en
Feedback
CHARACTER HALLMARK ACADEMY S.C

CHARACTER HALLMARK ACADEMY S.C

Open in Telegram

Changing Lives Forever!!“ራእዩ ገና እስከ ተወሰነው ጊዜ ነው፥ ወደ ፍጻሜውም ይቸኵላል፥ እርሱም አይዋሽም፤ ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው፤ እርሱ አይዘገይም።” — ዕንባቆም 2፥3 “For the vision is yet for an appointed time, but at the end it shall speak, and not lie: though it tarry, wait for it; because

Show more
896
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-130 days
Posts Archive
General Science ANSWER G-8.pdf2.11 KB

+4
Grade_12_Mathematic_Model_2016_answer_key_for_Natural_and_Social.pdf1.94 KB

2016 ዓ.ም ሞዴል ፈተና መልስ።

ሰላም ለሁላችን ይሁን የስምንተኛ ክፍል የሞዴል ፈተና በሰላም ተጠናቋል። የፈተና ወረቀት በአገባቡ በማስቀመጥ ቀጥለውም እስከ ዋናው ፈተና ድረስ የሚፈተኗቸውን ፈተናዎች ደጋግሞ በመስራት እንዲያጠኑ ይሁን። የስድስተኛ ክፍል ሞዴል ነገ 4:00 ሰዓት የሚጠናቀቅ ይሆናል። ከታች የፈተናዎቹን መልሶች እንደደረሰን እናጋራችኋለን ፕሪንት እያደረጋችሁ ብትሰጧቸው ከፈተናው ወረቀት ጋር እንዲያይዙት እና እንዲያጠኑት ይረዳቸዋል። መልካም ቀን

ውድ ወላጆች ልጅዎን ነገ ከጠዋቱ 2:00 ሰአት በማምጣት የተጀመሩ ስራዎችን ይበልጥ ማስቀጠል እንድንችል ይተባበሩን። የት/ቤቱ አስተዳደር።

photo content
+3

photo content
+9

የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ትም/ጽ/ቤት የስርዓተ ትምህርት ትግበራ ቡድን ለሁለቱም መርሃ-ግብር ለጓልማሶች እና አማራጭ መሠረታዊ ትምህርት በነደፈው ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ካራክተር ሆል ማርክ አካዳሚ ለጠየቅነው ጥያቄ ፈጣን ምላሽ በመስጠት በቀን 26/04/2016 ዓ.ም ወረዳው ውስጥ ለሚኖሩ 50 ችግረኛ ወላጆች እና ለልጆቻቸው የምሳ ግብዣ እና የአልባሳት ስጦታ አበርክቶል።በእለቱ የትም/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሞላ መንገሻ፣ቡድን መሪዎች፣ ባለሙያዎች፣ሱፐርቫይዘሮች፣የመንግስት ት/ቤት ወተመህ ሰብሳቢ ወ/ሮ እሌኒ እና የክብር ተጋባዥ እንግዳ ከሴቶች፡ህፃናት እና ማህበራዊ ጽ/ቤት ተወካይ ወ/ሮ ቤተልሄም በተገኙበት ፕሮግራሙን በደመቀ መልኩ ማስኬድ ተችላሏል።ፕሮግራሙን እና ዝግጅቱን የአንበሳውን ድርሻ ወስደው በበላይት ሲመሩ እና ሲያስተባብሩ የነበሩት የት/ቤቱ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ነበሩ፣ካራክተሮች ለሰው ተኮር ተግባራችሁ ከልብ እናመሰግናለን። በጨማሪም ተቋሙ በም/በር ቁ.2 ት/ቤት ለምትማር የ8ኛ ክፍል ተማሪ መሉ መጪዋን ሸፍኖ መነፀር ሊያሰራት ቃል ገብቷል ለዚህም ምስጋና እናቀርባለን።

ውድ ወላጆች እንኳን ደስ አላችሁ። የት/ቤቱ የበጎ አድራጎት ክበብ ተፅህኖውን በማስፋት የእ/ርን አላማ አሳክቷል። በእለቱ ለተጋበዙት እንግዶች የምስራቹ ቃል ተነግሯል። ማዕድ አጋርተናል፣የአልባሳት ስጦታዎችም ተደርገዋል። የበጎ ስራዎችም ተከናውኗል። የክበቡ አስተባባሪዎች በተለይም ተማሪ ምህረት ሚኒሊክና ጓደኞቿ በሲኤምሲ የምትገኙ ተማሪዎቻችን ከት/ቤት ባሻገር ማህበረሰቡ ድረስ ቤት ለቤት ላደረጋችሁት ትጋት ብድራታችሁ ከጌታ ዘንድ የከበረ ነውና በርቱልን።እንዲሁም በእለቱ የተገኛችሁ የ12ክፍል ተማሪዎች ላደረጋችሁት አርአያነት ተግባር ጌታ አብዝቶ ይባርካችሁ።

ለመላው የካራክተር ሆል ማርክ አካዳሚ ወላጆች ሁሉ መልካም የልደት በአል ይሁንላችሁ። በዓሉ የጌታን መወለድ፣ማገልገልና የአብን ፈቃድ አድርጎ እንዳለፈ እንዲሁም በመነሳቱና በክብር ሊወስደን እንደሚመጣ እያሰብን እንድናከብር ጌታ ይርዳን እላለሁ። ተባረኩልኝ።

ሰላም ለካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ ቤተበቦች የተከበራችሁ #የሁለተኛ_ደረጃ ተማሪዎቻችን እና ወላጆቻቸው በሙሉ  እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም የጤናና የአንድነት እንዲሆንልዎ እንመኛለን!!! የአስራ ሁለተኛ (12ኛ) ክፍል ተማሪዎቻችችን በሙሉ በበዓሉ ሳይዘናጉ እሮብ ለሚጀምረው ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና እንዲዘጋጁ እያሳሰብን የተቀሩትም ከ9ነኛ - 11ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ሁለተኛ ፈተናቸው ዕሮቡ የሚቀጥ ይሆናል። የሁለተኛው ሩብ አመት ማጠቃለያ ፈተናም ከአንድ ሳምንት በኋላ ማለትም ከጥር13/2016ዓም ጀምሮ በመሆኑ ተማሪዎች ሳይንጠባጠቡ ከበዓል መልስ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ እንጠይቃለን። ሁሉም የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ተፈታኞች መሆናቸውን በአለመዘንጋት የፈተና ዝግጅት ላይ በመሆን በዓሉን ያከብሩ ዘንድ እናሳስባለን። ረቡዕ ዕለት ሲመጡ የትምህርት መሳሪያቸውን አሟልተው እንዲሁም የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ ማጥቆሪያ እርሳስ፣ የእርሳስ መቅረጫ እና ላፒስ መያዝ የሁሉም ተማሪዎች ግዴታ ነው። ሁሉም ሲሆን ለተማሪዎች ጥቅም ለጌታ ክብር ይሁን። እናመሰግናለን t.me/characterhallmark

ሰላም ለሁላችን ይሁን ለተከበራችሁ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎቻችን ወላጆች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ። ለመላው ቤተሰብ መልካም የበዓል ጊዜ እንዲሆን እንመኛለን!!! የስድስተኛ እና የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎቻችችን በበዓሉ ሳይዘናጉ እሮብ ለሚጀምረው ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና እንዲዘጋጁ እያሳሰብን ትምህርት ማክሰኞ የሚቀጥል ሲሆን የሁለተኛው ሩብ አመት ማጠቃለያ ፈተናም ከአንድ ሳምንት በኋላ በመሆኑ ተማሪዎች ሳይንጠባጠቡ ከበዓል መልስ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ እንጠይቃለን። ተፈታኞች ረቡዕ ዕለት በጠዋት ሁለት ሰዓት በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት የሚሰጠውን ገለፃ/Orientation/ እንዲቀበሉ እንዲሁም የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ ማጥቆሪያ እርሳስ እና ላፒስ እንዲይዙ ያስፈልጋል። እናመሰግናለን

ለ11ም ክፍለ ከተማ

መልካም የጌታችንና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በአል ይሁንልን። ዛሬም ጌታ በመንፈሱ ከእኛ ጋራ ነው። አማኑኤል ከእኛ ጋራ ነው!!! ልጆቻችን በደስታ ንጉሳቸውን የሾሙበት ቀን ነው። በበጎ ፈቃዳችሁ ጌታን ታዛችሁ ላገለገላችሁን ሁሉ ከጌታ ቤት ባረክናችሁ። ለበረከትም ሁኑ። የበአሉ ስሜት በጥቂቱ በኬጂ እና በዋናው ግቢ ይህንን ይመስል ነበር። መልካም በአል ይሁንላችሁ።

20240104_085705.jpg1.90 MB

20240104_113308.jpg1.20 MB

20240104_140024.jpg2.47 MB

Training on goal setting and achievement by Brother Sinetibub.

20240103_084151.jpg2.24 MB