en
Feedback
ወርቃማዎች

ወርቃማዎች

Open in Telegram
540
Subscribers
-324 hours
-57 days
-130 days
Posts Archive
ወንድሜ ማንም አይፈልገኝም ብለህ አትከፋ ! ሚሊሻ 👮‍♂️አጥብቆ ይፈልግሀል 😂 አብሽር

አንዋር መስጂድ በየአመቱ ሁለት ግመል አንዳንዴም ከዛ በላይ ይገባል ። በእለቱ ግን የሚደርሰን ከረሜላ ነው ብቻ ነገሩ ውስብስብ ነው ። አማራጭ መስጂድ መፈለግ ይኖርብኛል።

ዛሬ ሰፈር ስደርስ ፖሊስ ግርግር አለእኔም ደንግጬ ወንድሜን ደውዬ “የት ነህ?” ስለው “ቤት ነኝ” አለኝ አልሐምዱሊላህ ብዬ ወደ ቤት ስሄድ 😂 አጠገቤ ያለ ልጅ አስነጠሰ 😭😂 እኔም እንደተተኮሰ ጥይት እሩጫዬን ጀመርኩ🏃‍♀️ቤት በር ጋር ደርሼ መቆም አቅቶኝ በሩን አልፌ ተመልሼ ነው የገባሁት🤣🤣🤣

የሆነ ቤት በተዘረፈ ቁጥር የሰፈር ሰው ተሰብስቦ"ይሄማ ውስጥ አዋቂ ነው ከሩቅ አልመጣም"የሚሉት ነገር🤔

መቼም የማይረሳኝ ገጠመኝ። 1997 መርካቶ ላይ አፈሳ ተጧጡፎ ወጣት የሆነ ሙስሊሙም ክርስቲያኑም ለማምለጥ ጀለቢያ ይለብስ ነበር። እና ሀለፎም የሚባል የሰፈራችን ልጅ ጀለቢያ ይገደግድና ወደ በርበሬ በረንዳ ይሄዳል። በትልቅ ካቻማሌ ወጣቱ ሲጫን ጀለቢያ ለበስኩ ብሎ እየተንቀባረረ ሲንጎማለል አንድ ወታደር “አንተ ና ወደዚህ፣ግባ ወደ መኪናው” ሲለው “አረ ሙስሊም ነኝ ከመስጂድ ነው እየመጣሁ ያለሁት ጀለቢያ ለብሼ አታየኝም?” ሲለው ወታደሩ ምን ቢል አሪፍ ነው። “ዝም ብለህ ግባ ለዱአ ታስፈልገናለህ” አረ ኡኡኡኡኡ😂😂😂😂 መልካም ቅዳሜ

ደሞዝህ ስንት ነው? ምን ያደርግልሻል? ቢሉን ማን እንደሚዘጋው ለመወሰን እንዲመቸን ልበልህ¡? አንቺ እድሜሽ ስንት ነው? ምን ያደርግልሀል? ሞግዚት ማን እንደሚያስፈልገው ለመለየት እንዲመቸን ልበልሽ¡? አንተ ደሞ የሆነ ግግም የምትለው ነገር አለህ አንቺስ ምን አለሽ? እኔማ አንተነህ ያለኸኝ ሌላ ምን ይኖረኛል? ውይ የኔ እናት ይቅርታ ስለሰገጥኩብሽ ችግር የለውም የኔ ጌታ በቃ የፈለግሽውን ጠይቂኝ ከዚ በኋላ የኔ ፍቅር ደሞዝህ ስንት ነው? ኧሯሯሯ

😥 ስቅስቅ ብዬ ነው ያለቀስኩት ጠዋት ፌስቡክ ከፍቼ ስገባ አይቸው 🥹 እናታቸው የሞተችባቸው አሊያም ተፋተው ልጆቻቸውን ይዘው ከእናንተ ጋር የሚኖሩ ባሎች ያላችሁ ሴቶች እንደው አደራችሁን ልጆችን በሆድ እንዳትቀጡ 😒 በጣም መጥፎ እና ከባድ ነገር ቢኖር ልጆች ረሃብ አይችሉም 💔 ሁሉም እንጀራ እናቶች መጥፎ ናቸው ወይም ጥሩ ናቸው ብሎ ለመደምደም ያስቸግራል ! እንክብካቤያቸው እናትን የሚያስንቁ እንጀራ እናቶች ስላሉ በጅምላ መውቀጥ ነውር ነው ! እኔ የ እንጀራ እናትን እጅ ቀምሻለሁ! አባቴ ጠንካራ ስለሆነ እንጂ ብዙ በደል ነው የምታደርስብን ! ሰራተኞቹን እንኳን ይታዘቡኛል አትልም 🧐 በምግብ በኩል ከአባታችን እጅ ካልሆነ ስለማንበላ በተለይ እኔ ሩቅ ሐገር ካልሄደ በስተቀር ሚስትና ሰራተኛ አምኖ አይተወንም ይሰጧቸዋል ብሎ ! ጠዋት አብልቶን ወደ ሥራ ~ ምሳ ሰዓት መጥቶ አብልቶን ይመለሳል ~ መቅሰስ ካልተመቸው አደራ ይሰጣል ለሁለታቸውም ( ሲመጣ የተሰራውን ሁሉ በዝርዝር ዘጋቢዋ እኔ ስራዬን እቀጥላለሁ 🤭) እራታችንንም አብልቶን አጣጥቦ ነው የሚያስተኛን 😍 ሲበዛ ክፉ ናት በሌሉት በእናቶቻችን ሁላ ነው እየቀናች የነሱን ንዴት እኛ ላይ የምታበርደው 🫤 ቀን ምንም ሳናጠፋ ሁላ ነው የምትማታው ~ አንዳችን ካጠፋንም ሶስታችንንም በጫማ ጥፊ አንገብግባ ትለቀናለች 🥹 አባቴ ሲመጣ ግን አስገርፋታለሁ 🤭 ቀን ስትወግረን የዋለችውን እሷን ደግሞ አባቴ ማታ በጥቁር ሶኬት በቀሚሷ ፊቷን ሸፍኖ ያቀምስልናል እንባችን በከንቱ አይቀርም ምክንያቱም ምንም እንደማናጠፋ እርግጠኛ ነው አባቴ ! አንድም ነገር ሳልደብቅ ነው የምናገረው ! ከሁሉም አሁን ድረስ በጣም የሚያናድደኝ ጥራጥሬ እወዳለሁ ንፍሮም ሆነ ቆሎ ግን እያየነው አንቀምሰውም አትሰጠንማ 😥 የሆነ ቀን ስንጫወት ወድቄ አፍንጫና ጉልበቴ ተፋቀ በማንኪያ ከተጣደው ንፍሮ አውጥታ አሽትች ካ ለችኝ በኃላ ቆሻሻ ውስጥ ልትደፋው ብላ አይ በቃ ብይው ብላ አፌን ከፍታ ትኩስ ንፍሮ የጨመረችው አይረሳኝም 🙃 ውይ ብሶት አበዛሁ 😵‍💫 እናም ሴቶችየ ወንዱ በደላችሁም አልበደላችሁም ከሌላ የወለዳቸውን ልጆች አታስርቡ አታስጠሙ በአሏህ! ወንዶችም ለሚ ስትም ለልጆችም ፍትሃዊ ሁኑ አትልፈስፈሱ 😵‍💫 ንግግራችሁ ( አምባገነን የሆነውን አላልኩም ፍትህ ያለውን እንጂ ) ተሰሚነት እንዲኖረው ሁኑ 🧐 ማግባትና መውለድ ብቻ ቁምነገር አይደለም !!

photo content

ነይ እስኪ ሀጂ መኪና ግፊልኝ ብሎ ከገፋለት በኋላ ኪሱ ሲገባ ስልኩ የለም 😂😂😂😂😂😂

ደግሞ በስኳር ቡና እየጠጣ ፣ ' ቡናኮ' ይላል ። ወሬኛ ።

ውይ ውይ አቤት ቅሌት ቀለልኩላቹ ወላሂ😭💔😂 መንገድ ላይ ከፊት ለፊቴ አንድ ልጅ ሲመጣ አየሁት እቃ የሚያመጣልኝ ከስተመሬ ነው ብዬ ልክ አጠገቤ ሲደርስ "አንተ እዚም እየዞርክ ነው" ብዬ ፈገግ😊 ስል ግራ በተጋባ ሁኔታ በደረቅ ፈገግታ "እሺ ሰላም ነው"🙄 ብሎኝ ሲያልፍ ያመዋል እንዴ ብዬ ልክ አንድ ሁለት እንደተራመድኩ ትዝ ሲለኝ ለካ አንድ ቀን ባንክ ሄጄ የሆነ ነገር አስተካክልልኝ ስለው እኔ አላውቅም ማናጀሩን አናግሪ ሲለኝ "ምናለ ባትጠም ጠማማ" ያልኩት ባንከር ቢሆንስ 😭😭😭 ነገ እንዴት ነው እዛ ባንክ ምሄደው አረ ምን ይሻለኛል💔😭

የአረብ ቀልድ ልንገራቹማ አንድ ግመል ነጋዴ አረብ ሊያጭ ይሄዳል ከዛም የልጅቷ ቤተሰቦች መህር 40ሺ ይሉታል ምን ቢል ጥሩ ነው እነ እንትና ቤት እኮ ከእነ ልጇ በ20ሺ አግኝቻለው 😂😂😂😂

በአንድ ወቅት እጅግ ተጫዋች፣ ፈጣንና በደስታ የተሞላችሁ ሰው የነበራችሁበት ጊዜ ነበር...ዛሬ ግን ዝምታን፣ ብቸኝነትንና መረጋጋትን ልትመርጡ ትችላላችሁ።🙌 ​ይህ ማለት ማንነታችሁን አጣችሁ ማለት አይደለም፤ ህይወት ያስተማረቻችሁ ትምህርት፣ ያለፋችሁበት ፈተና እና የገጠማችሁ ድካም የፈጠረው ተፈጥሯዊ የጥበቃ መንገድ (Self-protection) ነው። ጸጥ ማለታችሁ ድካም ቢመስልም፣ የውስጥ ሰላማችሁን ለመጠበቅ ያበጀችሁት ወሰን ሊሆን ይችላል።🤝 ዝም ማለታችሁ ወይም ድካም መሰማቱ የተሰበራችሁ ያደርጋችኋል ማለት አይደለም። አንዳንዴ አእምሮአችን ራሱን ለማደስ (Recharge) ለማድረግ ጊዜ ይፈልጋል። ለራሳችሁ እረፍትና ፍቅር ስጡ።🤌 Silence isn't always a sign of defeat; sometimes it's your soul's way of resting and rebuilding. Be gentle with yourself.🔥 ቀድሞ ከነበራችሁበት ተጫዋችነት ወደ ዝምታ እንድትቀየሩ ያደረጋችሁ የህይወት አጋጣሚ አለ? በርቱ! አመሰግናለሁ 🙂

አሁን የገጠመኝ አብነት ጋር ታክሲ ውስጥ ..ታክሲው ገና እየጫነ እያለ ሁለት ተሳፋሪዎች አጠገቤ ፀብ ጀመሩ! ከዛ አንዱ ሽጉጥ አወጣ ልጁ ሽጉጥ ስለያዝክ ምሰማህ መሰለህ እንዴ? እያለ በboክስ ላጥ ላጥ ደም በdም አደረገው። ስንት አይነት ጀግና ወንድ አለ እኔ እዳይተኩስ ወይ እንዳይባርቅበት ደንግጬ ዘልዬ ውርድ ! ለራሴ አራት ሚስት የማግባት እቅድ ያለኝ ሰው ነኝ በጊዜ ሊቋጨኝ ብዬ😀 ልጁም ወርዶ ሮጠ ሰውዬው ወደ ላይ ተኮሰ ።የታክሲውን ሰው አትወርዱም ብሎ ያዛቸው እኔ የናቴ ዱዐ ጠበቀኝ ሌላ ታክሲ ይዤ ወደ ቤቴ😌

በነገራችን ላይ የሆነ ወቅት ላይ ተቸግረህ ስለደረሰልህ ብቻ እንደ ኢሉምናቲ ማንነትህን እንድትገብርለት የሚፈልግ ሰው ነፍ ነው። ምክንያቱም የሆነቀን የቆመበት እንደሚከዳው ስለሚያውቅ ለዛች ቀን የሚሆነውን ስንቅ ዛሬ ላይ ነው በችግር ጎንህ መጥቶ የሚቋጥረው። ከዛ የዚህን ሰው አደገኛነት መቼ መሰለህ የምታየው ልክ መንሸራተት ሲጀምር ነው። ይመጣና ደግፈኝንጂ ይልሀል። በራሱ ደንባራ አረማመድ እራሱላይ ያመጣውን ውድቀት ብቻውን መጋፈጥ አይፈልግም። የሆነ ቀን ተቸግረህ ያደረገልህን እያስታወሰ ዛሬላይ ህልውናህን አሳልፈህ እንድትሰጠው ይጠይቅሀል። አይ ያኔ እገዛህን ስቀበል ራሴን አልሸጥኩልህም ባመንኩበት ጉዳይ ብቻ ነው የማግዝህ ስትለው ልፈፋውን ይጀምራል። ያኔ እንዲ አርጌለት እሱግን ዛሬ አላግዝ አለኝ ጲሪሪም ጳራራም ምናምን... ውለታን መቁጠር የጀመርክ ሰአት ነው ውለታነቱ የሚያበቃው! ሲጀመር ውለታ ከተቆጠረ manipulation ነው

ሀኪሙ ታማሚዎችን እየጎበኘ አንዱ ታማሚ ግርግዳውን በቴስተ ሲመታ አየው ''ምን ሆኖ ነው?'' አለ "አንድ ልጅ እሱን ትታ ሌላ አግብታ ነው" አሉት የሚቀጥለው ክፍል ሲገባ ሌላኛው ታማሚ ጭንቅላቱን በ
ሀኪሙ ታማሚዎችን እየጎበኘ አንዱ ታማሚ ግርግዳውን በቴስተ ሲመታ አየው ''ምን ሆኖ ነው?'' አለ "አንድ ልጅ እሱን ትታ ሌላ አግብታ ነው" አሉት የሚቀጥለው ክፍል ሲገባ ሌላኛው ታማሚ ጭንቅላቱን በጫማ ይመታል "ይሄስ ምን ሁኖ ነው?" "ያቺን ልጅ ያገባት እሱ ነው"🚶

የህግ ተማሪዎችን 4 ከ Square root እንዴት ይወጣል ስትላቸው... ( በዋስ )

"ጌታህም ለባሮቹ በዳይ አይደለም::"💙🤍

ከአንዳንድ ፕሮግራም በኋላ ምሳ በልተን ስንጨርስ ጫት ያዝ ሲሉኝ 😊
ከአንዳንድ ፕሮግራም በኋላ ምሳ በልተን ስንጨርስ ጫት ያዝ ሲሉኝ 😊

አይስክሬም ሻጩን የሚጎዳው ተመሳሳይ ዝናብ...ለጃንጥላ ሻጩ ደግሞ ትልቅ እድልና በረከት ነው። እያንዳንዱ ቀን ለእኛ ብቻ ይመች ዘንድ አልተፈጠረም! and that's okay.🙌 ​ህይወት የሁልጊዜ ደስታና ስኬት ብቻ አይደለችም። ለእኛ ፈተናና መጥፎ አጋጣሚ የሚመስለን ነገር፣ ለሌላው ሰው ደግሞ በረከትና አዲስ እድል ሊሆን ይችላል።🤷‍♀️ ​ሁሉም ቀን ለእኛ ተመችቶ አይውልም፤ የህይወት ውበቷም ያለው በዚህ ሚዛን ውስጥ ነው። ነገሮች እንደፈለግነው ባልሄዱ ቁጥር ከመበሳጨት ይልቅ፣ የሂደቱ አካል መሆኑን አምኖ መቀበል ትልቁ የአእምሮ እረፍት ነው። ✨ ​ሁልጊዜ አየር ሁኔታው ወይም ሁኔታዎች ለእናንተ ብቻ እንዲመቹ አትጠብቁ! ​በህይወታችን ውስጥ የምናልፍባቸው አስቸጋሪ ቀናት የራሳቸው የሆነ ዓላማ አላቸው!🔥 ​~አንድ ነገር ለእኛ አልሳካ ማለቱ ዓለም አበቃች ማለት አይደለም፤ ይልቁንም የህይወት ሚዛን መጠበቂያ መንገድ ነው። ​~ዛሬ ዝናቡ የእናንተን መንገድ ቢያስተጓጉል እንኳ፣ ነገ ደግሞ ፀሐይ ለእናንተ ትወጣለች። ቀናትን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር አለመሞከር የአእምሮ ሰላም ይሰጣል።😍 ​Not every storm comes to disrupt your life; some come to balance it. Trust the timing and accept that not every day is meant to be yours.🌧️🧠✨ በርቱ! አመሰግናለሁ🙂 @WERKAMAA