢሀት @tenbihat

🌟 ብዥታና እውነታ! 👌 በአጥማሚዎች ሹቡሀት ላለመደናገር የሚያግዝ ወቅታዊ መልዕክት! 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/590 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

👌 ብዥታና እውነታ! 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ በአጥማሚዎች ሹቡሀት ላለመደናገር የሚያግዝ ወቅታዊ መልዕክት! 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/589 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📹 የትዕግስት ፍሬ በነብዩ አዩብ ታሪክ 🌟 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🟦 የ youtube ሊንክ https://youtu.be/i6vrsSuFzwY?si=43zSaPrX2T01mX3v 🌟 Audio MP3 https://t.me/abujunaidposts/356 ---------------- 📮 የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔈 የሙሐደራዎች ማውጫ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ 1) ተውሒድ በሱረቱል ከሕፍ ታሪኮች https://t.me/abujunaidposts/136 2) ኢስላማዊ ማንነት https://t.me/abujunaidposts/391 3) ወደ አላህ ሽሹ https://t.me/abujunaidposts/184 4) ቁርአን የልብ ብርሃን! https://t.me/abujunaidposts/97 5) የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት https://t.me/abujunaidposts/92 6) የሰለፎች ብሩህ ፋና! https://t.me/abujunaidposts/521 7) ደስተኛ ኢስላማዊ ቤተሰብ https://t.me/abujunaidposts/103 8) እህቴ ሆይ! ከሷሊሀት ነሽን? https://t.me/abujunaidposts/153 9) የትዳር አለመግባባትና ሸሪዓዊ መፍትሄዎቹ https://t.me/abujunaidposts/190 10)  የሙስሊም ወጣቶች ሚና እና ሃላፊነት https://t.me/abujunaidposts/143 11) ከተርቢያ ጥበቦች https://t.me/abujunaidposts/341 12) የተውሒድ እውነታ በቁርአን እይታ https://t.me/abujunaidposts/360 13) ተጋሾችን አበስራቸው https://t.me/abujunaidposts/416 14) መውሊድ.. ብዥታዎችና መልሶቻቸው https://t.me/abujunaidposts/105 15) መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? (በነሲሓ ቲቪ  የቀረበ አጭር  ውይይት)  https://t.me/abujunaidposts/514 16) የሙስሊሞች አንድነት https://t.me/abujunaidposts/132 17) የቁርአን ወዳጆች https://t.me/abujunaidposts/147 18) የአላህ ስሞችና ሲፋት https://t.me/abujunaidposts/160 19) የረጀብ ወር እና ድንጋጌዎቹ https://t.me/abujunaidposts/322 20) የሰለፎች ልገሳና አርአያነቱ https://t.me/abujunaidposts/86 21)  ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች https://t.me/abujunaidposts/47 22) ዒባዳን ለመገንዘብ! https://t.me/abujunaidposts/209 23) የኑህ መርከብ https://t.me/abujunaidposts/520 24) ሸ/ ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲል ወሓብ (ብዥታዎችና መልሶቻቸው) https://t.me/abujunaidposts/215 25) የዳዕዋ መሰረቶች https://t.me/abujunaidposts/237 26) ዓቂዳ እና መንሐጅ... 9 ወሳኝ ነጥቦች  https://t.me/abujunaidposts/88 27) የመሰባሰብ (መጃሊስ) አዳቦች https://t.me/abujunaidposts/343 28)  አምስት ምክሮች ለቁርአን ሐፊዞች https://t.me/abujunaidposts/72 29) ተውሒድ በምሳሌ https://t.me/abujunaidposts/484 30) ሱናን መከተል https://t.me/abujunaidposts/395 31) የመስጂዶች ሚና https://t.me/abujunaidposts/399 32) ቅድሚያ ለተውሒድ (በትርጉም የቀረበ) ዶ/አብደላህ አልጀርቡዕ https://t.me/abujunaidposts/125 33) የህይወት ጥያቄዎች (በትርጉም የቀረበ) ዶ/ሚስዓድ አልሑሰይኒይ https://t.me/abujunaidposts/177 34) ከሱረቱል ፋቲሀ ቁምነገሮች (በትርጉም የቀረበ) ዶክተር ሙሀመድ አልሁጀይሊይ https://t.me/abujunaidposts/217 35) የትዕግስት ፍሬ በነብዩ አዩብ ታሪክ https://t.me/abujunaidposts/356 36) ይህ ነው ዳዕዋችን https://t.me/abujunaidposts/551 37) የወንዶች አለባበስ https://t.me/abujunaidposts/545 38) ከኢስባል እንጠንቀቅ! https://t.me/abujunaidposts/537 39) ንፁሕ ልብ https://t.me/abujunaidposts/137 40) እውነትን ፍለጋ! የሰልማን አልፋሪሲይ የመስለም ታሪክ https://t.me/abujunaidposts/581 41) ደስተኛ ህይወት ምንድነው? የ "አልወሳኢል አልሙፊዳ" መግቢያ https://t.me/abujunaidposts/585 42) የከሽፉ ሹቡሃት ኪታብ መልእክቶች(1-8) https://t.me/abujunaidposts/439 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ። ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ [2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን። ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት https://tewhidfirst.blogspot.com/2015/09/blog-post_13.html?m=1 __ 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች t.me/abujunaidposts

🌟 ደስተኛ ህይወት ምንድነው? የ "አልወሳኢል አልሙፊዳ" ማብራሪያ መቅድም የተወሰደ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts